Lawyer

Lawyer Attorney and legal advisory

25/06/2026
25/06/2026

ጥልቅ የሀዘን መግለጫ ​በአሩሲ አካባቢ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች እና በቤተክርስቲያን ላይ የተፈፀመው ዘግናኝ ግድያ እና ጥቃት ሰብአዊነት የጎደለው ብቻ ሳይሆን፣ በሀገሪቱ ህገ-መንግስት እ...
04/06/2026

ጥልቅ የሀዘን መግለጫ
​በአሩሲ አካባቢ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች እና በቤተክርስቲያን ላይ የተፈፀመው ዘግናኝ ግድያ እና ጥቃት ሰብአዊነት የጎደለው ብቻ ሳይሆን፣ በሀገሪቱ ህገ-መንግስት እና አለምአቀፍ ስምምነቶች የተረጋገጡ መሰረታዊ ሰብአዊ መብቶችን በከፋ ሁኔታ የጣሰ ድርጊት ነው።ይህ ድርጊት ​ከህግ አንጻር ስንመለከተው፦
​የመኖር መብት (Right to Life): ማንኛውም ሰው በህይወት የመኖር መብት አለው። ይህ ጥቃት በኢፌዴሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 14 እና 15 ላይ የተደነገገውን የተቀደሰ የመኖር መብት የገፈፈ ነው።
​የእምነት ነፃነት (Freedom of Religion): በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 27 መሰረት ማንኛውም ሰው የመረጠውን እምነት የመያዝ እና የማከናወን መብቱ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ይህ ጥቃት የእምነት ተቋማትን እና አማኞችን ኢላማ በማድረግ መብቱን ጥሷል።
​የመንግስት ግዴታ (Duty of the State): መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ እና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ቀዳሚ ኃላፊነት አለበት (አንቀጽ 52)።
​ጥሪያችን፦
1ኛ.​የሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት በጥቃቱ የተሳተፉ ወንጀለኞችን በአስቸኳይ ለህግ እንዲያቀርቡ።
2ኛ.​በግፍ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች ተገቢው ፍትህ እና ካሳ እንዲሰጥ።
3ኛ.​ወደፊት መሰል የህግ ጥሰቶች እንዳይደገሙ ዘላቂ የህግ ከለላ እንዲደረግ
4ኛ.መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ እና ጥፋተኞችን ለህግ የማቅረብ ኃላፊነቱን ይወጣ ህግ ባለበት ሀገር የንፁሃን ደም በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም በንፁሃን ላይ የሚፈፀም ግፍ ይቁም በማለት ጥሪያችንን እያቀረብን
በአጠቃላይ ​​በአሩሲ በሰው ህይወት እና በእምነት ተቋማት ላይ የተፈፀመው ጥቃት የዜጎችን በሰላም የመኖር እና የማመን መብት በከፍተኛ ደረጃ የሚጥስ አሳዛኝ ድርጊት ነው። በግፍ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ጥልቅ ሀዘናችንን እየገለጽን፣
ለሟች ቤተሰቦች እና ለመላው የቤተክርስቲያን ልጆች መጽናናትን​፣ለሀገራችን ሰላምን እንመኛለን።
የህግ የበላይነት ይከበር፤ በንፁሃን ላይ የሚፈፀም ግፍ በህግ ይጠየቅ!
#ፍትህ #የህግየበላይነት #አሩሲ #ኢትዮጵያ
ሙሉጌታ ንጉሴ ታደሰ ጠበቃ ና የህግ አማካሪ

Address

Debra Markos

Telephone

+251936695274

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lawyer posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share