ተመረሮት የበጎ አድራጎት ማህበር Temererot Charity Association

  • Home
  • Ethiopia
  • Kibet
  • ተመረሮት የበጎ አድራጎት ማህበር Temererot Charity Association

ተመረሮት የበጎ አድራጎት ማህበር Temererot Charity Association Charity association

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለ63 አቅመደካሞች የረመዷን አስቤዛ አከፋፈለ።ተመረሮት ኮሚኒኬሽን የካቲት 09/2018አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህእንኳን 1447 ዓ/ሂ የረመዷን ፆም...
19/02/2026

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለ63 አቅመደካሞች የረመዷን አስቤዛ አከፋፈለ።

ተመረሮት ኮሚኒኬሽን
የካቲት 09/2018

አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ

እንኳን 1447 ዓ/ሂ የረመዷን ፆም በሰላም አደረሳችሁ

ረመዷን ሙባረክ

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ዛሬ እለተ ሰኞ የካቲት 09/2018 ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ካሉ ከአካባቢው ወጣቶችና የማህበሩ አባላት ጋር በመተባበር ከመቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ብር ወጪ በማድረግ ለ63 (ስልሳ ሶስት) አቅመደካሞች የረመዷን አስቤዛ አከፋፈለ።

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለአቅመደካሞች በየአመቱ አቅመደካሞች የረመዷን ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል። ዘንድሮም በ 2018 ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ካሉ ከአካባቢው ወጣቶችና የማህበሩ አባላት ጋር በመተባበር ለ63 አቅመደካሞች ማከፋፈል ተችሏል።

በዚህም መርሓግብር ለአንድ ቤተሰብ 8 ኪሎ ቅንጬ እና አንድ ሊትር ዘይት ማከፋፈል ተችሏል።

ይህ ድጋፍ የተከናወነው የተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር አባላት እና የማህበሩ ደጋፊዎች ከሰበሰቡት ድጋፍ ነው። የማህበሩ አባላት በየወሩ ቋሚ መዋጮ የሚያደርጉ ሲሆን ማህበሩ ድጋፎችን የሚያደርገው ከዚህ መዋጮ፣ለረመዷን እና ለተለያዩ በዓላት ከሚሰበሰበስ ገንዘብና ማህበሩን ከሚደግፉ ደጋግ ግለሰቦች ጋር በመተባበር ነው።

የበጎ አድራጎት ማህበሩ ከዚህም ቀደም ብሎ ዘርፈ ብዙ የበጎና የልማት ተግባራት ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ከዚህ በፊት ከተከናወኑ የበጎና የልማት ስራዎች መካከል መንገድ የማስተካከል፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር፣ በሴቶችና ህፃናት ላይ ፆታዊ ትንኮሳ እንዳይደርስ ሰላም የማስከበር፣ በረመዳን ማፍጠሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ በኢድ ማክበሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ መታከሚያ ለሌላቸው የመታከሚያ ድጋፍ፣ ቤት ለሌላቸው ቤት መገንባት፣ ደብተርና እስክሪብቶ ማሟላት ለማችይችሉ ተማሪዎች ድጋፍ እና የመሳሰሉት ድጋፎች ከብዙ በጥቂቱ ለአብነት ያክል መጥቀስ ይቻላል።

ማህበሩ ለወደፊት ከዚህም በላይ ለመስራት ራዕይ ያለው ሲሆን መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ማህበሩ ያለመው ዓላማና ራዕይ ያሳካ ዘንድ ከጎኑ ይሆኑ ዘንድ በዚሁ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን።

በዚሁ አጋጣሚ ለዚህ መሳካት ትብብር ያደረጋችሁ ሁሉ በተለይም የማህበሩ አባላት፣ ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያላችሁ የማህበሩ ደጋፊዎች በማህበሩና በአባላቱ ስም ለማመስገን እንወዳለን። አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁ!! ጀዛኩሙላሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊኩም !!!

የማህበሩ አባል ለመሆን የሚከተለውን ሊንክ ጆይን ያድርጉ
1. Telegram: t.me/temerarot
2. Tiktok: temererot.charity

ማህበሩን ለመደገፍ ከፈለጉ በማህበሩ ስም በተከፈተ የንግድ ባንክ ቁጥር

የማህበሩ አካውንት ቁጥር/ንግድ ባንክ👇👇

1000504873416
የትመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር
ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ

// አቅመደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር 15,000ብር ለአባታችን ሳሎ ባርጊቾ ህክምና በቲክታክ Live ኒያ አድርጓልማሻ አላህ ማሻ አላህአላሁ አክበር አላሁ አክበር
13/02/2026

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር 15,000ብር ለአባታችን ሳሎ ባርጊቾ ህክምና በቲክታክ Live ኒያ አድርጓል

ማሻ አላህ ማሻ አላህ

አላሁ አክበር አላሁ አክበር

27/01/2026

ለአቶ ሳሎ ባርጊቾ ገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌግራም ግሩፕ
Join አድርጉ

27/01/2026



አቶ ሳሎ ባርጊቾ ነዋሪነቱ ስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አስተዳደር አጎዴ ቀበሌ ሲሆን ለብዙ ዘመናት የቀበሌ አመራር ሆኖ ህብረተሰቡን እያገለገለ የነበረ ሲሆን እንዲሁም እንዲሁም ህመሙ እስኪጥለው ድረስ ቅበት ከተማ አስተዳደር አጎዴ ቀበሌ ምክትል ሊቀመንበር በመሆን እያገለገለ ቆይቷል።

በዚህ ሁኔታ ባለበት ነው እንግዲህ ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከአገልግሎት ውጪ የሆኑት(fail ያደረጉት)

ዛሬ በኩላሊት ህመም እየተሰቃየ የሚገኘው አባታችን አቶ ሳሎ ባርጊቾ የዛሬ አያድርገውና ከመታመሙ በፊት ደግ፣ ቅን እንዲሁም ለሰው አዛኝ እና ሩህሩህ ከመሆኑ የተነሳ የአካባቢው ማህበረሰብ "የደነብ ሼክ" በሚል መጠሪያ ስም ሲጠራው ቆይቷል።

አቶ ሳሎ ባርጊቾ በደረሰበት የኩላሊት ህመም ሁለቱም ኩላሊቶች ከጥቅም ውጪ በመሆናቸው ከ2015 ዓል ጀምሮ ከወራቤ ኮ/ስ/ሆ ሪፈር ተፅፎለት አዲስ አበባ ሲ.ኤም.ሲ አጠቃላይ ሆስፒታልከዚያም ወደ ኢትዮ ጠቢብ አጠቃላይ ሆስፒታል ተዛውሮ ለብዙ ወራት ፅኑ ህሙማን ክፍል ተኝቶ የታከመ ሲሆን ከታመመበት ግዜ ጀምሮ ትንሽ ሲያገግም ወደቤተሰብ እየተመለሰ ህመሙ ሲብስበት አአ የጠቀስናቸው ሆስፒታሎች ላይ እየተመላለሰ ቆይቶ ወራቤ ሂስፒታል የኩላሊት እጥበት/dialesis ሲጀምር ወደ ወራቤ በመዛወር ህክምናውን በመከታተል ላይ ይገኛል።

አባታችን አቶ ሳሎ ባርጊቾ ወደ ወራቤ ሆስፒታል በመመላለስ በሳምንት ሶስት ግዜ ለአንድ እጥበት ብቻ 5000/አምስት ሺህ ብር እንዲሁም ለመድሃኒት ብቻ 6000/ስድስት ሺህ ብር በመክፈል የኩላሊት እጥበት/dialesis በማድረግ ያለውን ገንዘብና ንብረት ጨርሶ የወገን ደራሽ ወገን ነውና እጁን ወደናንተ ደጋግ ወንድሞችና አህቶች እጁን ዘርግቷል።

ስለሆነም ውድና የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች “አንዲትን ነፍስ ያዳነ ሰዎችን ባጠቃላይ እንደማዳን“ ነውና አቶ ሳሎ ባርጊቾ ነፍስ ለማዳን ከፊታችን ቅዳሜ (23/05/2018) ጀምር ለተከታታይ ሰባት ቀናት አጎዴ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ስለተያዘ ሁላችሁም በቀጠሮው ቀን መኖሪያ ቤቱ ላይ በመገኘት አቅማችሁ የፈቀደውን ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በአላህ ስም እንማፀናችኋለን።

በአካል ለመገኘት የማትችሉ በወንድሞቹ (ሸረፋ ባርጊቾ፣ አብዶ ባርጊቾ እና ኢስማኢል ባሙድ) በጣምራ በተከፈተው የንግድ ባንክ ቁጥር
1000742285247
ገቢ ማድረግ ትችላለችሁ።

ለምታደርጉልኝ ድጋፍ ከወዲሁ አመሰግናለሁ፣ ጀዛኩሙላሁ ኸይረን ይላችኋል።
አባታችን አቶ ሳሎ ባርጊቾ!!
አላህ ከእንደዚህ አይነት አደጋ ይጠብቃችሁ!! አሚን!!

አድራሻ፦ ቅበት ከተማ አስተዳደር አጎዴ ቀበሌ መንደር 1 ከጥቁር አስፓልት ገባ ብሎ ወደ ሀረ-ሸይጣን ሀይቅ መሄጃ መንገድ።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር
0920 97 34 51
0912 91 34 21
ይደውሉ

07/08/2025

🎤🎤አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ🎤🎤

🔊🔊 //ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር// 📢📢📢

አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝

ውድና የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች!!

በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛልን!!
🤚🤚🤚🤚🤚🤚🤚🤚

በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አጎዴ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቅመ ደካሞች

1ኛ) ወ/ሮ ከድጃ ኡስማን ከ5(አምስት) ቤተሰቦች ጋር

2ኛ) አቶ አህመድ_አልሃዲ መሀመድ ከ2(ሁለት) ቤተሰቦች ጋር

ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሱት እናታችን ወ/ሮ ከድጃ ኡስማን በስልጤ ዞን ቅበት አጎዴ ቀበሌ ነዋሪ ስትሆን የ 5 ሴት ልጆች እናት ናት፡፡

ምንም እንኳን 5 ልጆች ቢኖሯትም እሷም ይሁን ልጆቿ ቤት ለመገንባት ቀርቶ ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ እንኳን መኖር አልቻለችም፡፡

ወ/ሮ ከድጃ ኡስማን የምትኖረው እጅግ በጣም ትንሸ እና ለመፍፈርስ በቀረበች ጎጆ ቤት ላይ እየኖረች ያለች እናታችን ስትሆን ምንም ሊረዳትና አይዞሸ ሊላት የሚችል አንድም ሰው የሌላት እንዲሁም ቤት ለመገንባትም ምንም አይነት የገንዘብ አቅም የሌላት መሆኑን ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር እሰከ ቤቷ ድረስ በመሄድ ለማጣራት ችሏል።
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

ቁጥር 2 ላይ የተጠቀሰው ወንድማችን አቶ አህመድ_አልሃዲ መሀመድ በስልጤ ዞን ቅበት አጎዴ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ባልትዳርና የ1 አባት ናት፡፡

አቶ አህመድ_አልሃዲ ምንም እንኳን ባልትዳርና የ 1 ልጅ አባት ቢሆንም ምንም አይነት እራሱን እና ቤተሰቡን የሚያስተዳድርበት አቅም የሌልው ከመሆኑም ባሻገር ቤት የሚባል ነገር የሌለው በመሆኑ ጅብ ከሚበላኝ ብሎ ከወንድሙ ጋር የሚኖር እጅግ በጣም አሳዛኝ ሚስኪን ወንድማችን ነው፡፡

ውድ ወንድምና እህቶች እስቲ እኔ በሆን ብለን እናስበው፣ መኖሪያ ቤት በማጣት ልጅና ምስት ይዞ ከወንድም ጋር መኖር!
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

አቶ አህመድ_አልሃዲ ከአቅመድካማነቱ በተጨማሪ በተፈጥሮ አንደበቱ የተሳሰረ በመሆኑ የመናገርና ከሰዎች ተግባብቶ በመስራት ኑሮውን የማሸነፍ እደል የለውም፡፡

ከላይ የተጠቀሱት 2/ሁለት አቅመደካሞች ወ/ሮ ከድጃ ኡስማን እና አቶ አህመድ_አልሃዲ መሀመድ

👉ወ/ሮ ከድጃ

😭መች በመች ቤቱ በላዬ ላይ ይደረመስ ይሆን!?
😭መች በመች ዝናብ ሲዘንብ ጎርፍ ይወስደኝ ይሆን!?
😭መች በመች ጅብ ይወስደኝ ይሆን!?

እንዲሁም
👉አቶ አህመድ_አልሃዲ
😭መች በመች ከወንድሜ ቤት ተባርሬ ልጄን ጅብ ይወስድብንኝ ይሆን!?
😭መች በመች ዝናብ ሲዘንብ ጎርፍ ይወስደን ይሆን!?

በማለት በስጋት ያለ እንቅልፍ እና ያለ እረፍት በስጋት ላይ እየኖሩ ይገኛሉ።

ወላሂ ውድ ወገኖቻችን የሁለቱን ቤተሰቦች ያሉበትን ሁኔታ የሚገልፅ ቪድዮ ብትመለከቱ እራሳችሁን መቆጣጠር ያቅታችኋል።

ለበለጠ መረጃ ቪድዮውን ብታዩት እውነታውን ልትረዱ ትችላላችሁ!

ስለዚህ ውድ ወገኖቻችን 2ቱ/ ሁለቱ አቅመደካሞች ወ/ሮ ከድጃ ኡስማን እና አቶ አህመድ_አልሃዲ መሀመድ ከነቤተሰቦቻቸው ጋር አደጋ ከደረሰባቸው በኋላ ከማልቀስና ከንፈር ከመምጠጥ ዛሬውኑ የአቅማችንን ያህል ድጋፍ በማድረግ ከተጋረጠባቸው ስጋት እንታደጋቸው ሲል ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ወገናዊና ሰብዓዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ለወገን ደራሽ ወገን ነውና አቅማችሁ የፈቀደውን ትንሽ ናት ሳትሉ ድጋፍ እንድታደርጉ በአላህ ስም እንጠይቃለን።

ድጋፍ ለማድረግ በተመረሮት በጎ አድራጎት መህበር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ገቢ ማድረግ ትችላላችሁ።
👇👇👇
1000504873416

ማሳሰቢያ፡

👉 ደጋፍ ለማድረግ በማህበሩ አካወንት በተጨማሪ በካሸና በቁሳቁስ ገቢ ማድረግ የምትፈልጉ
👌አጎዴና ቅበት ላይ 1/ ለጀማል መኪ 2/ ፈጅሩ ሱልጣን 3/ ሚፍታ አብዶ መስጠት ትችላላቸሁ
👌አዲስ አበባ ያላችሁ 1/ አብድረህማን መሀመድ 2/ አህመድ ሸፋ
ድጋፍ ስታደርጉ በ Material / በቁሳቁስ ቢሆን የበለጠ ተመራጭ ነው፡፡
👌ሳውዲ ያልችሁ 1/ ለሁሴን ባሙድ 2/ መሀመድ ሁሴን

👉ድጋፍ ስታደርጉ በ Material / በቁሳቁስ ቢሆን የበለጠ ተመራጭ ነው፡፡

//አቅመደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር የ2017 ዓመታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ።ሀምሌ 20/ 2017 ተመረሮት ኮሚኒኬሽንተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ዛሬ ሀምሌ 20/2017 ዓመታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ።...
27/07/2025

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር የ2017 ዓመታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ።

ሀምሌ 20/ 2017 ተመረሮት ኮሚኒኬሽን

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ዛሬ ሀምሌ 20/2017 ዓመታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ የማ/ሰብ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን ለአብነት ያክል
👉 የቅ/ከ/ወጣቶችና ስፖርት ጵ/ቤት ኃላፊ አቶ ሁሴን አማን፣ የቅ/ከተማ ጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ኸሊል፣
👉 የአጎዴ ቀበሌ ስራ አስኪያጅ አቶ ሀሰን አደም፣
👉 ምሁራን፣ ወጣቶች፣ አባወራዎች እና ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

መድረኩ በማህበሩ ፀኃፊ አቶ ሚፍታ መሀመድ የተመራ ሲሆን የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራት ተከናውነዋል።

1/ ለችግኝ ተከላ ጉርጓድ ቁፋሮ
2/ የእንኳን መጣችሁ መልዕክት በቅ/ከተማ ጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ኸሊል ቀርቧል።
3/ የመግቢያ ንግግር በቅ/ከ/ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሁሴን አማን ቀርቧል።
4/ በማህበሩ የተሰሩ ስራዎች ሪፖርትና የወደፊት ዕቅድ በማህበሩ ሰብሳቢ አቶ መሀመድ አብራር ቀርቧል።

ሪፖርቱ ላይ ከተነሱ አንኳር ተግባራት ለአብነት ያክል:

