Biruk Assefa Legal Service/ብሩክ አሰፋ የሕግ አገልግሎት

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • Biruk Assefa Legal Service/ብሩክ አሰፋ የሕግ አገልግሎት

Biruk Assefa Legal Service/ብሩክ አሰፋ የሕግ አገልግሎት Top Rated Legal Service Provider in Southwest Ethiopia Regional State, Ethiopia. Biruk Assefa +251938489815
Your First Choice!

👉በደቡብ ምእራብ ለሚገኙ ጠበቆች በጠበቆች መሀበር ስልጠና ተሰጠ!!!!!!የሙያ ስነምግባር የሚያከብር ብቃት ያለቸው ጠበቆችን ለማፍራት ተግተን እንሰራለ!!! በሚል መርህን  አስቀምጦ  የደቡብ...
17/05/2024

👉በደቡብ ምእራብ ለሚገኙ ጠበቆች በጠበቆች መሀበር ስልጠና ተሰጠ!!!!!!

የሙያ ስነምግባር የሚያከብር ብቃት ያለቸው ጠበቆችን ለማፍራት ተግተን እንሰራለ!!! በሚል መርህን አስቀምጦ የደቡብ ምዕራብ ክልል ጠበቆች ማህበር በክልሉ ርዕሰ ከተማ ቦንጋ በመምህራን ትምህርት ኮሌጅ አዱራሽ በውይይት የተደገፈ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዋናነት የስልጠናው ይዘት አስመልክቶ ፦
1. በጠበቆች ሥነ ምግባር እና የሰነ ምግባር ሙያው ከሚጠይቀው አንፃር ሊኖር የሚገባው የሥነ ምግባር ግዴታዎች ላይ
2. በተገቢው መረጃዎች ላይ በመደገፍ ሥራውን የመስራት እና ተገቢውን መረጃ ለሥራው የሚጠቅመውን ተገቢነቱ ከታመነ ከየትኛውም አካል ቀርቦ መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብት ያለው ስለመሆኑ እና
3. በአዋጁ 1249/13 2/8/ 19/15 2/10/ 2/4/ በዚህ ህግ ""የደንበኛ ማንነት እና የደንበኛ ጉዳይ ምን እነደሆነ እና ምን እንደምመስል እንዲሁም የደንበኛ አቀባበልና የማገልገል ግዴታ እንዲሁም የደነበኛ እምነትን ስለማግኘት " ጠበቃ እና የህግ ምሁር እንዲሁም የጠበቆች ማህበር ሰቢሳቢ የሆኑ አቶ አብዱረህማን / LLB/LLM / በብቃት የተደገፈ በውይይት የተደገፈ ስልጠና ሰጥተዋል።

የይርጋ መቋረጥ/እንደ አዲስ መቆጠር መጀመር/=================➦በፍ/ብ/ሕ/ቁ/1852 ድንጋጌ መሠረት ይርጋ በተቋረጠ ጊዜ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ እንደገና አዲስ የይርጋ ዘመን መቁጠ...
04/12/2023

የይርጋ መቋረጥ/እንደ አዲስ መቆጠር መጀመር/
=================
➦በፍ/ብ/ሕ/ቁ/1852 ድንጋጌ መሠረት ይርጋ በተቋረጠ ጊዜ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ እንደገና አዲስ የይርጋ ዘመን መቁጠር እንደሚጀምር በዚሁ ድንጋጌ በንዑስ ቁጥር /1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የሚቻለው ይርጋው በተቋረጠ ጊዜ ቀድሞ የነበረው የይርጋ ጊዜ እንደ አዲስ መቁጠር የሚጀምር መሆኑን ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 31185 ቅጽ 6
➦በሕግ ተለይቶ የተወሰነ የይርጋ ጊዜ የመቋረጥ እና ያለመቋረጥ ጉዳይ አከራካሪ ነጥብ ሆኖ ሊነሳ የሚችለው የይርጋውን መቆጠር ያቋርጠዋል የተባለው ምክንያት የተከሰተው የይርጋው ጊዜ ከመሙላቱ በፊት በሆነ ጊዜ እንጂ የይርጋው ጊዜ የሞላ ወይም ያለፈ በሆነ ጊዜ ጭምር አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 90361 ቅጽ 6
➦ክስ የማቅረብ ውጤት ስልጣን ለሌለው የዳኝነት አካል ክስ ማቅረብ ይርጋን ያቋርጣል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 36730 ቅጽ 9
➦ክስ የማቅረብ ውጤት /ሽያጭ ውል/ ይርጋ ከሚቋረጥባቸው ምክንያቶች አንደኛው ባለገንዘቡ መብቱ እንዲታወቅለት በፍ/ቤት ክስ አቅርቦ ለባለእዳው አስታውቆ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 43992 ቅጽ 10፣ ፍ/ህ/ቁ. 1851(ለ)
➦ክሱ የቀረበው መብቱን በሚጠይቀው ባለገንዘብ ባይሆንም ባለዕዳው በባለገንዘቡ ላይ ያቀረበው ክስ በይዘቱ የይርጋ መቃወሚያ ከተነሳበት ክስ ጋር ተያያዥነት ካለው ይርጋውን ያቋርጠዋል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢ ንብረቱን ለመረከብ (የሽያጭ ውሉ እንዲፈጸምለት) ያቀረበው ክስ ከሽያጭ ውሉ ቀን ጀምሮ ሲቆጠር በይርጋ የሚቋረጥ ቢሆንም ሻጭ ቀደም ብሎ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስለት ክስ ካቀረበ በገዢው ላይ ተፈጻሚ የሚሆነውን የይርጋ ጊዜ ያቋርጠዋል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 43636 ቅጽ 10
➦በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1776 እና በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 ድንጋጌዎች መሠረት የቤት ሽያጭ ውል ይፈጸምልኝ ክስ ሲቀርብ በሕግ የተደነገገው የይርጋ ሕግ የጊዜ ገደብ አልፏል ወይስ አላለፈም? የሚለውን ነጥብ ለመወሰን በመጀመሪያ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ እንደዚሁም ድንጋጌው ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2875 መሠረታዊ መርህና ስለ ሽያጭ እና ጠቅላላ ውል ከተደነገጉ ድንጋጌዎች ጋር ሊኖረው የሚገባውን ተፈፃሚነት መመርመር ያስፈልጋል፡፡
ሻጭ በውሉ መሠረት ለመፈፀም የማይፈልግ መሆኑን ገዥ ያረጋገጠ መሆኑን ገዥ ውሉ እንዲፈፀምለት ማስጠንቀቂያ መስጠቱንና ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ሻጭ በውሉ መሠረት አለመፈፀሙን በማየት ብቻ ለማረጋገጥ አይችልም፡፡ ሻጭ ገዥ ማስጠንቀቂያ ከሰጠው በኋላም ቢሆን የተለያዩ ችግሮችን እያነሣ በመካከላቸው ያለውን የመተማመንና የቅን ልቦና ግንኙነት ተጠቅሞ ከአንድ ዓመት በላይ ውሉን ሣይፈፅም የሚቆይበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ ስለዚህ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ይርጋ ተፈፃሚነት የሚኖረው ገዥ ለሻጭ ማስጠንቀቂያ የሰጠበትን ቀን መነሻ በማድረግና ጊዜውን በማስላት ሣይሆን ሻጭ በውሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ገዥ እንዲያውቀው ያደረገበትን ቀን መነሻ በማድረግ መሆን ይገባዋል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 38935 ቅጽ 8
➦ሻጭ የውል ይፍረስልኝ ክስ ለፍርድ ቤት ማቅረቡ ውሉን ለመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን ለገዢ በማያሻማ መንገድ ከማሣወቅ ያለፈ ምክንያትና ውጤት ያለው ተግባር ነው፡፡ ሻጭ ውሉ እንዲፈርስ ሲጠይቅ ውሉ ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለማቋቋም የማያስችሉ ጉድለቶች ያሉበት በሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች እንደ ሕግ ሆኖ ሊገዙበት የማይገባ መሆኑን የሚያሣዩ የውሉን ሕልውና ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባና የውል ሕጋዊነት በፍርድ ቤት ተመርምሮ ፈራሽ እንዲባል ወይም እንዲሠረዝ የሚቀርብ ነው፡፡ የውሉ ሕጋዊነትና ሕልውና ጥያቄ ተነስቶበት በፍርድ ቤት በሚመረመርበት ጊዜ ሂደት ገዢ ውሉ ሕጋዊ መሆኑን ከማሣየትና ከማስረዳት አልፎ ውሉ በግዳጅ እንዲፈጽምለት የመጠየቅ ግዴታ አይኖርበትም፡፡
ከዚህ አንፃር ውሉ በፍርድ ቤት ፈራሽ እንዲሆን ወይም እንዲሰረዝለት በውሉ የሚገደድበት ሁኔታ ይቋረጣል፡፡ በሌላ በኩል በክርክሩ ከተረታ ገዢ ሕጋዊ ተፈፃሚነትና አስገዳጅነት ባለው ውሉ ንብረቱን የገዛ መሆኑ ከሻጭ ጋር ባደረገው የውል ሰነድ ብቻ ሣይሆን በፍርድ ቤት ውሣኔ የተረጋገጠለት የፍርድ ባለመብት ይሆናል፡፡ ስለሆነም ገዢ ፍርድ ቤቱ ሕጋዊነቱንና አስገዳጅነቱን መርምሮ በፍርድ ያረጋገጠውን ውል እንዲፈጽምለት ሻጭን የመጠየቅ መብቱ በፍርድ ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 384/ሀ/ በተደነገገው አስር ዓመት ጊዜ ውስጥ እንጂ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 በተደነገገው የአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ የሚገደብ አይደለም፡፡ ስለዚህ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀስ 3 የተቀመጠው የጊዜ ገደብ በዚህ ጉዳይ አግባብነት የለውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 39725 ቅጽ 8

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ተፈጻሚነት ያለው የይርጋ ደንብ በፍትሐ ብሔር ሕጉ አንቀጽ 1149/2/ የተመለከተው የሁለት ዓመት የይርጋ ጊዜ ነው፡፡ በይዞታ አጠቃቀም ላይ የኃይል ድርጊት ወይም ጣል...
24/11/2023

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ተፈጻሚነት ያለው የይርጋ ደንብ በፍትሐ ብሔር ሕጉ አንቀጽ 1149/2/ የተመለከተው የሁለት ዓመት የይርጋ ጊዜ ነው፡፡ በይዞታ አጠቃቀም ላይ የኃይል ድርጊት ወይም ጣልቃ ገብነት ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ክስ መቅረብ አለበት፡፡

የሠ/መ/ቁጥር 235430 ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ/ም

ዝርዝር የውሳኔውን ፍሬ ነገር ከስር ከተያያዘው ሰነድ ይመልከቱ

❗የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁ.1284/2023የዲጂታል መታወቂያ የአንድን ነዋሪ ማንነትንለማስረዳት ወይም ለማረጋገጥ እንደ ህጋዊ እና በቂ ማስረጃ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል❗ #ሀበሻ  ...
23/11/2023

❗የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁ.1284/2023

የዲጂታል መታወቂያ የአንድን ነዋሪ ማንነትንለማስረዳት ወይም ለማረጋገጥ እንደ ህጋዊ እና በቂ ማስረጃ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል❗

#ሀበሻ

ሰዎች የይርጋ ጊዜ አስመልክቶ በቂ ግንዛቤ ባለመያዝ ለክፍተኛ ፍትህ እጦት ሲዳረጉ ይታያል ለዚህም በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ የይርጋ መቆጠር የሚጀምርበት ከመቼ ጀምሮ እንደሆነ ማወቁ አስፈላጊ በመ...
27/09/2022

ሰዎች የይርጋ ጊዜ አስመልክቶ በቂ ግንዛቤ ባለመያዝ ለክፍተኛ ፍትህ እጦት ሲዳረጉ ይታያል ለዚህም በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ የይርጋ መቆጠር የሚጀምርበት ከመቼ ጀምሮ እንደሆነ ማወቁ አስፈላጊ በመሆኑ በፍታብሔር ሕጉ እና ከሰበር ውሳኔ አንፃር የተመለከተውን የይርጋ መነሻ ጊዜ እንደምከተለው በጽሑፌ ጠቅሻለሁኝ‼

ይርጋ መቆጠር የሚጀምርበት ጊዜ

የይርጋ ቀን መቆጠር የሚጀምረው ግዴታውን ለመጠየቅ ተገቢ ከሆነው ወይም ውሉ የሚሰጠው መብት ከተሰራበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ የሥራ ውል የተቋረጠበትና የስንብት ደብዳቤ የተሰጠበት ቀን ከተለያየ ይርጋ መቆጠር የሚጀምረው ደብዳቤው ለሠራተኛው ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 94931 ቅጽ 16፣ ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1846
በፍትሐ ብሔር ስነ-ስርዓት ህጉ የሚገኙት የጊዜ ገደቦች አቆጣጠር የሚመራው በፍትሐ ብሔር ህግ ባሉት የጊዜ አቆጣጠር ደንቦች ነው፡፡ ጉዳዩ በሌለበት ታይቶ ውሳኔ የተሰጠበት ወገን ውሳኔው እንዲነሳለት በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 78/1/ መሰረት በአንድ ወር ውስጥ የሚያቀርበው ጥያቄ የአንድ ወር ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ውሳኔ መሰጠቱን ከተረዳበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ቀን ለይርጋው ጊዜ መቆጠር መነሻ አይሆንም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 76601 ቅጽ 13፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 78/1/
በወራሾች መካከል ውርስ እንዲጣራ አቤቱታ መቅረብ ያለበት በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሲሆን ይህም ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው አንደኛው ወራሽ የውርሱን ንብረት በእጁ ካደረገበት እንጂ ስመ ሀብቱን በስሙ ካዞረበት ጊዜ ጀምሮ አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 52407 ቅጽ 11፣ ፍ/ህ/ቁ. 1000/1/
ከውርስ ሃብት ጋር በተያያዘ ወራሽ የሆነና አካለ መጠን ያልደረሰ ሰው ላይ የይርጋ ጊዜ ሊቆጠር የሚገባው አካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ አንስቶ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 57114 ቅጽ 11
ይዞታን አስመልክቶ ከሚነሳ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ ጋር በተያያዘ ተፈፃሚ የሚሆነው የይርጋ ጊዜ መቆጠር ያለበት አቤቱታ አቅራቢው የይዞታ መብቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ከሚመለከተው አካል ካገኘበት ቀን ጀምሮ እንጂ አቤቱታ የቀረበበት ድርጊት መፈፀም ከጀመረበት ዕለት አይደለም፡፡ ሰ/መ/ቁ. 60392 ቅጽ 11፣ ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1140፣ 1149፣ 1146/1/፣ 1144/2/.

ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ስራ ካስቀጠሯቸው ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ምን ያህል መቁረጥ ይችላሉ በሚለው አጭር ግንዛቤ መያዝ ግድ ይላል።በአገር ውስጥ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ስለሚሰጥበት...
29/07/2022

ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ስራ ካስቀጠሯቸው ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ምን ያህል መቁረጥ ይችላሉ በሚለው አጭር ግንዛቤ መያዝ ግድ ይላል።

በአገር ውስጥ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ስለሚሰጥበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 45/2013 አንቀፅ 33

የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ከአገልግሎት ተጠቃሚ ድርጅት ጋር በሚፈፅመው የአገልግሎት ውል ስምምነት ውስጥ ከተመለከተው ጠቅላላ ክፍያ ላይ ለሠራተኛው የሚከፈለው ደመወዝ ከሰማንያ በመቶ (80%) ማነስ የለበትም:: ይህ ማለት ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ስራ ካስቀጠሯቸው ሰራተኞች ላይ የሚቆርጡት ደመወዝ ከሰራተኛው ወርሃዊ ደመወዝ ከ20 በመቶ (20%) መብለጥ የለበትም ይላል::

🚨የአክሲዮን ማኀበር እና የኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ልዩነት ⁉️                                        (S.C vs PLC)1/  #አክሲዮን ማህበርየአክሲዮን ማ...
26/07/2022

🚨የአክሲዮን ማኀበር እና የኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ልዩነት ⁉️
(S.C vs PLC)
1/ #አክሲዮን ማህበር

የአክሲዮን ማህበር ማለት ዋናው ገንዘቡ ወይም ካፒታሉ አስቀድሞ ተወስኖ በአክሲዮን የተከፋፈለና ለዕዳው ንብረቱ ብቻ ዋስ የሆነ ማህበር ነው፡፡ ይህም ማለት አባላት አስቀድሞ ተወስኖ የተከፋፈለ አክሲዮን በመግዛት የንግድ ማህበሩ ባለቤት የሚሆኑበት ሲሆን ማህበሩ በሚያጋጥመው ማናቸውም አይነት አዳ እያንዳንዱ አባል ኃላፊነት ሊወስድ የሚችለው በማህበሩ ላይ ባለው ካፒታል መጠን ብቻ ነው ማለት ነው፡፡

የአክሲዮን ማህበር አባላት ቢያንስ አምስት መሆን ያለባቸው ሲሆን የመነሻ ካፒታሉም በሃምሳ ሺህ ብር በታች መሆን እንደሌለበት የንግድ ህጉ ላይ ተመልክቷል፡፡

መስራች አባላት ለሶስተኛ ወገኖች ለማህበሩ መቋቋም ለገቡባቸው ግዴታዎች በአንድነት ሳይከፋፈል ያለወሰን ሃላፊዎች ሲሆኑ የማኀበሩም መቋቋም የሰዎች ወይም የአባላት ማንነት ላይ ሳይሆን በኩባንያው ውስጥ የሚገባውን ገንዘብ ከግምት በማስገባት ነው፡

?? #የአክሲዮን ማኀበር ጠቀሜታ

ኃላፊነቱ የተወሰነ መሆኑ፡- እንደ ግለሰብ ነጋዴና የሽርክና ማህበር ባለአክሲዮኖች በማህበሩ ላይ ካላቸው ድርሻ በላይ በእዳ ሊጠየቁ አይችሉም፡፡

የአክሲዮን ባለቤቶችና በድርጅቱ ሥራ አመራር የተለያዩ መሆኑ፡- የአክሲዮን ማህበር የአክሲዮን ባለቤቶችና የድራጅቱ ሥራ አመራር የተለያየ በመሆኑ ድርጅቱ የተሻለ ብቃት ባላቸው ሙያተኞች ይመራል፡፡

የአክሲዮን ድርሻን ወይም ባለቤትነትን በቀላሉ ከአንዱ ወደ አንዱ ማስተላለፍ ይቻላል

የአክሲዮን ማህበራት ያልተገደበ የጊዜ ቆይታ ያላቸው መሆኑ፡- የአክሲዮን ማህበራት ህልውና እንደ ግለሰብ ነጋዴና የሽርክና ማህበር በጥቂት ግለሰቦች ላይ የተወሰነ ሳይሆን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ባለአክሲዮኖች ሊኖሩት ስለሚችሉና የአክሲዮን ዝውውር የተፈቀደ በመሆኑ የንግድ ድርጅቱ ህልውና በቀለሉ አደጋ ላይ ሊወድቅ አይችልም፡፡

በህግ የሰውነት መብት ያለው መሆኑ፡- በስሙ የመክሰስ የመከሰስ፣ ንብረት የመያዝ፣ የመበደርና የመሳሰሉትን መብቶች አንዲያገኝ ያስችለዋል፡፡

ካፒታሉን ለማሳደግ ቀላል መሆኑ፡- የአክሲዮን ማህበራት የአክሲዮን ባለቤትነት የሚሸጋገር በመሆኑ፣ ኃላፊነቱ የተወሰነ በመሆኑና የቢዝነስ ዘመኑ ያልወሰነ በመሆኑ ካፒታሉን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን ይፈጥርለታል፡፡ የአክሲዮን ማህበራት ካፒታላቸውን ለማሳደግ ከፈለጉ በቀላሉ አዳዲስ አክሲዮኖችን ለገበያ ማቅረብና አዳዲስ ኢንቨስተሮችን መሳብ ይችላሉ፡፡

#የአክሲዮን ማኀበር ጉዳት

የጽሁፍና የሪኮርድ ሥራዎች የሚበዙበት መሆኑ፡– የአክሲዮን ማህበራት የመመስረቻ ሰነድ /Article of incorporation or charter/ የሚያስፈልገው ሲሆን ሰነዱ ከሌሎች ማህበራት በተለየ መልኩ በርካታ ጉዳዮችን ያካተተ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አመታዊ ሪፖርት፣ የባለአክሲዮን መረጃዎች፣ የባለአክሲዮን ስብሰባዎች ቃለጉባኤ፣ የቦርድ አመራሮች ቃለጉባኤ ወዘተ.. ሰነዶችን ማደራጀትና መያዝን ይጠይቃል፡፡

ሁለት ጊዜ ግብር የሚከፍሉ መሆናቸው፡– የአክሲዮን ማህበራት በራሳቸው ህጋዊ የሰውነት መብት ያላቸው በመሆኑ ግብር የመክፈል ግዴታ ሲኖርባቸው ካገኙት ትርፍ ባለድርሻ የሆኑ ባአክሲዮኖችም ካገኙት ገቢ ላይ ግብር የሚከፍሉ በመሆናቸው ግብር የሚታሰበው ሁለት ጊዜ ይሆናል፡፡

የአክሲዮን ማህበራትን ለማደራጀት በርካታ ሂደቶችን ማለፍ የሚጠበቅብን በመሆኑ ብዙ ጊዜንና ወጪን የሚጠይቁ መሆናቸው፡፡

የባለ አክሲዮኖች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ በእነሱ መካከል አለመግባባትና ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ማዕቀፎች በደንብ ሊጤኑ ይገባል።

ብሩክ አሰፋ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ

የውርስ ሀብት ክፍፍልን ስለ ማፍረስበፍትሀ-ብሄር ሕግ ቁጥር 1102-1108 ውርስ ክፍፍል ሊፈርስ የሚችልባቸው ምክንያቶች ተመልክተዋል፡፡ ለምሳሌ የተረሱ ንብረቶችን በተመለከተ የውርስ ክፍፍሉ...
25/07/2022

የውርስ ሀብት ክፍፍልን ስለ ማፍረስ

በፍትሀ-ብሄር ሕግ ቁጥር 1102-1108 ውርስ ክፍፍል ሊፈርስ የሚችልባቸው ምክንያቶች ተመልክተዋል፡፡ ለምሳሌ የተረሱ ንብረቶችን በተመለከተ የውርስ ክፍፍሉ ከተደረገ በኋላ በክፍያ ውስጥ ያልገቡ በውርሱ ንብረት ውስጥ ገብተው የሚቈጠሩ አዲስ ሀብቶች የተገኙ እንደሆነ በነዚሁ አዲስ ንብረቶች መጠን አዲሰ የክፍያ ሥርዐት መፈጸም እንደሚያስፈልግ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1103. ያስረዳል፡፡ በሌላ በኩል ይህ በክፍያ ውስጥ ሳይገባ ቀርቶ የተገኘው አዲስ ንብረት ከወራሾቹ በአንዱ እጅ እንደነበረና ይህንኑ ደብቆት የነበረው በመጥፎ ልቡና ከሆነ በዚህ ዐይነት ከደበቀው ንብረት የሚደርሰውን ድርሻ ያጣል፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1104.

በተጨማሪም የአንዳንድ ንብረቶች ዋጋ በተሳሳተ ሁኔታ በመገመቱ ምክንያት የክፍያው ተጠቃሚ ከሆነው ወራሽ አንዱ ሊደርሰው ከሚገባው ከሦስት ሩብ በታች ደርሶት እንደሆነ በዚሁ ባለመብት በሆነው ወራሽ ጠያቂነት የክፍያው ሥርዐት እንደገና እንዲቃና ይደርጋል፡፡ ነገር ግን የውርስ ክፍፍሉ እንዲስተካከል/እንዲቃና የሚቀርበው ጥያቄ ውርሱ በተከፋፈለ በ3 ዓመት ውስጥ ያልቀረበ እንደሆነ ተቀባይነትን ያጣል፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1106

ብሩክ አሰፋ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ

የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት ሥራ ስለሚፈቀድበት፣ የክፍያው መጠን እና ማካካሻ እረፍት ስለሚሰጥበት ሁኔታ የወጣ መመሪያ ቁ. 921/2014የትርፍ ሰዓት ክፍያ ስለሚፈቀድባቸው ሁኔ...
24/07/2022

የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት ሥራ ስለሚፈቀድበት፣ የክፍያው መጠን እና ማካካሻ እረፍት ስለሚሰጥበት ሁኔታ የወጣ መመሪያ ቁ. 921/2014

የትርፍ ሰዓት ክፍያ ስለሚፈቀድባቸው ሁኔታዎች፣ ስለክፍያው መጠን እና የማካካሻ እረፍት ስለሚሰጥበት ሁኔታ በፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁ. 1064/2010 አንቀጽ 35 መሠረት መመሪያ እንደሚወጣ መደንገጉ ይታወቃል።

በመሆኑም የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጁ አንቀጽ 97 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የተዘጋጀውን የአፈፃፀም መመሪያ ያወጣ ሲሆን ከነሐሴ 1፣ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።

❗የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮችን በሚመለከት 🇪🇹👉 የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮች በትግራይ ክልል ካከናወኑት የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የሚፈለ...
21/07/2022

❗የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮችን በሚመለከት 🇪🇹

👉 የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮች በትግራይ ክልል ካከናወኑት የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የሚፈለግባቸው የግብር እዳ መኖር አለመኖሩን ማረጋገጥ ስለማይቻል : ንብረት መሸጥን ሳይጨምር [የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት : የተሽከርካሪ/የመሳሪያዎች አመታዊ ምርመራ ማድረግ : ብድር መውሰድ እና በጨረታ መሳተፍ] የሚያስችል ጊዜያዊ የታክስ ክሊራንስ ሰርተፍኬት ከገቢዎች ሚኒስቴር እንዲያገኙ ይደረጋል::

👉 በአሁኑ ወቅት በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የምትገኙ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮች በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ካከናወናችሁት የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ ለክልሉ መንግስት ገቢ ልታደርጉ ሲገባ ያልከፈላችሁት ግብር ካለ ገቢያችሁን ለገቢዎች ሚኒስቴር ማሳወቅ ያለባችሁ ሲሆን የገቢዎች ሚኒስቴር ግብሩን በአደራ ሰብስቦ ለዚሁ አላማ በሚከፈት የአደራ የባንክ ሂሳብ ተቀማጭ የሚያደርግ ይሆናል::

👉 የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብር ከፋዮች የስራ ቦታቸውን አሁን ወደሚገኙበት አድራሻ ለመቀየር ከፈለጉ ቀደም ሲል በወሰዱት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በሚፈልጉት አድራሻ ምዝገባ በማከናወን የንግድ ስራቸውን እንዲቀጥሉ የሚደረግ ይሆናል::

19/07/2022

የደቡብ ምዕራብ ክልል ከተመሰረተ ወዲህ ያወጣቸውን ሕጎች ደንብ ና መመሪያዎች ለማግኘት ጥረት ያደረኩ ቢሆንም አላገኘሁም።

ስለ ውል ማፍረስና እና ውል መሠረዝ በፍታብሔር ሕጉ ድንጋጌ እና ከሰበር  የተሰጠ ውሳኔ  አንጻር ሲታይ ውል ማፍረስ/Invalidation of Contract/የውል ማፍረስ ከውል አመሠራረት ጋ...
16/07/2022

ስለ ውል ማፍረስና እና ውል መሠረዝ በፍታብሔር ሕጉ ድንጋጌ እና ከሰበር የተሰጠ ውሳኔ አንጻር ሲታይ
ውል ማፍረስ/Invalidation of Contract/
የውል ማፍረስ ከውል አመሠራረት ጋር ተያይዞ የሚነሳ ሲሆን ውሉ ከአመሰራረቱ በህጉ የተመለከቱትን ሁኔታዎች ባለሟሟላቱ ግድፈት ያለበት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ለምሳሌ ከተዋዋዮቹ አንዱ ከ18 አመት በታች ከሆነ የታወቀ የአዕምሮ ችግር ያለበት ሰው ከሆነ ወይም ውሉን ሲፈፅም በመገደድ ወይም በመጭበርበር ወይም በስህተት ከሆነ ውሉን የፈፀመው ውሉ ሊፈርስ ይችላል፡፡ ሕጉ ያስቀመጠውን የውል አፈፃፀም ስርዓት አለመከተል ውሉን ፈራሽ ሊያደርገው ይችልል፡፡
ውል መሰረዝ/cancellation of Contract/
በሌላ በኩል የውል መሰረዝ ጉዳይ ከውል አመሰራረት ችግር የሚነሳ ሲሆን ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታውን ካለመወጣት የሚመነጭ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32299
ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንደኛው እንደ ውሉ ባለመፈጸሙና የውሉን ግዴታ በመጣሱ ከተዋዋዩ ወይም በፍርድ ቤት ውሉን ወይም በውሉ የተቋቋሙትን ግዴታዎች ቀሪ ማድረግ ውል መሠረዝ ይባላል፡፡ የውል መሠረዝ ምክንያት ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታን ከመፈፀምና ካለመፈፀም ጋር ተያይዞ የሚከሰት ነው፡፡ ውሉን የመሰረዝ ፍላጎት ያለው ወገን የውል ግዴታ ባለመፈፀም የተነሳ ከሕግ ወይም ከውሉ ከራሱ ባገኘው መብት ተጠቅሞ ውሉን ሊሰረዝ ይችላል፡፡ የውል ይሰረዝልኝ ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎች በሕጉ አግባብ የሚስተናገዱ ስለመሆኑ የፍትሐብሔር ሕግ ቁ. 1784 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ያስገነዝባሉ፡፡ ሰ/መ/ቁ. 32299

Address

Bonga

Telephone

+251938489815

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Biruk Assefa Legal Service/ብሩክ አሰፋ የሕግ አገልግሎት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category