ጠበቃ እሱባለው አማረ የሻነው

ጠበቃ እሱባለው አማረ የሻነው Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጠበቃ እሱባለው አማረ የሻነው, Lawyer & Law Firm, Debra Markos.

07/06/2024
30/07/2023

የፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም የመጀመሪያ ልጅ፣ ደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋርያት በግለ-ታሪካቸው መግቢያ የጻፉት ክስተት መቼም የማይረሳ ነው፡፡

“አንድ ቀን በጉባዔው ላይ ሲከራከሩ ሳለ፣ በብስጭትና በሐዘን እንባቸውን ሲጠርጉ ታይተው፣ ብዙ ሰዎች ከበቡዋቸውና ‘ምን ሆኑ?’ እያሉ ቢጠይቁአቸው ‘ድካሙ ነው’ አሉ ተብሎ በጋዜጦች ተገልጧል፡፡”

ትምህርት እና ተፈጥሮገናኑ ደራሲ ዳኛቸው ወርቁ "ምሥጢርስ ተፈጥሮ ተአምር የምትሠራበት ቀመር" የሚያስብል ታሪክ አለው። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ ክፍ...
06/10/2022

ትምህርት እና ተፈጥሮ

ገናኑ ደራሲ ዳኛቸው ወርቁ "ምሥጢርስ ተፈጥሮ ተአምር የምትሠራበት ቀመር" የሚያስብል ታሪክ አለው። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ ክፍል የተማሪነት ዘመኑ "እንደ ነገሩ" እንዳለፈ ተጽፎ አንብበናል። መምህሩ በኋላም አለቃው የነበሩት ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በግለ ታሪካቸው ይህን መስክረዋል።

"አቶ ዳኛቸው ወርቁ ... ተማሪዬ ነበር፤ በትምህርቱ ጎበዝ ባይሆንም፥ የድርሰት ዝንባሌ ስላየሁበትና የአስተማሪ እጥረት ስለነበረብን፥ የመጀመሪያውን አካዳሚክ ማዕርግ እንደያዘ እንዲቀጠር አደረግሁ።”

በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ትምህርት "ጎበዝ ባይሆንም" የተባለው ዳኛቸው ወርቁ ርዕሱ “The Thirteenth Sun” የሆነ በ1965 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ከታተመ በኋላ ወደ ሦስት ቋንቋዎች (ፖርቱጊስ፣ ጀርመንኛና ቻይኒስ) ተተርጉሞ በስፋት የተነበበ፤ በታላላቅ የምዕራባውያን የፈጠራ ጽሑፍ ትምህርት ቤቶች በማስተማሪያነት እያገለገለ የሚገኝ መጻሕፍ ደርሷል።

ምሥጢርስ ተፈጥሮ ተአምር የምትሠራበት ቀመር።

በተለያየ ዘመንና ሥፍራ ሀገርን የመሩ ሦስት ሰዎችን አደንቃለሁ፡፡ አንዱ ቋረኛው ንጉሥ ቴዎድሮስ ነው፡፡ ለምን? እነሆ ከብዙ ሦስት ምክንያቶች፡-***በግልፅ እና በዝርዝር ከሚታወቀው ልጀምር፡...
03/10/2022

በተለያየ ዘመንና ሥፍራ ሀገርን የመሩ ሦስት ሰዎችን አደንቃለሁ፡፡ አንዱ ቋረኛው ንጉሥ ቴዎድሮስ ነው፡፡ ለምን? እነሆ ከብዙ ሦስት ምክንያቶች፡-

***
በግልፅ እና በዝርዝር ከሚታወቀው ልጀምር፡፡ በፖለቲካ ታሪካችን ሥልጣንን እና ባለሥልጣንን የሚያገናኘው ትጋት ወይም ብቃት አይደለም፡፡ አጋጣሚ ነው፡፡ አጋጣሚው ለዙፋን “ከተመረጠ” የዘር ሀረግ መወለድ ሊሆን ይችላል፡፡ አጋጣሚው የፖለቲካ ሥልጣን የያዘ ስብስብ አባል ሆኖ መገኘት ሊሆን ይችላል፡፡ ከጥንት እስከ አሁን፣ መሪዎቻችን በአጋጣሚ በተገኙበት የሥልጣን ወለል ላይ የበቀሉ ናቸው፡፡ ቴዎድሮስ በአጋጣሚ በተገኘበት የሥልጣን ወለል ላይ የበቀለ መሪ አይደለም፡፡ ሥልጣኑ የትጋት - የብቃት ውጤት ናት፡፡ የቴዎድሮስን የንግሥና ዘመን ስኬት እና ፍጻሜ ነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ “አጤ ምኒልክና ኢትዮጵያ” በተሰኘው መጻሕፍ በጥሩ ገልጾታል፡-

“ያ ቋረኛ ንጉሥ ተበጣጥሰው የነበሩትን ያበሻን መንግሥት ክፍሎች በሰላው ጎራዴው ቀጥቅጦ አዋደደ፡፡ ሕዝቡንም ከካህናትና ከሹሞች ቀምበር አርነት ሊያወጣ አገር በጄ ብሎ አወጀ ትምህርትንም ሊከፍት ተከራከረ፡፡ አንባቢ ሆይ በዚህ ጥረቱ ምን ተጠቀመ ይመስልሃል፡፡ በመላው ሕዝብ በካህናትና በሹሞች ተመክሮ ተነሳበት አሳበደውም፡፡ በመጨረሻም ለባዕድ አሳልፎ ሰጠው በገዛ እጁም ሞተ፡፡”

***
ዳግማዊ ቴዎድሮስ እና አብርሃም ሊንከን በተለያየ ሥፍራ በተመሳሳይ ጊዜ የተለያዩ ሕዝቦችን መርተዋል፡፡ የቴዎድሮስ ሰሞነ-ፍስሐ (heydays) ከአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት (American Civil War) ጋር የተገጣጠመ ነበር፡፡ ቴዎድሮስ የዚህ ጦርነት ውጤት የዓለምን የፖለቲካ ሥርዓት እንደሚወስን የተረዳው ገና በጦርነቱ ጅማሬ ነው፡፡ የፖለቲካ እርምጃዎቹን ከዚህ ጦርነት ውጤት ጋር ለማስማማት፣ ስለጦርነቱ መረጃዎችን ያሰባስብ እንደነበር ተጽፎ አንብበናል፡፡ ለማሳያ በአጼ ቴዎድሮስ ተይዘው ከታሰሩት እንግሊዛውያን መካከል አንዱ የነበረው ዶክተር ሔንሪ ብላንክ የጻፈውን እንጥቀስ፡-

“The following day, during the march, Theodore sent Samuel backwards and forwards with questions,--such as: ‘Is the American war over? How many were killed? How many soldiers had they? Did the English fight with the Ashantees? Did they conquer them? Is their country unhealthy? Is it like this?’ …”

***
ዳግማዊ ቴዎድሮስ ቋንቋ ሲጠብ መግባቢያ ሲሰፋ የፖለቲካ መሳሪያ መሆኑን የተረዳ መሪ ነው፡፡ በዘመኑ የኢትዮጵያ ግዛት ለሚገኝበት ንፍቀ-ዓለም የአረብኛ ቋንቋ ዕውቀት ቁልፍ የፖለቲካ መሳሪያ ነበር፡፡ ቴዎድሮስ ይህን በመገንዘብ አረብኛ ለመማር ሞክሯል፡፡ ዶክተር ሔንሪ ብላንክን በድጋሚ እንጥቀስ፡-

“… Mr. Rassam, having complimented his Majesty on his great work, added, that before long he hoped that our people would have the same pleasure of admiring it as we did. Samuel, who translated on that occasion, turned quite pale, but as … Emperor [Theodore] understood a little Arabic he was obliged to render the sentence, though he evidently did not like it.”

(የተያያዘው ምስል “THE END OF KING THEODORE” ከሚል መግለጫ ጋር የተገኘው ሔንሪ ስታንሊ በግሪጎሪያኑ የዘመን አቆጣጠር በ1896 ‹‹Magdala: The Story of the Abyssinian Campaign of 1866-7›› በሚል ርዕስ ካሳተመው መጻሕፍ ነው፡፡)

02/10/2022

Ethiopia Legal Network’s Quote of the Week.

