የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር -ሆከወማ'' Homecho town Administr youth Association.

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር -ሆከወማ'' Homecho town Administr youth Association.

የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር -ሆከወማ'' Homecho town Administr youth Association. Wel done

'' ሆመቾን በጋራ እናልማ ''!! ይላል በሶስት ሰው ጣምራ ፊርማ የሚንቀሳቀስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ስያሜው።የበለፀገ ሀሳብ ሀገርን ይገነባል።የምንኖራት ሀገር የምትለማውም የምትጎ...
21/12/2023

'' ሆመቾን በጋራ እናልማ ''!! ይላል በሶስት ሰው ጣምራ ፊርማ የሚንቀሳቀስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ስያሜው።
የበለፀገ ሀሳብ ሀገርን ይገነባል።የምንኖራት ሀገር የምትለማውም የምትጎሳቀለውም በኛ ሀሳብ ነው። የሚጠበቅን ልትለግስ ስትጀምር ከመልካም ሀሳብ ጀምር።ምክንያቱም ጥሩ ሀሳብ ከምትሰጠው ንዋይ እጅጉን ይበልጣል።

እናንተ ደጋግ የሀሳብ ባለቤቶች ሆይ ተባረኩ። ምክንያቱም ሆመቾን እንድታድግ ከኔ ይጀምር ማለታችሁን በተግባር አሳይታችሁዋልና።ከጥቂት ቀን በፊት የሆመቾን የውጭ ማብራት በውዛ ለማስገባት አካውንት ከፍተን እንመለሳለን ባልኩት መሠረት እነሆ በሶስት የአከባቢው ተወላጆች አማካይነት ተከፍቷል።

አካውንቱ በስማቸው ያስከፈትነው ባለ ራዕዮች ስራው ከኛ ይጀምር በሚል:-
1ኛ. እረሽ ሀዱሞ የሁለት በውዛ ዋጋ 5600 ብር ገቢ አድርጓል።
2ኛ. ታገሰ ጋታ የሁለት በውዛ ዋጋ 5600 ብር ገቢ አድርጓል።
3ኛ. መስፍን ላጲሶ የአንድ በውዛ ዋጋ 2800 ብር ገቢ አድርጓል።
4ኛ. ደምበሎ ቢካጎ የአንድ በውዛ ዋጋ 2800 ብር ገቢ አድርጓል።
5ኛ. ጌታብቻ ደጀኔ የአንድ በውዛ ዋጋ 2800 ብር ገቢ አድርጓል።
6ኛ. ሰለሞን ታምሬ የአንድ በውዛ ዋጋ 2800 ብር ገቢ አድርጓል።

ይህ ገቢ በሺዎች በሚቆጠሩ በአከባቢያችን ቀና አሳቢዎች ይቀጥለል።ካለኛ ለኛ አከባቢ የሚያስብ የለምና በዚህ መልካም ተግባር ለመሳተፍ ለጠየቃችሁን አካውንት ቁጥሩን ከዚህ በታች መለጠፋችንን እያሳወቅን ላላችሁ ቀና ሀሳብ ከወዲሁ ልናመሰግናችሁ እንወዳል።

ደቡብ አፍሪካ ያላችሁ ውድ ወንድሞቻችን ለከተማችሁ ለከተማችን ያላችሁን ተቆርቃሪነት እያመሠገንን ከዚህ በፊት በተነጋገርነው መሠረት ተሳትፎዋችሁን እንድትጀምሩ እየነገርናችሁ ያደረጋችሁን አስተዋጽኦ ህዝቡ እንዲያመሰግናችሁ በዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ ስማችሁን ከመለጠፍም በላይ ሙሉ መረጃችሁን ወስደን በአከባቢያችን ባሉ ልማት ናፋቂ ሽማግሌዎች እንደምናስመርቃችሁ ለማሳወቅ እንወዳለን።

ሀገር ውስጥ ያላችሁ ወንድም እህቶቼ ከዚህ በፊት ለሠጣችሁ ልባዊ ሀሳብ ከልብ ለማመስገን እንወዳለን። ሆመቾን ለማልማት ያላችሁን ሀሳብ አምጡ።ምክንያቱም የእድገት ቁንጮ ሀሳብ ነው።ያለኛለዚህች ከተማ የሚንቀሳቀስ የለም እያልኩ በአካውንቱ በልባችሁ የመጣውን ማስገባት እንደምትችሉ እየገለጽን ያስገባችሁትን የባንክ አስሊፕ ወይም በሞባይል ባንክንግ ከሆነ ስክሪን ሹት በማድረግ በውስጥ መስመር እንድትልኩልን እናሳስባለን።

ሆመቾን በቅርብ ጊዜያት እንደምናለማት አልጠራጠርም።
==== ተባረኩ ====

21/09/2022

ሆመቾ!!