👉 ለ4 አቅመደካሞች ቤት ተገንብቷል
👉ከ 4 በላይ ለሆኑ ህመምተኞች ማሳከም
👉ከ200 በላይ ለሚሆኑ አቅመደካሞች የረመዳን አስቤዛና የአረፋ መክበሪያ ስጋ ተለግሷል
👉ከ10 በላይ ለሆኑ ደካማና ወላጅ አልባ ህፃናት የት/ት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል
👉 ለ2 ለተበላሹ መንገዶች ጥገና ተደርጓል

5/ የፓናል ውይይት ከታዳሚዎች ተደርጎ የወደፊት አቅጣጫ ተቀምጧል።
6/ ማህበሩ በሰራቸው በጎ ስራዎች ላይ ጉልህ ሚና ለነበራቸው ማህበራትና ግለሰቦች የማትጊያ ሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቷል።

ከተቋማት:-

👉ለቅ/ከ/አስተዳደር
👉ለቅ/ከ/ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት
👉ለቅ/ከ/ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት
👉ለቅ/ከ/ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት
👉ለአጎዴ ቀበሌ አስተዳደር

ከግለሰቦች
👉 ለኡስታዝ መሀመድ ሀሰን/ አቡ ሷሊህ ከአ/አ
👉ለአብድረህማን መሀመድ ከአ/አ
👉 ለአለዊያ ሀሰን ከወራቤ
👉ለኸይሪያ ስርሞሎ ከወራቤ

ከማህበራት:-
👉 ለሳውዲ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች
👉ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ኮሚቴዎች
👉ቲጋገዞት አሻዋ ማህበር
👉ያትኬሻን አሻዋ ማህበር
👉አሴ ለርከቦት ማህበር
👉የሱጅነ አሻዋ ማህበር
👉መሊቅ የዲንጋይ ማህበር

ከተነሱ ወሳኝ ሀሳቦች ለአብነት ያክል

1/ ማህበሩ ዘርፈብዙ በጎ ስራዎች እየሰራ ስለሆነ ሁሉም ሰው የማህበሩ አባልና አምባሳደር በመሆን ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት

2/ ለማህበሩ ቢሮ ስለሌለው በቀጣይነት እየሰራ ያለውን በጎ ስራ አጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ የቀበሌው አስተዳደር፣ የቅበት ከተማ አስተዳደር፣ የቀበሌው ማ/ሰብ፣ ወጣቶች፣ ዲያስፖራዎች እና ምሁራን ማህበሩ ቢሮ ይገነባ ዘንድ መተባበር አለባቸው

3/ ለወደፊት በታሰቡ በጎ ስራዎች ሁሉም ሊረባረብና ገቢ ሊያሰባስብ እንደሚገባ ተነስቷል።

በመሆኑም ማህበሩ ከዚህ በላይ ተጠናክሮ ይቀጥል ሁሉም አቅም በፈቀደው ይረባረብ የሚለው የማህበሩ ዋና መልዕክት ነው።

// አቅመ ደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር!!

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር  በ1ኛ ደረጃ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተለት።የቅበት ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት የ2017 በጀት አመት የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ ተግባራት ...
20/07/2025

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር በ1ኛ ደረጃ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የቅበት ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት የ2017 በጀት አመት የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ ተግባራት መዝጊያ እንዲሁም የ2017 የክረምት ወራት የበጎ ስራዎች ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ ሐምሌ 12/2017 አካሄዷል።

በመድረኩ ላይ የ2017 የበጋ ወራት የበጎ ስራዎች ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በክረምቱ ደግሞ የታሰቡ የበጎ ስራዎች ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ገደርጓል።

በዚህም ፕሮግራም በበጋው በጎ ስራ ላይ ለተሳተፉ የተለያዩ ግለሰቦች እና ተቋማት የምስጋናና የማትጊያ ሰርተፊኬት የተበረከተ ሲሆን

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር በበጋው የበጀት ዓመት ከበጎ አድራጎት ማህበራት አፈፃፀም 1ኛ ደረጃ በመሆን የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል።

በዚሁ አጋጣሚ ይህ ውጤት የብዙ አካላት የርብርብ ውጤት በመሆኑ የሚከተሉትን የማ/ሰብ ክፍሎች በማህበሩ ስም በልዩ ሁኔታ ምስጋና ማቅረብ እወዳለሁ።

1ኛ/ የተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎችን

2ኛ/ የማህበሩ ስራዎች እና ገቢ አሰባሰብ ንቁ ተሳታፊዎችን በተለይም

ሀ/ በየወሩ ገቢ አሰባሰብ ላይ እንዲሁም የተለያዩ በጎ ስራዎች ላይ የሚሳተፉ ወጣቶች

ለ/ ሀረሸይጣን ዙሪያ ያሉ የዲንጋይና የአሻዋ ማህበራት

ሐ/ የማህበሩ የጀርባ አጥንት የሆኑ ውጭ ሀገር የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች

መ/ አዲስ አበባ ላይ ያሉ በማህበሩ ገቢ አሰባሰብ ላይ ንቁ ተሳታፊ የሆኑ የአካባቢው ትላጆች

ረ/ የማህበሩ ወርሃዊ ገቢ አሰባሰብ ላይ ንቁ ተሳታፊ የሆነችው የወራቤ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት መምህርት አለዊያ ሀሰን

ሰ/ በሀሳብም በገንዘብም ከማህበሩ ጎን የማይጠፋው የማህበሩ አጋር ኡስታዝ መሀመድ ሀሰን ሽፋ/ አቡ ሷሊህ

3/ የቅበት ከተማ ስፖርትና ወጣቶች ፅ/ቤት

4/ የቅበት ከተማ አስተዳደር

5/ የቅበት ከተማ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት

እና ሌሎችም ስማችሁን ያልጠቀስኳችሁ ማህበሩ በሚሰራው በጎ ስራ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ስትሳተፉ የነበራቸፈሁ በአጠቃላይ በማህበሩ ስም እያመሰገንኩኝ ለወፊቱም ከማህበሩ ጎን እንዳትጠፉ የሚል አደራዬን አስተላልፋለሁ።

መሀመድ አብራር ላሎ
//የማህበሩ ሰብሳቢ//

// አቅመ ደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

ሀምሌ 13/2017

 #የማይቀርበት የአላህ ውዴታ የምናገኝበት ወሳኝ ቀጠሮአሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህበነገው እለት መስከረም 4/2017 ከጧቱ 2:00 ጀምሮ በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አጎዴ ቀበሌ ለሚገ...
13/09/2024

#የማይቀርበት የአላህ ውዴታ የምናገኝበት ወሳኝ ቀጠሮ
አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
በነገው እለት መስከረም 4/2017 ከጧቱ 2:00 ጀምሮ በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አጎዴ ቀበሌ ለሚገኘው አቅመ #ደካማ #አቶ #ተማም #ዑመር ቤት ለመገንባት ፕሮግራም ስለተያዘ ቅን ልቦና ያላችሁ ሁሉ በዚህ በተቀደሰ አላህ በሚወደው ታሪካዊ ፕሮግራም በፍፁም እንዳትቀሩ አደራ ጭምር እናስተላልፋለን።

ልብ ይበሉ: በዚህ ፕሮግራም የግድ ገንዘብ ይዘን መገኘት አይጠበቅብንም። ምናልባት ከገንዘብ በላይ ጉልበት እና የሙያ ድጋፍ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል።
ስለዚህ በጧቱ በመገኘት በዚህ አላህ የሚወደው ታሪካዊ ፕሮግራም እንድትገኙ ሲል ተመረሮት በጎ አድራጊት ማህበር ያሳስባል።

ነቢዩ(ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላል:—
“አላህ ባሪያውን ከመርዳት አይወገድም ባሩያው ወንድሙን እስከረዳ ድረስ“

//አቅመደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

🎤🎤🎤 ማስታወቂያ 🎤🎤🎤👉 ለተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር አባላት እና ደጋፊዎች በሙሉ                      🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝                  አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ...
25/07/2024

🎤🎤🎤 ማስታወቂያ 🎤🎤🎤
👉 ለተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር አባላት እና ደጋፊዎች በሙሉ
🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝
አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ!!
🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝
የተመረሮት በጎ አድራጎት በነገው እለት ሀምሌ 18/2016 የክረምት በጎ ፍቃድ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ ጉርጓድ ኩፋሮ ስለሚካሄድ ሁላችንም ሀረሸይጣን ሀይቅ ተገናኝተን መረሃግብሩን ተግባራዊ እናድርግ ሲል ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ጥሪውን ያስተላልፋል።

ቂያማ ነገ ቢሆን እንኳን እጁ ላይ ያለችውን ተክል ይትከላት!! (ነቢዩ ሙሀመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)
//ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር//

24/06/2024

የትመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት ፋርማሲ ግንባታ የ10 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገ

ሰኔ 17/2016 ቅበት ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን

በቅበት ከተማ አስተዳደር አጎዴ ቀበሌ የሚገኘው ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር በሕብረተሰቡ ተሳትፎ እየተገነባ ለሚገኘው የመድኃኒት ፋርማሲ ግንባታ የ10 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።

ማህበሩ የመድኃኒት ፋርማሲ ግንባታን በማቋቋም የመድኃኒት አቅርቦት እጥረቱን ለመቅረፍ እየተደረገ ያለውን ጥረት ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን አበርክቷል።

ማህበሩ ከተመሰረተ ጥቂት ጊዜ ቢሆንም በከተማ አስተዳደሩ በጾም፣በበዓላትና በሌሎች መደበኛ ጊዜያት ለአቅመ-ደካሞች ድጋፍ በማድረግ በርካታ የበጎነት ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የማህበሩ አስተባባሪ አቶ መሀመድ አብራር ገልፀዋል።

አስተባባሪው አቶ መሀመድ ማህበሩ በቀጣይም የበጎነት ስራዎችን በማጠናከር በከተማ አስተዳደር በልማትና የመደጋገፍ ስራዎች ላይ በስፈት በመሳተፍ አሻራውን ለማሳረፍ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር በትናንትው እለት (የውሙ ነህር ሰኔ 9/2016) ከኡስታዝ አቡ ሷሊህ(መሀመድ ሀሰን ሽፋ) ጋር በመተባበር ከግማሽ ሚልየን ብር በላይ የሚገመት ብር ወጪ በማድረ...
17/06/2024

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር በትናንትው እለት (የውሙ ነህር ሰኔ 9/2016) ከኡስታዝ አቡ ሷሊህ(መሀመድ ሀሰን ሽፋ) ጋር በመተባበር ከግማሽ ሚልየን ብር በላይ የሚገመት ብር ወጪ በማድረግ ለ150 (መቶ ሀምሳ) አቅመደካሞች ለዒደል አድሃ(አረፋ) በዓል ማክበሪያ የሚሆን ስጋ አከፋፈለ።

አሰላሙዐለይኩም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱህ

ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ለአቅመደካሞች በየአመቱ ለአጎዴ ቀበሌና አጎራባች ቀበሌ (ቅበት ከተማ 01 እና 02፣ ቦዜ ሳቦላ፣ ኮራሜ፣ መንደር 2፣ ገሬራ እና መስቃን) አቅመደካሞች የኢድ ማክበሪያ ስጋ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል። ዘንድሮም በ 2016 (1445 ዓ ሂጅራ) እንደተለመደው ከኡስታዝ መሀመድ ሀሰን ሽፋ (አቡ ሷሊህ) ጋር በመተባበር ለ150 አቅመደካሞች ማከፋፈል ተችሏል። ይህን ድጋፍ ለማድረግ ሶስት ሰንጋ፣ አንድ ላም እና 5 በጎችን በማረድ ነው የድጋፍ ስርዓቱ የተከናወነው። የተደረገው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከግማሽ ሚልየን ብር በላይ ሊሆን ይችላል።

ይህ ድጋፍ የተከናወነው የተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር አባላት እና የማህበሩ ደጋፊዎች ከሰበሰቡት ድጋፍ ነው። የማህበሩ አባላት በየወሩ ቋሚ መዋጮ የሚያደርጉ ሲሆን ማህበሩ ድጋፎችን የሚያደርገው ከዚህ መዋጮ ከተሰበሰበስ ገንዘብና ማህበሩን ከሚደግፉ ደጋግ ግለሰቦች ጋር በመተባበር ነው።

ከማህበሩ ደጋፊዎች መካከል ኡስታዝ መሀመድ ሀሰን ሽፋ(አቡ ሷሊህ)ይገኝበታል። ኡስታዝ መሀመድ ሀሰን ማህበሩ በሚያደርጋቸው ድጋፎች በአጠቃላይ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል።
የአረፋ በዓል ከመድረሱ 2 ቀን ቀድም ብሎም የኢድ ዋዜማን ምክንያት በማድረግ 1 ሰንጋ በማረድ ለ 60 (ስልሳ) አቅመደካሞች ድጋፍ አድርጓል። በዚሁ አጋጣሚ ኡስታዝ መሀመድ በማህበሩ እና በአባላቱ ስም ለማመስገን እንወዳለን። ጀዛከላሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊክ!!

የበጎ አድራጎት ማህበሩ ከዚህም ቀደም ብሎ ዘርፈ ብዙ የበጎና የልማት ተግባራት ላይ ሲሳተፍ ቆይቷል። ከዚህ በፊት ከተከናወኑ የበጎና የልማት ስራዎች መካከል መንገድ የማስተካከል፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር፣ በሴቶችና ህፃናት ላይ ፆታዊ ትንኮሳ እንዳይደርስ ሰላም የማስከበር፣ በረመዳን ማፍጠሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ በኢድ ማክበሪያ ለሌላቸው ድጋፍ፣ መታከሚያ ለሌላቸው የመታከሚያ ድጋፍ፣ ቤት ለሌላቸው ቤት መገንባት፣ ደብተርና እስክሪብቶ ማሟላት ለማችይችሉ ተማሪዎች ድጋፍ እና የመሳሰሉት ድጋፎች ከብዙ በጥቂቱ ለአብነት ያክል መጥቀስ ይቻላል።

ማህበሩ ለወደፊት ከዚህም በላይ ለመስራት ራዕይ ያለው ሲሆን መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ማህበሩ የለመው ዓላማና ራዕይ ያሳካ ዘንድ ከጎኑ ይሆኑ ዘንድ በዚሁ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን።

በዚሁ አጋጣሚ ለዚህ መሳካት ትብብር ያደረጋችሁ ሁሉ በተለይም የማህበሩ አባላት፣ ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያላችሁ የማህበሩ ደጋፊዎች በማህበሩና በአባላቱ ስም ለማመስገን እንወዳለን። አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁ!! ጀዛኩሙላሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊኩም !!!

የማህበሩ አባል ለመሆን የሚከተለውን ሊንክ ጆይን ያድርጉ
t.me/temerarot

// አቅመደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

30/05/2024

አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ

የተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር ቤተሰቦች ሁላችሁም በያለችሁበት እንዴት ናችሁ!?

ሰላማችሁ ብዝት ይበልልኝ

ዛሬ አንድ ነገር ማለት ፈለኩኝ ብዙዎቻችሁ በውስጣችሁ ለሚመላለሱ ጥያቄዎች መልስ ታገኙበታላችሁ ብዬ ተስፋ አሰርጋለሁ!

ወደ ጉዳዩ እናምራ

ከቅርብ ግዜ ወዲህ ተመረሮት ላይ ያለው እንቅስቃሴ በተለይም ገቢ/መዋጮ አሰባሰብ ላይ ቀዝቀዝ ብሏል። የዚህ ምክንያቱ ምንድነው ለሚለው አጠር ያለ ገለፃ ላድርግ።

እንደሚታወቀው ማሀበራችን አጎዴ ላይ ነው መቀመጫው። ይህ እንመሆኑ መጠን ወርሃዊ መዋጮ የሚያደርገውም በዋናነት እዛው ያለው አባል ነው።

ከቅርብ ግዜ ወዲህ ደግሞ አጎዴ ላይ የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ስለበዙ እና አባላቶቻችን ወርሃዊ መዋጮ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ ላይ አይደሉም የሚል ሀሳብ ስለነበረን ላልተወሰነ ግዜ ወርሃዊ መዋጮ ለማቆም ተገደናል።

ስከዚህ አባላቱ ጫናዎች እና ወጪዎች አሁን ቀንሰዋል የሚል እምነት ካላቸው አሁን ወር በገባ በመጀመሪያው እሁድ መዋጮ መሰብሰብ እንዲሁም ተቀዛቅዘው የነበሩ የተለያዩ የማህበሩን ስራዎች የምንቀጥል ይሆናል።

አላህ ይርዳን አላህ ያግዘን!!

ለምትሰጡን ገንቢ ሀሳብና አስተያየቶች ከልብ ነው የምናመሰግነው።

ጀዛኩሙላሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊኩም!!

አሚን አሚን አሚን አሚን!!!
//አቅመ ደካሞችን በጋራ እንታደግ//
ተመረሮት በጎ አድራጎት ማህበር

Address

Kibet

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተመረሮት የበጎ አድራጎት ማህበር Temererot Charity Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category