22/08/2026
የምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ ሰላም ጸንቶ እንዲኖር የሚያደርግ ነው ሲሉ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
( #ገደብ ነሐሴ 16/2018 ዓ/ም) የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በምክክር የውስጥ ችግሮቿን ለመፍታት የወሰደችው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል ።
አስተዳዳሪው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በሰላምና በውጤት መጠናቀቁን አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ኢትዮጵያ ለዘመናት በአብሮነትና በአንድነት የዘለቀ የመኖር እሴት ያላት ሀገር ናት ።
ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያን አንድነት ለማፍረስ በውስጥና በውጭ ጠላት የተደረገ ሴራ ለማክሸፍ ኢትዮጵያ ላለፉት አራት ዓመታት አጀንዳ በማሰባሰብ ምክክር ስታካሂድ መቆየቷን አስተዳዳሪው ገልጸዋል ።
ይህም አሁን ላይ ፍሬ አፍርቶ የመጨረሻ ደረጃ ውጤት ሀገርን ማጽናት መሆኑን ማየት መቻሉን ነው ዶክተር ዝናቡ የገለጹት ።
በቀጣይም ቀሪው ሂደቶች የሚጠናቀቁ እንዳለ ሆኖ ጉባኤው በቀረበው አጀንዳ ላይ በመምከር የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በድጋሚ በአለም ገኖ እንዲታይ በማድረጉ በዞኑ ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል ።
በቀጣይም የምክክር ኮሚሽን በየደረጃው የሚያካሂዳቸው ሂደቶች በስኬትና በውጤት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ አስተዳዳሪው ጥሪ አቅርበዋል ።
@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት !