19/02/2026
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለ63 አቅመደካሞች የረመዷን አስቤዛ አከፋፈለ።
ተመረሮት ኮሚኒኬሽን
የካቲት 09/2018
አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
እንኳን 1447 ዓ/ሂ የረመዷን ፆም በሰላም አደረሳችሁ
ረመዷን ሙባረክ
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ዛሬ እለተ ሰኞ የካቲት 09/2018 ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ካሉ ከአካባቢው ወጣቶችና የማህበሩ አባላት ጋር በመተባበር ከመቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ብር ወጪ በማድረግ ለ63 (ስልሳ ሶስት) አቅመደካሞች የረመዷን አስቤዛ አከፋፈለ።
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለአቅመደካሞች በየአመቱ አቅመደካሞች የረመዷን ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል። ዘንድሮም በ 2018 ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ካሉ ከአካባቢው ወጣቶችና የማህበሩ አባላት ጋር በመተባበር ለ63 አቅመደካሞች ማከፋፈል ተችሏል።
በዚህም መርሓግብር ለአንድ ቤተሰብ 8 ኪሎ ቅንጬ እና አንድ ሊትር ዘይት ማከፋፈል ተችሏል።
ይህ ድጋፍ የተከናወነው የተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር አባላት እና የማህበሩ ደጋፊዎች ከሰበሰቡት ድጋፍ ነው። የማህበሩ አባላት በየወሩ ቋሚ መዋጮ የሚያደርጉ ሲሆን ማህበሩ ድጋፎችን የሚያደርገው ከዚህ መዋጮ፣ለረመዷን እና ለተለያዩ በዓላት ከሚሰበሰበስ ገንዘብና ማህበሩን ከሚደግፉ ደጋግ ግለሰቦች ጋር በመተባበር ነው።
የበጎ አድራጎት ማህበሩ ከዚህም ቀደም ብሎ ዘርፈ ብዙ የበጎና የልማት ተግባራት ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ከዚህ በፊት ከተከናወኑ የበጎና የልማት ስራዎች መካከል መንገድ የማስተካከል፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር፣ በሴቶችና ህፃናት ላይ ፆታዊ ትንኮሳ እንዳይደርስ ሰላም የማስከበር፣ በረመዳን ማፍጠሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ በኢድ ማክበሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ መታከሚያ ለሌላቸው የመታከሚያ ድጋፍ፣ ቤት ለሌላቸው ቤት መገንባት፣ ደብተርና እስክሪብቶ ማሟላት ለማችይችሉ ተማሪዎች ድጋፍ እና የመሳሰሉት ድጋፎች ከብዙ በጥቂቱ ለአብነት ያክል መጥቀስ ይቻላል።
ማህበሩ ለወደፊት ከዚህም በላይ ለመስራት ራዕይ ያለው ሲሆን መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ማህበሩ ያለመው ዓላማና ራዕይ ያሳካ ዘንድ ከጎኑ ይሆኑ ዘንድ በዚሁ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን።
በዚሁ አጋጣሚ ለዚህ መሳካት ትብብር ያደረጋችሁ ሁሉ በተለይም የማህበሩ አባላት፣ ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያላችሁ የማህበሩ ደጋፊዎች በማህበሩና በአባላቱ ስም ለማመስገን እንወዳለን። አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁ!! ጀዛኩሙላሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊኩም !!!
የማህበሩ አባል ለመሆን የሚከተለውን ሊንክ ጆይን ያድርጉ
1. Telegram: t.me/temerarot
2. Tiktok: temererot.charity
ማህበሩን ለመደገፍ ከፈለጉ በማህበሩ ስም በተከፈተ የንግድ ባንክ ቁጥር
የማህበሩ አካውንት ቁጥር/ንግድ ባንክ👇👇
1000504873416
የትመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር
ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ
// አቅመደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር