05/04/2025
ለክቡር ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ አቀባበል ተደረገላቸው።
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ለተመደቡት ክቡር ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በኮሚሽኑ የማኔጅመንት አባላት እና መኮንኖች የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ላይ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እና የሰው ኃብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር አያልነህ ተስፋዬ የተቋሙን አመራሮች እና አባላትን በመወከል አዲስ የተመደቡትን ክቡር ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴን እንኳን ደህና መጡ ብለዉ በከፍተኛ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ለህብረተሰቡ ሰላም በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
ክቡር ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በበኩላቸው ፖሊሳዊ ብቃት እና ስብዕናን የተላበሰ የተሰጠውን ተልዕኮ የሚወጣ ዘመናዊ ፖሊስ እና አደረጃጀት በመፍጠር የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በጋራ እና በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።