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በከተማ ውበትና ፀጥታ ዘርፍ የተሠማሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች በፎቶ‼️
04/08/2022

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በከተማ ውበትና ፀጥታ ዘርፍ የተሠማሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች በፎቶ‼️

👉ሆመቾ ከተማ አስተዳደር ደምቃለች‼️
30/07/2022

👉ሆመቾ ከተማ አስተዳደር ደምቃለች‼️

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።****** ሐምሌ 22,2014 ዓ/ም****               👉ሆመቾበሆመቾ ከተማ አስተዳደር በበጎ ፈቃድ አገልግ...
29/07/2022

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
****** ሐምሌ 22,2014 ዓ/ም****
👉ሆመቾ
በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተደራጁ ወጣቶች ስራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።በጎ መስራት ለራስ ነው በሚል እሳቤ ዛሬም ቢሆን ወጣቶቹ በበጎ ስራ ተሰማርተዋል።

''ለኛ ከተማ እኛ ለኛ ማህረሰብም እኛ'' የሚለውን መሪ ቃል ያነገቡት ወጣቶች በዛሬ ቀን በከተማ ውበት ላይ አመርኪ ውጤት አስመዝግበዋል።በዛሬ ስምሪት አዳባባይ ዙርያን የማጽዳት፣በአደባባዩ ወስጥ ሳር መትከል፣በአዳባባዩ ዙርያ የሀዲያን የባህል ቀለም መቀባትና በአደባባዩ ውስጥ የአበባ ተከላን የማከናወን ስራ ሰርተዋል።

በወጣቶች እንቅስቃሴና ስራ የረኩ የከተማው ነዋሪዎች ከስራ መልስ በርቱ ከጎናችሁ ነን በማለት በቡና ሴርሞኒ ላይ ተካፍለዋል።

የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ አጥናፉ በቀለና የማዛገጃ ኃላፊ አቶ ሰላሙ ሴሜ የወጣቶችን ስራ በመጎብኘት አበረታተዋል።በጉብኝታቸውም ለስራ ግብአት የሚሆኑትን ቁሳቁሶች በማሟላት ከወጣቱ ጎን እንደሚቆሙ ቃል ገብተዋል።

በግቤ ወረዳና በሆመቾ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፤ባለሙያዎችና በአከባቢው ማህበረሰብ ቅንጅታዊ የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር ተካሄደ።***** ሐምሌ 21,2014 ዓ/ም *****          ...
28/07/2022

በግቤ ወረዳና በሆመቾ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፤ባለሙያዎችና በአከባቢው ማህበረሰብ ቅንጅታዊ የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር ተካሄደ።
***** ሐምሌ 21,2014 ዓ/ም *****
👉ሆመቾ
በሀገር አቀፍ እየተከናወነ ያለውን የአረንጎዴ አሻራ መረሃ ግብር እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል።

ዛሬ በሀዲያ ዞን በግቤ ወረዳና በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የተቀናጀ የችግኝ ተከላ ተካሄዷል።በችግኝ ተከላ የዞን፤የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።

የችግኝ ተከላውን በከተማ ውስጥ ለችግኝ ተብሎ በተመረጡ ቦታዎች የተተከለ ሲሆን ይህም እንደ ሀገር የተያዘውን እቅድ ግብ የማድረስ እላማነን ይመታል ተብሎ ይጠበቃል።

በችግኝ ተከላ ጎን ለጎን አመራሮች፤ለችግኝ ተከላ የታደሙ ባለሙያዎችና የአከባቢው ነዋሪዎች በግቤ ወረዳ እየተከናወነ ያለውን የቴክኒክና ሙያ ተቋም ግንባታን የደረሰበትን ደረጃ ጎብኝተዋል።አመራሮቹ እነደገለጹት የግንባታው አፈጻጸም በጣም ጥሩና የሚበረታታ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ከችግኝ ተከላ መልስ የወረዳው አስተዳደር አቶ አዲነው ባፋ ዛሬ ሀገራችን በፈተና ውስጥ እያለች ድል ቀንቷታል ሲሉ በ18ኛ በአለም ሻምፒዮና ጀግኖች አትሌቶቻችን ለኢትዮጵያ ያመጡትን ድል''ወሳኝ ድል ነው'' ሲሉ ገልጸዋል።

የተመዘገበልንን ድል ታሳቢ በማድረግ ሁላችንም ኢትዮጵያዊነትን እያስታወስን በጀግንነት በኩራትና በነጻነት እንቀጥላለን የሚል ጽኑ አቋም ላይ በመሆን ታዳሚዎችም በኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር የዛሬውን የችግኝ ተከላ አቋጨተዋል።

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የሴቶች ሊግና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች  ዛሬ በሆመቾ ከተማ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።👉ሀምሌ 19,2014 ዓ/ም******* ሆመቾ ******ዛሬ በሆመቾ ከተማ...
26/07/2022

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የሴቶች ሊግና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ዛሬ በሆመቾ ከተማ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
👉ሀምሌ 19,2014 ዓ/ም
******* ሆመቾ ******
ዛሬ በሆመቾ ከተማ አስተዳደር የሴቶች ሊግና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች አረንጓ አሻራቸውን አኑረዋል።በችግኝ ተከላው ከሁለቱም ቀበሌ የተወጣቱ ሴቶች ተሳትፈዋል።