ተንኮል እና መከፋፈል የነገሱበትን የፖለቲካ ታሪካችንን ለማደብዘዝ፣ የጽሑፍ ታሪካችንን ማድመቅ ፍቱን መድኃኒት ይመስለኛል።ከ389 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርዐ ያዕቆብ አክሱማዊ (...
01/10/2022

ተንኮል እና መከፋፈል የነገሱበትን የፖለቲካ ታሪካችንን ለማደብዘዝ፣ የጽሑፍ ታሪካችንን ማድመቅ ፍቱን መድኃኒት ይመስለኛል።

ከ389 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርዐ ያዕቆብ አክሱማዊ (ወርቄ) በተወለደበት ሀገር በአክሱም ጠላቶች ሲነሱበት የተሰደደው ወደ ጎንደር እንፍራዝ ነው። የሕይወቱን ብዙ ምዕረፍ የኖረውም፣ ፍልስፍናውን የጻፈውም፣ አግብቶ የልጅ ልጆች ያየውም፣ ያረጀውም፣ የሞተው፣ የተቀበረውም.... በጎንደር እንፍራዝ ነው።

የኦቦ ገብረመድኅን ሮባን ልጅ - ጸጋየ ገብረመድኅንን - ግዕዝና ዜማ ያስተማሩት፣ ቅኔ ያስቀፀሉት ... የአንኮበር አማራ ተወላጅ የነበሩት የእናቱ ዘመዶች ናቸው። ጸጋየ ለአባቱ ከተማ ለአምቦ፣ ለእናቱ ቅየ ለአንኮበር፣ ለወይጦ ባላገር፣ ለሐረር፣ ለአሥመራ፣ ለማይጨው፣ ለአዘቦ ... በእኩል ስሜት ተቀኝቷል።

የጎጃምን ሙሉዕ የትውልድ ሰንሰለት ቆጥረው የጻፉት የወለጋው አለቃ ተክለኢየሱስ ዋቅጅራ ናቸው።

ዳኛቸው ወርቁ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሌሎች ጋር ያልተቀላቀለ ንፁህ ብሔር የለም ይላል፡፡ የአባቱ የአቶ ወርቁ በዛብህ እናት የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ እንደሆኑም ራሱ ዳኛቸው ለዶክተር ሬይዱልፍ ሞልቬር ተናግሯል፡፡ ስለ ራሱ ብሔር በዶክተር ሞልቬር ተጠይቆ የሰጠው መልስም፤ “no tribal feelings”፡፡

ስለ ኃይለመለኮት መዋዕል ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ መጻሕፉ እንዳሰፈረው፣ "... [ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል] ግማሽ መንዜ - ግማሽ ኤርትራዊ ነው። ከሁለቱም ወገን አክስቶቹ እሱ ቤት ሲገናኙ እሱ አስተርጓሚ ሆኖ ያዋያቸዋል። ማርያም ሰላም ታመጣ ዘንድ የሚለምኑ ደጋግ አክስቶች ነበሩት። የኢትዮ - ኤርትራ ጦርነት እየተካሄደ እነሱ ቡና እየጠጡ አምላክን ይለማመኑ ነበር።

የስብሐት ገብረእግዚአብሔር የመጀመሪያ ባለቤት የሰሎሞን ዴሬሳ የአጎት ልጅ - ሃና ይልማ ዴሬሳ - ነበረች። ጎህ ሳይቀድ ፣ "ታሪክ ነው!" የሚል ርዕስ በሰጠው ወለሎ..
"የጠፋውን ሁሉ ባማራ አሳበን፤ የለማውን ልንሰጥ ለማን?" ብሎ ለአማራ ሕዝብ ጥብቅና የቆመው የጩታው (የወለጋው) ሰሎሞን ዴሬሳ ነው።

በዓሉ ግርማ (በአባት ህንዳዊ) እና ጳውሎስ ኞኞ (በአባት ግሪካዊ) አብሮነታችን ባሕር ተሻጋሪ ለመሆኑ ማስረጃዎች ናቸው።

ከሩብ ምዕተ-ዓመት በፊት  "ታሪክ ነው!" የሚል ርዕስ በሰጠው ወለሎ…"የጠፋውን ሁሉ ባ’ማራ አሳበን፤ የለማውን ልንሰጥ ለማን?" ብሎ ለአማራ ሕዝብ ጥብቅና የቆመው የጩታው (የወለጋው) ሰሎሞ...
30/09/2022

