Melaku Kebede መላኩ ከበደ Lawyer/የህግ ባለሙያ

Melaku Kebede መላኩ ከበደ Lawyer/የህግ ባለሙያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Melaku Kebede መላኩ ከበደ Lawyer/የህግ ባለሙያ, Lawyer & Law Firm, Hawassa.

💡 ህግን ይወቁ፣ መብትዎን ያስከብሩ!

ስለ ኢትዮጵያ ህጎች ጥልቅ ግንዛቤ የሚያገኙበት፣ ሙያዊ ሃሳቦችንና ሰነዶችን በነፃ የሚያገኙበት ልዩ መድረክ።
🔗 ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/share/1B2utzQBiT/
ያግኙን፦ https://t.me/lawyermelaku/16

📌 ያለበቂ ምክንያት ከሥራ ተሰናብተዋል? መብትዎ በሕግ የተጠበቀ ነው! ⚖️በኢትዮጵያ የአሰሪና ሠራተኛ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሠረት፣ ያለ አግባብ ከሥራ ለተሰናበተ ሠራተኛ ሕጉ የ...
09/05/2026

📌 ያለበቂ ምክንያት ከሥራ ተሰናብተዋል? መብትዎ በሕግ የተጠበቀ ነው! ⚖️
በኢትዮጵያ የአሰሪና ሠራተኛ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሠረት፣ ያለ አግባብ ከሥራ ለተሰናበተ ሠራተኛ ሕጉ የሚከተሉትን መፍትሔዎች አስቀምጧል።

የእነዚህን ክፍያዎች ዝርዝር ሁኔታ እና አሰላል፣ የሕግ ቅደም ተከተሎችን እና መብትዎን ለማስከበር መውሰድ ያለብዎትን እርምጃዎች በዝርዝር በቴሌግራም ቻናላችን ላይ አዘጋጅተናል።

👇 ሙሉ መረጃውን ለማግኘትና ነፃ የሕግ ሰነዶችን ለማውረድ ሊንኩን ይጫኑ፦

📩 ቴሌግራም፦ https://t.me/lawyermelaku/16

ሕግን ይወቁ፣ መብትዎን ያስከብሩ!
የሕግ ባለሙያ መላኩ ከበደ

#ቴሌግራም

⚖️ የውርስ ንብረትን ማጣራትና ማስተዳደር፦ ማወቅ የሚገቡን ቁልፍ ነጥቦች!ሰው ሲሞት ንብረቱ ወዲያውኑ ለወራሾች አይከፋፈልም። የሟች ንብረት "አንድ የተለየ ንብረት" (Distinct Estat...
06/05/2026

⚖️ የውርስ ንብረትን ማጣራትና ማስተዳደር፦ ማወቅ የሚገቡን ቁልፍ ነጥቦች!
ሰው ሲሞት ንብረቱ ወዲያውኑ ለወራሾች አይከፋፈልም። የሟች ንብረት "አንድ የተለየ ንብረት" (Distinct Estate) ሆኖ ተለይቶ መያዝ እና በአግባቡ መጣራት አለበት። የዛሬው አጭር ጽሑፋችን ስለ ውርስ ማጣራት ሂደትና ስለ ውርስ አጣሪዎች መብትና ግዴታ ግንዛቤ ያስጨብጣል።
🔍 ተጨማሪ የሕግ መረጃዎችንና ሙያዊ ምክሮችን ለማግኘት ገጻችንን Like እና Follow ያድርጉ!

💡 ሕግን ይወቁ፣ መብትዎን ያስከብሩ!
ስለ ኢትዮጵያ ሕጎች ጥልቅ ግንዛቤ የሚያገኙበት፣ ሙያዊ ሃሳቦችንና ሰነዶችን በነፃ የሚያገኙበት ልዩ መድረክ።
ተጨማሪውን 📩 ያግኙን (ቴሌግራም)፦ https://t.me/lawyermelaku/16

#ውርስ #ኢትዮጵያ

"የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር እና ያለ ማስጠንቀቂያ ማስወጣት አሳስቦዎታል? አዲሱ ሕግ ምን ይላል? ስለ ቤት ኪራይ ውል ማወቅ ያለብዎትን 10 ወሳኝ ነጥቦች በቴሌግራም ገጻችን በዝርዝር አስፍረና...
05/05/2026

"የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር እና ያለ ማስጠንቀቂያ ማስወጣት አሳስቦዎታል? አዲሱ ሕግ ምን ይላል? ስለ ቤት ኪራይ ውል ማወቅ ያለብዎትን 10 ወሳኝ ነጥቦች በቴሌግራም ገጻችን በዝርዝር አስፍረናል፦
👉👉👉 🔗 https://t.me/lawyermelaku"

05/05/2026

የህግ ባለሙያ መላኩ ከበደ:
የተለያዩ ህግ-ነክ መረጃዎች ቶሎ ቶሎ እንዲደርስዎ ፔጁን Like & Share ያድርጉ!
በተጨማሪም የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀላሉ!
#መላኩከበደ #የህግ #ባለሙያ

https://t.me/lawyermelaku

🚨 ፖሊስ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰውን መያዝ የሚችለው መቼ ነው? ⚖️

ብዙዎቻችን ፖሊስ ሰውን ለመያዝ የግድ የፍርድ ቤት መጥሪያ ወይም ትዕዛዝ ያስፈልገዋል ብለን እናስባለን። ነገር ግን ሕጉ ፖሊስ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ (Warrant) በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ የሚፈቅድባቸው ልዩ ሁኔታዎች አሉ።

እነዚህን 12 ነጥቦች ይወቋቸው፦

1️⃣ እጅ ከፍንጅ ሲያዝ፦ ወንጀል ሲፈጸም ፖሊስ በዓይኑ ካየ ወይም ወንጀሉ እንደተፈጸመ በሕዝብ ጩኸትና በፖሊስ ክትትል ከተደረሰበት።

2️⃣ ከባድ ወንጀል ጥርጣሬ፦ ግለሰቡ ከባድ ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ በበቂ ሁኔታ ሲጠረጠር።

3️⃣ አድራሻ የሌለው ተጠርጣሪ፦ ፖሊስ የግለሰቡን ማንነት ማረጋገጥ ካልቻለ እና ቋሚ መኖሪያ የሌለው ሲሆን።

4️⃣ ከእስር ያመለጠ ሰው፦ ቀደም ሲል ተፈርዶበት ወይም በቁጥጥር ሥር እያለ አምልጦ የነበረን ሰው ለመያዝ።

5️⃣ የተከለከሉ ቁሶች፦ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ፣ ፈንጂ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ይዞ የተገኘ ሰው።

6️⃣ የወንጀል ውጤት፦ የተሰረቀ ንብረት ወይም ሌላ ከወንጀል የተገኘ ውጤት ይዞ ሲገኝ።

7️⃣ የሌሊት ወንጀል ጥርጣሬ፦ በምሽት ወንጀል (ለምሳሌ፡- ሰብሮ መግባት) ፈጽሟል ተብሎ በበቂ ሁኔታ ሲጠረጠር።

8️⃣ የሕዝብ ደህንነት፦ ሰውየው በሌሎች ላይ ወይም በራሱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል ተብሎ ሲታመን።

9️⃣ የዋስትና ውል መጣስ፦ በዋስ የተለቀቀ ሰው ግዴታውን ካልተወጣ።

🔟 ትዕዛዝ መኖሩ ሲታወቅ፦ ፍርድ ቤት የእስር ትዕዛዝ እንዳወጣበት በይፋ (በጋዜጣ ወይም በፖሊስ መረጃ) ሲታወቅ።

11️⃣ ማንነትን መደበቅ፦ ተጠርጣሪው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ለማሳየት ፈቃደኛ ካልሆነ።