በችግኝ ተከላው የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አብዮት አዲሴ ሴቶች በሀገር ልማት ላይ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልፀው ችግኝ መትከ፤ የተተከለውን ተንከባክቦ ማሳደግ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ፤በአፈርና አከባቢ ጥበቃ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል።

የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ሊግ ወ/ሮ ሽታ አለሙ በብልጽግና ዘመን ሴቶች የራሳቸውን የስራ ሚና ሊጫወቱ ሜዳው ክፍት እንደሆነና በየትኛውም ተልዕኮ አመርኪ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚችሉ ገልጸዋል።ወ/ሮ ሽታ እንደገለጹት ዛሬ የምናኖረው አረንጓዴ አሻራ ነገ ለልጅ ልጆቻችን የሚሆን ጥቅም አለው ሲሉ ለታዳሚዎች አብራርተዋል።

በዕለቱ ከሁለቱም ቀበሌያት( ከሰሜንና ከደቡብ) ቀበሌ የተወጣጡ ሴቶች አሻራቸውን ለማኖር አዚህ በመገኘታቸው ተደስተው የተተከለው ችግኝ እስከሚፀድቅ ድረስ ለመንከባከብ ኃላፊነት ለመውስድ ቃል ገብተዋል።

26/07/2022
በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ከተማውን የማስዋብ ስራ ዛሬ አከናውነዋል።👉ሀምሌ 18,2014 ዓ/ም****** ሆመቾ ******የሆመቾ ከተ...
25/07/2022

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ከተማውን የማስዋብ ስራ ዛሬ አከናውነዋል።
👉ሀምሌ 18,2014 ዓ/ም
****** ሆመቾ ******
የሆመቾ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት በጎ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ዛሬ ከተማውን የማስዋብ ስራ ሰርተዋል።ወጣቶቹ በተደራጀ አንድነትና ትብብር ለልማት ያላቸውን ቁርጠኝነት በከተማው አደባባዩን በማስዋብ ጀምረዋል።ተሳታፊዎቹ እንደገለፁት ''ለኛ ከተማ እኛ'' ለኛ ህብረተሰብም እኛ'' በሚል ቁረጠኝነት ተግባሩን በክረምት ወራት ብቻ ሳይሆን የዘውትር ተግባራቸው እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።በቀጣይ ቀናትም ተማሪዎችን የማስተማር፤ ለአረጋዊያና አቅመ ደካሞች ቤት የማደስ ስራና በመሳሰሉት ተግባር እንደሚሰማሩ ገልፀዋል።በጎነት ለራስ እንደሆነ ተገንዝበው መስራት ማስተዋል ነውና ሌሎች ወጣቶችም በዚህ ተግባር ሊሳተፉ ይገባል።የከተማው ህብረተሰቡም በራፉ ላይ ያለውን ቆሻሻ ሰብስቦ በማቃጠልና በማጽዳት ከጎናችን እንዲሆን ሲሉ ጠይቀዋል።

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በወጣቶች የክረምት ወራት በጎ አድራጎት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።ሀምሌ 15,2014 ዓ/ም      ***** ሆመቾ ****በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት በሚሰሩ ...
22/07/2022

በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በወጣቶች የክረምት ወራት በጎ አድራጎት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
ሀምሌ 15,2014 ዓ/ም
***** ሆመቾ ****
በሆመቾ ከተማ አስተዳደር በክረምት ወራት በሚሰሩ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ዛሬ የችግኝ ተከላ አካሄደዋል።በችግኝ ተከላው የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አጥናፉ በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት የተሰማሩ ወጣቶች ችግኙን ከመትከል ባለፈ እስከሚፀድቅ ድረስ ኃላፊነት እንደተጣለበቸው ገልፀዋል። በዚህ በያዝነው ዓመት በከተማ አስተዳደር ሊተከል የታቀደው ችግኝ 18ሺ ሲሆን ዛሬ እንደ መክፈቻ በከተማ ውስጥ መተከሉን ገልፀው ከወጣቱ ጋር አብረው አሻራቸውን አኑረዋል።በመቀጠልም የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዮት አዲሴ ወጣቶች አተማን ከማስዋብ ባለፈ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልፀዋል።ከንቲባው አቶ አብዮት አዲሴ ዛሬ በከተማ ውስጥ የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው አገልግሎት እስከሚሰጡ ድረስ ወጣቱም ማህበረሰቡም ኃላፊነት ሊወስድ ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።በቀጣይ ክረምት ወራት ወጣቶች ማህበረሰቡን ለማገልገልና ከተማውን ውብና ጽዱ ለማድረግ በሙሉ ተነሳሽነት እንደሚያገለግሉ በዕለቱ የተገኙት ወጣቶች ገልጸዋል።

Address

Homecho
Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር -ሆከወማ'' Homecho town Administr youth Association. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category