ከሩብ ምዕተ-ዓመት በፊት "ታሪክ ነው!" የሚል ርዕስ በሰጠው ወለሎ…
"የጠፋውን ሁሉ ባ’ማራ አሳበን፤ የለማውን ልንሰጥ ለማን?" ብሎ ለአማራ ሕዝብ ጥብቅና የቆመው የጩታው (የወለጋው) ሰሎሞን ዴሬሳ ነበር፡፡

ቃላት magic ለመሥራታቸው ማስረጃ፡፡
29/09/2022

ቃላት magic ለመሥራታቸው ማስረጃ፡፡

በዚህ ዘመን ለሙግት ከማይቀርቡ አርዕስት መካከል አንዱ የሌቭ ቶልስቶይ ታላቅ ጸሐፊነት ነው። ሌቭ ቶልስቶይ ከቀዳማይና ተከታይ ደራሲያን በሁለት ነቁጦች ይለያል።አንድ፣ ሦስትዮሽ (triangu...
28/09/2022

በዚህ ዘመን ለሙግት ከማይቀርቡ አርዕስት መካከል አንዱ የሌቭ ቶልስቶይ ታላቅ ጸሐፊነት ነው። ሌቭ ቶልስቶይ ከቀዳማይና ተከታይ ደራሲያን በሁለት ነቁጦች ይለያል።

አንድ፣ ሦስትዮሽ (triangular) የሕይወትና የድርሰት ጉዞ። ቶልስቶይ ሕይወቱም የድርሰቶቹ ፈትለ-ነገርም ሦስት ነጥቦችን የሚዞር ነው፡፡ እምነት፣ ጥርጣሬና ስብከት።

ሌቭ ቶልስቶይን ልዩ የሚያደርገው ሁለተኛው ምክንያት ሁለንተናዊነቱ ነው። የሰው ልጅ አዕምሮ ሊያፈልቃቸው የሚችላቸውን ሀሳቦች፣ ሰበበ-ድርጊቶች (motives) እና የድርጊት ማረጋገጫዎች (justifications) በብቃትና በጥልቀት ማወቁ። ይህን ለመረዳት፣ "The Kreutzer Sonata" የተሰኘውን ድርሰቱን ማንበብ ብቻ በቂ ይመስለኛል።

ከሰባት ዓመታት በፊት የተረጎምኳቸውን የሌቭ ቶልስቶይ አምስት አጫጭር ድርሰቶችን (ታሪኮችን) ከሥር በተያያዘው ሊንክ ማግኘት ይቻላል።
> https://t.me/EsubalewAmareLawOffice/67

በፍሎይድ ዴል የትውልድ ሀገር “ብሔራዊ የስካርፍ ቀን” ትላንት ተከብሮ ውሏል፡፡ ለራሴ ሥም ለመስጠት ደፋር በነበርሁበት ሰሞን "Floyd-Dellean ነኝ" ባይ ነበርሁ። ራስን Floyd-De...
28/09/2022

በፍሎይድ ዴል የትውልድ ሀገር “ብሔራዊ የስካርፍ ቀን” ትላንት ተከብሮ ውሏል፡፡ ለራሴ ሥም ለመስጠት ደፋር በነበርሁበት ሰሞን "Floyd-Dellean ነኝ" ባይ ነበርሁ። ራስን Floyd-Dellean ብሎ መጥራቱ ተቀንሶ፣ ዛሬም የአሜሪካዊው ‹‹አራት ዓይና›› ጸሐፊ ፍሎይድ ዴል አድናቂ ነኝ፣ በርግጥ።

ዴል ተፅዕኖ ያላሳረፈበት አሜሪካዊ ደራሲ ማግኘት ከባድ ነው። በተለይ እነ እዝራ ፖንድ፣ ቻርሎቴ ጊልማን፣ ቴዎዶር ድሬይሰር፣ ኤድና ቪንሴንት ሚላይ... የፍሎይድ ዴል ደቀ-መዛሙርት ናቸው።

ዛሬ ድረስ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ ደራሲያን ሕይወትና ሥራ የምናየው bohemian, socialist, Nietzschean & Freudian ባሕርይም የፍሎይድ ዴል ውርስ ነው።

እዚህ አገር ከዴል የተወረሰችው ዝነኛ ብቸኛ ባሕርይ ስካርፍ መጠምጠም ነች። ወራሾቹ አውራሻቸውን ባያውቁም። የሚገርመው ዴል ስካርፍ መጠምጠም የጀመረው በድሎት ሳይሆን በዕጦት መሆኑ። ማስረጃ፤

"... [Floyd Dell] had grown his hair long, flaunting his indifference to the clean-cut appearances of conventional youths, and he had taken to wearing a bohemianlike black silk scarf around his pale throat ... what he never admitted ... was that the scarf was really an affectation of convenience: he wore it mainly because he could not afford clean white collars".

- "Floyd Dell: The Life and Times of an American Rebel", Page 25

ለዴል የባሕርይ ወራሾች ሁሉ፣ !

28/09/2022

የሥራ ማስታወቂያ

ድርጅት፡- ብላክ ፊውቸር አ.ማ
የሥራ መደብ፡- የሕግ ባለሙያ
ተፈላጊ የሥራ ልምድ፡- ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት
ብዛት፡- በድምሩ 10
የሥራ ቦታ፡- አዲስ አበባ
የምዝገባ ጊዜ፡- እስከ መስከረም 20 ቀን 2015 ዓ.ም

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ገቢዎች ቢሮ በድለላ ሥራ የተሰማሩ ሰዎች ግብር የሚከፍሉበትን ሥርዓት የሚዘረጋ አዲስ መመሪያ አፅድቋል፡፡ መመሪያው በክልሉ ውስጥ በድለላ ሥራ በመሰማራት ልዩ...
26/09/2022

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ገቢዎች ቢሮ በድለላ ሥራ የተሰማሩ ሰዎች ግብር የሚከፍሉበትን ሥርዓት የሚዘረጋ አዲስ መመሪያ አፅድቋል፡፡ መመሪያው በክልሉ ውስጥ በድለላ ሥራ በመሰማራት ልዩ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረት፣ እንዲሁም የአክሲዮን ግብይትና ኪራይ በማመቻቸት ገቢ በሚያገኝ ማንኛውም ሰው ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ አዲሱ መመሪያ ገዥና ሻጭ የሥመ ንብረት ዝውውር ወይም የኪራይ ውል ሲፈጽሙ ያገናኛቸውን ደላላ የንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የምስክር ወረቀት እንዲያቀርቡ ያዝዛል፡፡
በአዲሱ መመሪያ መሠረት በክልሉ የሚሠሩና የፀና የድለላ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ደላሎች ያመቻቹት ግብይት ተጠናቆ የሥመ-ንብረት ዝውውር ሲደረግ ወይም የኪራይ ውል ሲፀድቅ ካገኙት የድለላ ሥራ ገቢ ላይ 30% የገቢ ግብር እና 10% ተርን ኦቨር ታክስ እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
ገዥና ሻጭ ተገኛኝተው ግብይት የፈፀሙት ሕጋዊ ፈቃድ በሌለው ደላላ ከሆነና ለዚህ የድለላ አገልግሎት ክፍያ ከፈጸሙ፤ 30% የገቢ ግብር እና 10% ተርን ኦቨር ታክስ ራሳቸው ገዥና ሻጭ እንዲከፍሉ መመሪያው ደንግጓል፡፡ ሆኖም ግን ገዥና ሻጭ ያለደላላ በራሳቸው ተገናኝተው ግብይት ከፈፀሙ የገቢ ግብር እንዲከፍሉ አይጠየቁም፡፡
ይህን አዲስ መመሪያ የሚከተለውን ማስከንተሪያ (link) በመጫን ማግኘት ይችላሉ፡፡ > https://t.me/TheLawOfficeofEAY/64

Address

Debra Markos

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠበቃ እሱባለው አማረ የሻነው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ጠበቃ እሱባለው አማረ የሻነው:

Share