12️⃣ የፖሊስን ሥራ ማደናቀፍ፦ ፖሊስ ግዴታውን እየተወጣ ባለበት ወቅት ተቃውሞ ሲገጥመው።

📌 ማወቅ ያለብዎት መሠረታዊ መብቶች፦

ፖሊስ ከላይ በተጠቀሱት ሁኔታዎች ሰውን በቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላ የሚከተሉትን ማክበር አለበት፦

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ሥር በዋለ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት።

የተያዘው ግለሰብ ለምን እንደተያዘ ወዲያውኑ የማወቅ መብት አለው።

👉https://t.me/lawyermelaku/16
"ሕግን ማወቅ ራስን ከበደል መከላከል ነው!"

https://t.me/lawyermelaku
23/02/2025

https://t.me/lawyermelaku

Get Free Legal views, documents, enactments, informations, updates, news, and ideas of Laws. Stay tuned by like our page and subscribing to our Telegram channel. Contact us for any Ethiopian Law related views.

የውንብድና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነትመግቢያወንጀል የአንድን አገር መንግስት፣ ህዝብ እና ነዋሪዎች ሰላምና ደህንነት የሚያናጋ ድርጊት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ወንጀል በግለሰብም ሆነ በ...
07/02/2025

የውንብድና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት

መግቢያ

ወንጀል የአንድን አገር መንግስት፣ ህዝብ እና ነዋሪዎች ሰላምና ደህንነት የሚያናጋ ድርጊት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ወንጀል በግለሰብም ሆነ በማህበረሰብ ውስጥ ያለውን መልካም መስተጋብር፣ የመስራት፣ የማሳደግ፣ የመነገድ ንብረት የማፍራት እንደልብ የመንቀሳቀስ ፍላጎት የሚገድብና ስጋት ያለበት ግለሰብ ወይም ህብረተሰብ የመፍጠር አቅሙ ከፍ ያለ ነው፡፡ በመሆኑም የወንጀል ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎችን ለመቅጣትና ህብረተሰቡ ሌላ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ለመጠበቅ የወንጀል ህግ አስፈላጊ ሲሆን በሀገራችንም የሀገሪቱን መንግስት፣ ህዝቦችና ነዋሪዎቹን ሰላምና ደህንነት፣ ሥርዓት፣ መብትና ጥቅምን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ እንዲሁም ወንጀል እንዳይፈጸም ለመከላከል በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠትና ማስጠንቀቂያነቱም በቂ ባልሆነ ጊዜ ወንጀል አድራጊዎቹ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡና ለሌሎች ማስተማሪያ እንዲሆን በሚል ዓላማና ግብ በ1996 አ.ም የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ የወጣና በዚህ የወንጀል ህግ የመንግስት፣ የህዝብና የግል ንብረት ጥበቃ የሚደረግለት ሲሆን የሌላን ሰው የንብረትና የኢኮኖሚ መብት ወይም በገንዘብ ሊተመኑ በሚችሉ መብቶች ላይ የሚደረግ ጣልቃ ገብነት በወንጀል ህጋችን የሚያስቀጣ ነው፡፡ በንብርት ላይ ከሚፈጸሙ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ የውንብድና ወንጀል ሲሆን በጦር መሳሪያ ታግዞ የሚፈጸም ውንብድና ወንጀልና ቅጣቱን በዚህ ጽሁፍ እንመለከታለን፡፡
የውንብድና ወንጀል (Robbery)
