26/11/2025
ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ፍትሐ ብሔር
ምድብ ችሎት ባለጉዳዮች በሙሉ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡-የይግባኝ አላላክን ማኑዋልን መነሳቱን ይመለከታል
ከዚህ ቀደም በፍታብሔር ይግባኝ አስራር ባለጉዳዩ ለእኛ ፍ/ቤት መዝገብ ይምጣልኝ ማመልከቻ አቅርቦ መዝገብ ይምጣ እየተባለ ሲመራ መቆየቱ ይታወሳል ፡፡ይሁን እንጂ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በቁጥር ጠ/1-29/4655 በቀን 22/12/2017ዓ/ም በተፃፈ ደብዳቤ ይህ አሰራር ለባለጉዳይ ምልልስ ምክንያት መሆኑን ግንዛቤ ተወስዶ አሰራሩ እንዲቀርና በስነ ስርአት ሕጉ 327 መሰረት እንዲከናወን ባሳወቁን መሰረት የይግባኝ አመጣጡ ስርአቱ ቀሪ መሆኑን አዉቃችሁ ከጳጉሜ 03/13/2017 ዓ/ም ጀምሮ ይግባኝ ማለት የፈለገ ባለጉዳይመዝገቡ ይምጣልኝ ብሎ ለእኛ ማመልከት ሳያስፈልገዉ ዉሳኔዉን ለሰጠዉ _ ለስር ፍ/ቤት መጠየቂያዉን አቅርቦ ግልባጩን በሚያመጣዉ መሰረት የይግባኝ መዝገቡ የሚከፈት መሆኑን አሳዉቃለሁ ፡፡
ከሰላምታ ጋር🙏👍✍️