የገደብ ከተማ ኮሙኒኬሽን

የገደብ ከተማ ኮሙኒኬሽን Communication service

የገደብ ከተማ አስተዳደር እስካሁን የተሰራውን የመንግስትና ፓርቲ ሥራዎች በመገምገም በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያየ ‎‎( #ሴነ 16/2018 ዓ.ም ) የገደብ ከተማ መንግስት ኮሙንከሽ...
23/06/2026

የገደብ ከተማ አስተዳደር እስካሁን የተሰራውን የመንግስትና ፓርቲ ሥራዎች በመገምገም በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያየ

‎( #ሴነ 16/2018 ዓ.ም ) የገደብ ከተማ መንግስት ኮሙንከሽን

በጌዴኦ ዞን የገደብ ከተማ አስተዳደር እስካሁን የተሰራውን የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች በመገምገም በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል ።

የገደብ ከተማ ም/ከንቲባ እና ሰላምና ጸጥታ፣ፍትህ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ከተማ ሞገስ በከተማ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ አጠቃላይ ተግባራቶች የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በማጠናከርና በማበረታታት በከተማችን ውስጥ እየተሰራ ያለውን የከተማ ኮልደር ስራዎችን ከከተማ ሕዝብ ጋር በጋራ በመሆን በጥሩ ሁነታ እንድሰራ ተሳትፎ ላደረጉ በሙሉ ምስጋናቸውን ገልጸው በቀሩት ቀናቶች ውስጥ የተቀሩትን ተግባር በጋራ ማከናወን እንዳለበት ገልጸዋል።

የገደብ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ የሆኑት አቶ ካሳሁን በርሶ በጥንካሬ የታዩ ጉዳዮችን እንደ መልካም ተግባር በመጠቀም ማነኛውንም የገቢ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀምና በመሰብሰብ አሁን እንደ ከተማችን እየታየ ያለውን የከተማችን ለውጦች በማስቀጠል ቅንጅታችን በማጠናከርና፣ የሰላምና የገቢ ስራዎችን እንዲሁም ውጠታማነትን መሠረት ያደረገውን የፍጠራ ስራዎችን ከበፊቱ በተጠናከረ መልኩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በመጨረሻም በቀጣይ በቀሩ ቀናት ውስጥ የፓርቲዉና መንግስታዊ ስራዎች በየደረጃው የሚገኙ አደረጃጀቶችን በማጠናከር በተቀላጠፈ መልኩ ለመምራት ሁሉም አመራሮች ከፍተኛ ሚና መወጣት እንዳለበትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በትኩረት መስራት እንዳለበት ተነስተዋል ።

ዘገባው የገደብ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነው ።

Gargarit hedheeke araddinke qortumi'a hiisichchoke kaddaxxi 10 wogga'a turtaaxxi plane mari'etike mini'a shiqqe murteese...
22/06/2026

Gargarit hedheeke araddinke qortumi'a hiisichchoke kaddaxxi 10 wogga'a turtaaxxi plane mari'etike mini'a shiqqe murteesende'en

( 15/2018 ) Ga/Qa/Ga/Mo/Koomunikeshiinen.

Gede'inxe Zoone'n Gadabeke qachchik mari'etiki mini 2018 G.W 'ni 3xxe tima woggaka hujetika muuxxa memmekisatiki 6xxe dawweki 24ki deetichchi yaa'i me'eme'en.

Gadabeke qachchike mari'et minik Yaa'i afo'i Aaddi Tegegn Tasamaki 3xxe tima woggake yaa'a'n saxxemaxxe 2xxe tima woggaki mari'etike miniki heddi ke'eemmaki laagaduwwi murteesemexxa kokessati wele wele ke'eeke yaaduwwa'ninna shiqqexxe eeruwwa'n badhaka yaado uwwe'en.

Gadabeke qachchike mari'etike minika 2018 woggaka 3xxe tima woggaka muuxa eero shiqisseexxi mari'etike minixxi itti aana yaa'i afo'i baaba Maaza Makuraxxi mari'etike mine'n sasiniinge handaara'n hujendeexxa huje mari'etike minixxe unoole'a shiqisse'en.

Shiqqexxe eero'n diidinxi to'e, sasinge handaara'n hujendaaxi tirtirsatixxi huje, teesso komitexxi hordoffenna ittanni wele welenna eloke garinni ca'a hite shiqqexxe kaddexxi kexxe'en.
Gadabeke qachchike murtetike minixxa 3xxe tima woggaxxa muuxa eero shiqiseek perezidaantich Tareqegn Xilahunik murtetik mini hujetixxe wogga'n lumolla araddinxa rakkuwwa tikeexxe kaddexxana seerimalexxe fugguwa'n toggitte murtuwwa uwwendeexxa eerote'n shiqise'en.

Gadabeke qachchiki itti aani kantiibinna nage'anna salala. Seera heqqisatixxe kilaasiteereki tirtirsanji Aaddi Katama Mogesik borrotike minuwwixxa 3xxe tima woggaxxa muuxa eero memmekisendaasha shiqiseexxe kadda wodda mari'etik minixxi unoolenna jabakanna shaqqaka darre memmekisse'en.

Baajetetixxe wogga'n eloxxe galcha'n, araddiinke mittoma'ninna haanjinninke darre'n hujendeexxi hujuwwa 2xxe tima wogga'n ke'eemaka heddo araddinka qortuma hiisitexxi huje hujendeexxe kaddexxi shiqqe'en.

Tomme wogga'a turtaaxxa haaroxxa qachchinxa pilaane gadabeke qachchik qophphesinke minik hujeti me'isalli aaddi Gizawu shiqiseexxe kadda wodda mari'etik mini memmekise uudati tomme wogga'a hujete'n hossasha murteesine'en.

Odo Gadabeke qachchixxe mootumatixxe koomunikeshiinexxen.

22/06/2026
‎የ2018 ዓ/ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ተግባራት በዞኑ አብይ ኮሚቴ ተገመገመ ‎‎( #ገደብ ሰኔ 15/2018 ዓ/ም) በጌዴኦ ዞን የ2018 ዓ/ም የክረምት...
22/06/2026

‎የ2018 ዓ/ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ተግባራት በዞኑ አብይ ኮሚቴ ተገመገመ

‎( #ገደብ ሰኔ 15/2018 ዓ/ም) በጌዴኦ ዞን የ2018 ዓ/ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ተግባራት በዞኑ አብይ ኮሚቴ ተገምግሟል ።

‎የጌዴኦ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደግነት ኃይሉ ዝርዝር ተግባራትን በሚመለከት ለአብይ ኮሚቴ አቅርቦ ውይይት ተደርጓል ።

‎አቶ ደግነት በማብራሪያቸው በዞኑ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ የተከናወኑ ተግባራት ከአመት አመት የተሻለ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

‎በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ በማድረግ ከመንግስትና ከህዝብ ይወጣ የነበረውን ሃብት እያስቀረ የሚገኝ ተግባር መሆኑን አንስተዋል ።

‎በዘንድሮውም ይህን በማጠናከር በ18 ዘርፎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰራ ነው አቶ ደግነት የገለጹት ።

‎ወጣቶችን በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ስምሪት መስኮች በንቃት በማሳተፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት እንደሚደረግ ተናግረዋል ።

‎የወጣቱን ሁለንተናዊ ስብዕና መገንባት እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባህል በማድረግ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን ከማጠናከር ረገድ ተግባሩ ያለው ፋይዳ የጎላ ነው ብለዋል ።

‎እንደ ዘንድሮ 4 መቶ ሺህ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችምን በ18 የስምሪት መስኮች በማሰማራት ከ1 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በአጽንኦት እንደሚሰራ አቶ ደግነት ገልጸዋል ።

‎የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ እና የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አዲሱ አየለ ፓርቲው ለበጎ ተግባር ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል ።

‎በዚህም ከጊዜ ወደ ጊዜ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሰው ተኮርነቱን እያረጋገጠ መሆኑን አቶ አዲሱ ተናግረዋል ።

‎እንደ ዘንድሮው የታቀደው እቅድ ከግብ እንዲደርስ ኮሚቴው ፊት በመሆን በማስተባበርና ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ሰብሳቢው አሳስበዋል ።

‎ለተግባሩ ስኬታማነት ወጣቶች ፣ የመንግስት ሰራተኞች ፣ የሐይማኖት ተቋማት ፣ የግል ባለሃብቶች ፣ የግል ድርጅቶች፣ ባንኮች፣ ግብረሰናይ ድርጅቶች ፣ የጸጥታ አካላት ፣ የሚዲያ ባለሙያዎች ፣ ዲያስፖራዎች እና ሌሎች በንቃት እንዲሳተፉ አቶ አዲሱ ጥሪ አቅርበዋል ።

‎የኮሚቴው አባላት በበኩላቸው የበጎ ተግባር የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት ያለውን ሚና በመረዳት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል ።

‎በባለፈው ዓመት ሲያጋጥሙ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት በዘንድሮው የተጠበቀ ውጤት እንዲመዘገብ ለማድረግ እንደሚንቀሳቀሱ አረጋግጠዋል ።

‎በቅርቡ በዞን ደረጃ የመርሃግብሩ መክፈቻ ተደርጐ በሁሉም መዋቅሮች ተግባሩ በሙሉ አቅም እንደሚከናወን ተገልጿል ሲል የዘገበው የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው ።

በገደብ ከተማ ምክር ቤት የ2018 3ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነውገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽንየገደብ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የ2018 3ኛ ሩ...
22/06/2026

በገደብ ከተማ ምክር ቤት የ2018 3ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነው

ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽን

የገደብ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የ2018 3ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ፣ 6ኛ ዙር 24ኛው መደበኛ ጉባኤውን ማከናወን ጀምሯል።

በጉባኤው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የገደብ ከተማ ምክርቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክቡር ተገኝ ተሰማ እንደተናገሩት ፦ ጉባኤው ላይ የስራ አስፈጻሚ ፣ የህግ ተርጓሚና የህግ አውጪ አካላት ርፖርት ቀርቦ እንደሚገመገም ተናግሯል ።

በ2018 በሃገራችን የተካሄደው ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ፍትሔዊ በመሆን በተጠናቀቀው ማግስት የሚናካሂደው ጉባኤ በመሆኑ ለየት ያደርገዋል ብለዋል።

ምክር ቤቱ በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ዘገባው የገደብ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው ።

የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክልል ምክር ቤቶች ውጤት*************1. ሐረሪ ክልልየተመዘገቡ መራጮች፡ 199,910የመቀመጫ ብዛት፡ 36የአሸናፊዎች ዝርዝር፡👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 32👉ኢዜማ፡...
21/06/2026

የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክልል ምክር ቤቶች ውጤት
*************
1. ሐረሪ ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 199,910
የመቀመጫ ብዛት፡ 36
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 32
👉ኢዜማ፡ 1
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 1
👉ጀማል አባጋሮ አህመድ (የግል)፡ 1
👉የሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 99%
2. መካከለኛው ኢትዮጵያ
የተመዘገቡ መራጮች፡ 2,340,664
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 170 (ከ34 የምርጫ ክልሎች)
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 140
👉ኢዜማ፡ 12
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 7
👉ኅብር ለኢትዮጵያ አንድነት፡ 3
👉ጉራጌ ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ፡ 3
👉የወላይታ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉የኦሞ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 96%
3. ሲዳማ ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 2,023,037
የመቀመጫ ብዛት፡ 190
የአሸናፊዎች ዝርዝር
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 175
👉መድረክ፡ 8
👉ሲዳማ አንድነት ፓርቲ፡ 3
👉የሲዳማ ሕዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፡ 1
👉ባንዲራ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ፡ 1
👉የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኩራት፡ 1
👉የመላው ሲዳማ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 97%
4. ሶማሌ ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 5,012,913
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 252 (ከ66 የምርጫ ክልሎች)
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 214
👉የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ONLF)፡ 20
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 13
👉የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፡ 2
👉አህመድ አርሻድ አሊ ኑር (የግል)፡ 1
👉የመላው ሶማሌ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉ኅብረት ለዲሞክራሲና ለነፃነት ፓርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 94%
5. ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል
የመቀመጫ ብዛት፡ 165
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 145
👉የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ፡ 15
👉የቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ፡ 4
👉ጌታቸው ወዲሻ ገሻዲ (የግል)፡ 1
6. አማራ ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 10,876,829
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 277
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 257
👉የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ፡ 4
👉ኢዜማ፡ 3
👉የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፡ 2
👉የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ፡ 1
👉የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፡ 1
👉ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ 1
👉ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት፡ 1
👉የዎሎ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 95%
7. አዲስ አበባ (ከተማ መስተዳድር)
የተመዘገቡ መራጮች፡ 1,957,676
የመቀመጫ ብዛት፡ 158
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 134
👉ኢዜማ፡ 8
👉አንዲት ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 4
👉ህዳሴ ፓርቲ፡ 2
👉የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)፡ 2
👉ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት፡ 2
👉ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ 2
👉የወላይታ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ፡ 1
👉አብን፡ 1
👉የዎሎ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉ዳንኤል ጌታቸው ጋረደው (የግል)፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 96%
8. አፋር ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 2,503,009
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 135
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 124
👉የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ፡ 4
👉መድረክ፡ 3
👉የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፡ 3
👉አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 94%
9. ኦሮሚያ ክልል
የተመዘገቡ መራጮች፡ 24,094,121
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 528 (ከ176 የምርጫ ክልሎች)
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 523
👉ፋጡማ ከማል ሁሴን (የግል)፡ 1
👉ፍልሀዲን ጠለሀ አህመድ (የግል)፡ 1
👉አቶ ሙሳኮ ሳሮባ (የግል)፡ 1
👉ንጋቱ ዋጋር ጀሳስ (የግል)፡ 1
👉ኢዜማ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 97%
10. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ
የተመዘገቡ መራጮች፡ 1,230,457
የመቀመጫ ብዛት፡ 171
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 144
👉ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ 12
👉ኢዜማ፡ 10
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 3
👉የዎሎ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 97%
11. ደቡብ ኢትዮጵያ
የተመዘገቡ መራጮች፡ 2,858,503
ውጤት የተገለጸባቸው መቀመጫዎች፡ 224 (ከ55 የምርጫ ክልሎች)
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 182
👉ኢዜማ፡ 27
👉የወላይታ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር፡ 3
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 2
👉የወላይታ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ፡ 2
👉ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ 2
👉ጌዴኦ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፡ 2
👉የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፡ 2
👉እነ ልቦ ጎዓ ዮታ (የግል)፡ 1
👉የጎዥ ሕዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ፡ 1
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 96%
12. ድሬዳዋ (ከተማ መስተዳድር)
የተመዘገቡ መራጮች፡ 269,102
የመቀመጫ ብዛት፡ 189
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 161
👉ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፡ 8
👉ኢዜማ፡ 6
👉አዲስ ትውልድ ፓርቲ፡ 3
👉የመራጮች ተሳትፎ፡ 98%
13. ጋምቤላ ክልል
የመቀመጫ ብዛት፡ 205
የአሸናፊዎች ዝርዝር፡
👉ብልጽግና ፓርቲ፡ 176
👉ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ 17
👉ኢዜማ፡ 6
👉ህዳሴ ፓርቲ፡ 3

በገደብ ከተማ ስሰጥ የቆየው የክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና ተጠናቀቀ ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽን በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ አስተዳደር ለተከታታይ ቀናት ስሰጥ የ...
19/06/2026

በገደብ ከተማ ስሰጥ የቆየው የክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና ተጠናቀቀ

ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽን

በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ አስተዳደር ለተከታታይ ቀናት ስሰጥ የቆየው የ2018 የክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና በሰላም ተጠናቋል ።

በገደብ ከተማ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ታደለ በየነ ፈተናው በሰላም መጠናቀቁ የተናገሩት ሲሆን ለተማሪዎች አርፍ ውጤት እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጿል ።

ለዚህም ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት አካላት ምስጋናቸውን አድርሷል ።

ዘገባው የገደብ ከተማ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው ።

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመኪና ሽልማት ተበረከተለት #ገደብ ፣ ሰኔ 12/2018 ዓ/ምተልዕኮዎችን በብቃትና በጥራት በመፈጸሙ የ...
19/06/2026

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመኪና ሽልማት ተበረከተለት

#ገደብ ፣ ሰኔ 12/2018 ዓ/ም
ተልዕኮዎችን በብቃትና በጥራት በመፈጸሙ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመኪና ሽልማት ተበርክቶለታል።

ወቅታዊና መደበኛ የፓርቲና መንግስታዊ ተልዕኮዎችን በብቃት በመፈጸሙ ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የተበረከተውን የመኪና ሽልማት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን በአካል ተገኝተው ተረክበዋል።

ኢንጅነር ተመስገን ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅት የተደረገው ማበረታቻ ሽልማት ለቀጣይ ተልዕኮ የይበልጥ የሚያተጋ መሆኑን ገልጸዋል።

አያይዘውም የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተግባራትን ቆጥረው በመገምገም ላደረገው ማበረታቻ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በገደብ ከተማ አመራሮች በልማት ሥራዎች እና በቀጣይ 1 ወር እቅድ ላይ የሚመክር መድረክ አካሄዱገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ በልማት...
18/06/2026

በገደብ ከተማ አመራሮች በልማት ሥራዎች እና በቀጣይ 1 ወር እቅድ ላይ የሚመክር መድረክ አካሄዱ

ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን

በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ በልማት ሥራዎች እና በቀጣይ 1 ወር እቅድ ላይ የሚመክር የአመራሮች መድረክ እየተካሄደ ነው።

በገደብ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢያሱ አበበ መድረኩን አስመልክቶ የተዘጋጀው ሰነድ አቅርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

የምርጫ ስራዎች አፈጻጸም ስኬታማ እንደነበረ የገለፁት የገደብ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን በርሶ ፦ ያሳየነውን ቁርጠኝነትን በድህረ ምርጫው ተግባራት መድገም ይኖርብናል ብለዋል።

ምርጫው መፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲከናወን የበኩሉን ለተወጣና ለመረጠው ህዝብ ዘላቂ ልማትን ማሳየት ይጠበቅብናል ሲሉም ተናግሯል ።

በተቀናጀ መንገድ በመምራት የተገኙ ስኬቶች ልቀጥል ያስፈልጋል ያሉት የዞን ደጋፊ የሆኑት አቶ አክልሉ ከድል የተሻሉ ተመክሮ የተቀመሩበት መሆኑን አንስተዋል ።

ስኬቱን በዘላቂነት ለማስቀጠል አመራሮች ድክመቶችን በመቅረፍ በመቀናጀት መስራት እንደሚገባ አስገንዝቧል ።

ዘገባው የገደብ ከተማ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው ።

በገደብ ከተማ የ2018 ክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽን የ2018 የክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ አ...
18/06/2026

በገደብ ከተማ የ2018 ክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው

ገደብ ከተማ ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የመንግስት ኮሙኒኬሽን

የ2018 የክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ተጀምሯል።

በዘንድሮው ክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና የሚቀመጡ በአጠቃላይ 606 ተማሪዎች መሆናቸውን መረጃ ያመለክታል ።

ፈተናውን ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ታደለ በየነ ከግብረሃይሉ ጋር በመሆን አስጀምረዋል ።

ዘገባው የገደብ ከተማ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው ።

Address

Gedeb Gedeo
Dilla

Telephone

+251913354266

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የገደብ ከተማ ኮሙኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category