ወንበዴ የሚለው ቃል ለማህበረሰባችን አዲስ አይደለም ይልቁንም ጉልበተኛ፣ ሽፍታ እና ቀማኛ በሚል ስያሜ ሲጠቀምበት ኖሯል፡፡ የውንብድና ተግባር ማለት ህግን በመቃረን የአንድን ሰው ንብረት ሀይል በመጠቀም ወይም በማስፈራት፣ በማንገላታት የራስ ያልሆነ ዕቃን መውሰድ ማለት ነው፡፡ የውንብድና ወንጀል በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች መካከል አንዱ ሲሆን የወንጀሉ ምንነት በወንጀል ህጋችን አንቀጽ 670 ስር እንደተቀመጠው ማንኛውም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት አስቦ የሌላ ሰው የሆነውን ተንቀሳቃሽ እቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ የገጠመውን ተቃውሞ ውጤታማነት ለማስቀረት ሲል በሌላ ሰው ላይ የሀይል ድርጊት ወይም ከባድ የሆነ የማንገላታት ተግባር ወይም ከባድ ዛቻ የፈፀመ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ይህን ሰው መከላከል እንዳይችል ያደረገና ንብረቱንም ከተበዳይ ላይ የወሰደ እንደሆነ የውንብድና ወንጀል ፈጽሟል ይባላል፡፡
የውንብድና ወንጀል ባህሪው
o ድርጊቱ የሚፈጸመው የሀይል ድርጊት የቀላቀለ ነው፡፡ የሌላ ሰው የሆነን ተንቀሳቃሽ ንብረት ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ ለመከላከል በሚሞክር ሰው ላይ የሀይል ድርጊት (ድብደባ ወይም ማነቅ) ፣ ማንገላታት ወይም ከባድ ዛቻ (እንደሚገለው፣እንደሚመታው በመግለጽ) መኖር አለበት
o ወንጀል አድራጊው የራሱ ያልሆነን ተንቀሳቃሽ ንብረት ለመውሰድ በማሰብ ድርጊቱን ሲፈጽም
o የውንብድና ተግባር የተፈጸመበት ንብረት የሌላ ሰው መሆን አለበት
o ንብረቱ ከባለቤቱ እጅ የወሰደ መሆን አለበት
o ንብረቱን ከባለቤቱ ለመውሰድ የሀይል ተግባር የተጠቀመ መሆን አለበት፡፡
ከባድ ውንብድና (Armed/ Aggravated Robbery)
ማንኛውም ሰው የሌላ ሰው የሆነውን ተንቀሳቃሽ እቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ የገጠመውን ተቃውሞ ውጤታማነት ለማስቀረት ሲል በሌላ ሰው ላይ ከሚፈጽመው የሀይል ድርጊት ፣ ከባድ የሆነ የማንገላታት ተግባር ፣ከባድ ዛቻ የፈፀመ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ይህን ሰው መከላከል እንዳይችል ከማስፈራራት እና ከማንገላታት አልፎ በሚከላከለው ሰው ላይ የአካል ጉዳት ባስ ሲልም ሞት በሚያስከትል መልኩ በልዩ ልዩ ጉዳት አድራሽ መሳሪያ በመታገዝ የውንብድናው ወንጀል ሊፈጸም ይችላል፡፡ ይህ አይነቱ ጉዳት መከሰትም የወንጀሉን አፈፃፀም የሚያከብድና ቅጣቱንም ከፍ የሚያደርግ ሲሆን ህጉም ይህንን ድርጊት ከባድ ውንብድና በሚል ስያሜ ሰጥቶታል፡፡
ከባድ የሚያሰኙ የአፈፃፀም ሁኔታዎች እና የወንጀል ተጠያቂነት
የውንብድና ወንጀል የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን እስራት ቅጣትን የሚያስከትል ሲሆን ቅጣቱም 15 አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ነው፡፡
በወንጀል ህጋችን በአንቀፅ 671 ስር በዝርዝር እንደተቀመጠው አንድ ውንብድና ከባድ ነው ከሚያስብሉት ሁኔታዎች ውስጥ የወንጀሉ አፈጻጸም ሲሆን ንብረቱን የሰረቀው ሰው በተለየ መልኩ አደገኛነቱን በሚያሳይ ማለትም በጦርመሳሪያ፣ በቡድን ሲፈጸም ሲሆን በወንጀል ህጋችን በውንብድና እና በከባድ ውንብድና መካከል ልዩነት የፈጠረው ወንጀሉ አፈጻጸም መሰረት ያደረገ እንደሆነ ከድንጋጌው ማየት ይቻላል በአንቀፅ 671(1) መሰረት ወንጀል ፈፃሚው፡-
• ወንጀሉን የፈፀመው በሰዎች ወይም በንብረት ላይ የሀይል ድርጊት ለመፈፀም በተቋቋመ የወንበዴ ቡድን አባል በመሆን ከሆነ፣
• ተበዳዩን እገድልሀለሁ ብሎ እርግጠኛ የሞት አደጋ እንደሚያደርስበት በመቃጣት ከሆነ
• በጦር መሳሪያ ወይም በተለይ አደገኛ በሆነ ሌላ አይነት መሳሪያ በማስፈራራት ወይም ስቃይ በሚያደርስ ሁኔታ በማንገላታት ወይም ከባድ የአካል ጉዳት በማድረስ ከሆነ
• በተለይ አደገኛነቱን በሚያሳይ በማናቸውም ሌላ ሁኔታ ከሆነ ቅጣቱ ከ5 እስከ 25 አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚያስቀጣ የተቀመጠ ሲሆን ወንጀሉን በስለት፣ በጩቤ፣ በጦር መሳሪያ ሌሎች በሰው አካል ላይ ጉዳት ለማድረስ በሚችል መሳሪያ ተፈጽሞ ቢገኘ ተከሳሹ በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ ሊቀርብበት ይችላል ማለት ነው፡፡ በአንቀፅ 671(2) ሥር የተገለፀው ደግሞ እስካሁን ከተገለፁት በከበደ ሁኔታ የተፈፀመ ድርጊትን የሚያሳይና ከፍተኛ ቅጣትም የሚያስቀጣው ወንጀሉ የተፈጸመው ከሚከተሉት ዘዴዎች በአንዱ የሆነ እንደሆነ ነው።
• ወንጀል ፈፃሚው ወንጀሉን የፈፀመው ከተደራጀ ቡድን ጋር በመሆን
• የጦር መሳሪያ ወይም ሌላ አደገኛ መሳሪያ በመያዝ፣
• የህዝብ ፀጥታን አደጋ ላይ የሚጥል ወይም የተለየ ጨካኝነትን የሚያሳይ ዘዴን የተጠቀመ ወይም
• የተፈፀመው የሀይል ድርጊት ዘላቂ የአካል ጉዳት ወይም ሞትን ያስከተለ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን የእድሜ ልክ እስራት ወይም ደግሞ ነገሩ እጅግ ከባድ በሆነ ጊዜ የሞት ቅጣት እንደሚወስን ተቀምጧል፡፡
ማጠቃለያ
በአጠቃላይ የውንብድና ወንጀል በተለይም ከባድ ውንብድና ለህብረተሰቡም ስጋት የሚፈጥር ድርጊቱም ከፍተኛ ቅጣት ሊያስከትል የሚችል ወንጀል ከመሆኑ አንፃር በወንጀል ፈፃሚዎቹ እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የሥነልቦና ጉዳት ጭምር የሚያስከትል ነው፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡ ይህንን ተረድቶ ወንጀሉን በመከላከልም ሆነ ተፈፅሞ ሲገኝም ለፍትህ አካላት ተባባሪ በመሆን የበኩሉን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡
Via:- misistry of justice

Get Free Legal views, documents, enactments, informations, updates, news, and ideas of Laws. Stay tuned by like our page and subscribing to our Telegram channel. Contact us for any Ethiopian Law related views.

22/09/2024
18/09/2024
አዲሱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት Central Ethiopia Regional  State ገፅ/Page ላይክ በማድረግ በገጹ የሚለቀቁ የተለያዩ የፍ/ቤቱን መረጃዎች ...
16/09/2024

አዲሱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት Central Ethiopia Regional State ገፅ/Page ላይክ በማድረግ በገጹ የሚለቀቁ የተለያዩ የፍ/ቤቱን መረጃዎች በቀላሉ ያግኙ

Address

Hawassa

Telephone

+251984130352

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Melaku Kebede መላኩ ከበደ Lawyer/የህግ ባለሙያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Melaku Kebede መላኩ ከበደ Lawyer/የህግ ባለሙያ:

Share