21/05/2026
የቤት ስጦታ ዉል አስፈላጊ የሆኑ 10 ቅድመ ሁኔታዎች
(ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል)
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
1. የቤት ስጦታ ውል በሕግ ፊት የጸና እንዲሆን በሰጪና በተቀባይ መካከል በጽሑፍ ተዘጋጅቶ በውልና ማስረጃ
ፊት መቅረብና መመዝገብ አለበት።
2. የቤቱ ስመ ንብረት ማስረጃ (ካርታ) ሰጪው የቤቱ እውነተኛ ባለቤት መሆኑንና ንብረቱን የመስጠት ሕጋዊ መብት እንዳለው ለማረጋገጥ ያገለግላል።
3. የሰጪና የተቀባይ የታደሰ መታወቂያዎች ውልና ማስረጃ ላይ ቀርበው የሚፈርሙትን አካላት ትክክለኛ ማንነት ለማረጋገጥ የሚጠየቁ መሠረታዊ ሰነዶች ናቸው።
4. የጋብቻ ሁኔታ ማስረጃ ቤቱ የባልና ሚስት የጋራ ንብረት መሆን አለመሆኑን በማጣራት የሕጋዊ አጋርን መብት ለመጠበቅ ወሳኝ ሚና አለው።
5. የግብር ዕዳ አለመኖሩን የሚያሳይ ማረጋገጫ (ክሊራንስ) ንብረቱ ከመዞሩ በፊት ለወረዳው ገቢዎች ጽሕፈት ቤት የሚገባው የመንግሥት የቤት ግብር በሙሉ መከፈሉን ያረጋግጣል።
6. ከእግድ ነፃ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ቤቱ በባንክ ብድር ዋስትና ወይም በፍርድ ቤት ክርክር ምክንያት ያልታገደ መሆኑን ለማረጋገጥ ይቀርባል።
7. የቤት ግምት ምንም እንኳ ዝውውሩ በነጻ የሚደረግ ቢሆንም፣ ለመንግሥት የሚከፈለውን የቴምብር ቀረጥና የስም ማዞሪያ ክፍያ ለማስላት ግድ ይላል።
8. እነዚህ ሰነዶች በሙሉ ተሟልተው ሲቀርቡ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የስጦታ ውሉን መርምሮ በሕጋዊ መንገድ ያጸድቀዋል።
9. ውሉ ከጸደቀ በኋላ የባለቤትነት መብቱ ከሰጪው ወደ ተቀባዩ እንዲዛወር ሰነዶቹ ለሚመለከተው የመሬት ማዘጋጃ ቤት ጽሕፈት ቤት ይመራሉ።
10. በመጨረሻም ማዘጋጃ ቤቱ የቀድሞውን የባለቤትነት ካርታ በመሰረዝ በተቀባዩ ስም አዲስ ሕጋዊ የቤት ካርታ ያዘጋጃል።
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል