የአብክመ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድቤቶች ዳኞች እና ዐቃቢያን ህግ ድምፅ.""".

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahrdar Giyorgis
  • የአብክመ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድቤቶች ዳኞች እና ዐቃቢያን ህግ ድምፅ.""".

የአብክመ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድቤቶች ዳኞች እና ዐቃቢያን ህግ ድምፅ.""". Justice : the quality of being just, impartial, or fair.

10/06/2026

>> የፍርድ ቤት ዉሳኔዎችን እና ትዕዛዞችን ያለመፈፀም የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት

>> ‎ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳን በተመለከተ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ
05/06/2026

>> ‎ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳን በተመለከተ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በወረዳው ለተቋቋሙ የባህል ፍርድቤቶች ዳኞች እና ጸሀፊዎች ያዘጋጀው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እና ስራ ማስጀመሪያ መድረክ መካሄድ ጀመረ ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨...
05/06/2026

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በወረዳው ለተቋቋሙ የባህል ፍርድቤቶች ዳኞች እና ጸሀፊዎች ያዘጋጀው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እና ስራ ማስጀመሪያ መድረክ መካሄድ ጀመረ ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በተሁለደሬ ወረዳ ለተቃቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ጸሀፊዎች የአቅም ማጐልባቻ ስልጠና እና የስራ ማስጀመሪያ መድረክ መካሄድ ጀመረ ።

በወረዳ አስተዳደሩ በ UNDP peace support facility የበጀት ድጋፍ ከግንቦት 28-30/2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየውን የስልጠና መድረክ የተገኙት የተሁለደሬ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጌታሁን የስልጠናው ተሳታፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችን በእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ተቀብለዋል ።

፨፨፨

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መድረኩን በንግግር የከፈቱ ሲሆን ፕሬዝዳንቷ በንግግራቸው መደበኛ የዳኝነት ስርአት ከመዘርጋቱ አስቀድሞ ማህበረሰቡ የዳበሩ የግጭት መፍቻ ስርአቶችን ዘርግቶ ለበርካታ ዘመናት ያለመግባባቶችን በመፍታት ህግን እና ሰላምን ሲያጸና መቆየቱን አውስተው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና መንግስት ለአማራጭ የሙግት መፍቻ ስርአቶች ትኩረት በመስጠት አባት አደር የባህል ፍርድ ቤቶች የህግ ማእቀፍ ኑራቸው የእውቅና እና የማቋቋሚያ አዋጅ እንዲወጣ በማድረግ እና አዋጁንም ማስተግበሪያ መመሪያ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ተገብቷል ብለዋል።

፨፨፨

በዚሁ አግባብ በዞናችን ሁሉም ወረዳዎች የባህል ፍርድ ቤቶችን የማቋቋም ፣ዳኞችን የማስመረጥ፣ጸሀፊዎችን የመመደብ እና የማስቻያ ቦታዎችን የማመቻቸት ስራ በተጠናከረ ሁኔታ ተሰርቷል ፤ እነዚህ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለማህበረሰቡ በአነስተኛ ወጭ እና በአጭር ጊዜ ተደራሽ የሆነ ዳኝነት ከመስጠታቸው ባሻገር በመደበኛ ፍርድ ቤቶች እየተፈጠረ ያለውን የስራ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንስ ይሆናል ብለዋል።

፨፨፨

አክለው የተሁለደሬ ወረዳ አስተዳደርም በባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን በማስመረጥ እና በስልጠና ሂደቱ ያሳየውን ድጋፍ በቀጣይ የማስቻያ ቦታዎችን በማመቻቸት እና አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች እና የጽህፈት መሳሪያዎችን በመደገፍ ረገድ አጋርነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

፨፨፨

ሰልጣኝ ዳኞችም ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀት በተግባር ከዳበረው ልምዳቸው ጋር በማጣመር የተሻለ የዳኝነት አገልግሎት በመስጠት በተለይም የሴቶች እና ህጻናትን መብት በማስከበር የሀገር ሰላምን በበለጠ እንዲያጸኑ አሳስበዋል።

፨፨፨

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ በበኩላቸው በወረዳው የባህል ፍርድ ቤቶችን በማቋቋም ተግባር ሽማግሌዎችን ከማስመረጥ ሂደት ጀምሮ ለስልጠና የሚያስፈልግ በጀትን በመደገፍ የወረዳ አስተዳደሩ ላሳየው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። የስልጠና ተሳታፊ ሽማግሌዎች እና ጸሀፊዎችም ማህበረሰቡ የሰጣቸውን ሀላፊነት ተቀብለው በበጐ ፈቃደኝነት አገልግሎት ለመስጠት ባሳዩት ቁርጠኝነት እና ፍርድ ቤቱ ያደረገላቸውን ጥሪ አክብረው በስልጠና መድረኩ በመገኘታቸው አክብሮታቸውን እና ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እያደረገላቸው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል።

፨፨፨

ትኩረቱን በዋናነት በአማራ ክልል የባህል ፍ/ቤቶችን ለመቋቋምና እውቅና ለመሰጠት በወጣው አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህንን አዋጅ ለማሰፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ላይ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባዘጋጃው የስልጠና ማንዋል ያደረገውን ስልጠና የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የሆኑት የተከበሩ መስጠት ጀምረዋል።

፨፨

ቀደም ባሉት ሳምንታት የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በሀይቅ ከተማ አሰተዳደር ለተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ጸሀፊዎች የስልጠና እና የስራ ማስጀመሪያ መድረክ በደማቅ ሁኔታ ማዘጋጃቱ የሚታወስ ነው።

© ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም (ሀይቅ) የደ/ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት

>> የህግ ውይይት በደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት ተካሄደ
26/05/2026

>> የህግ ውይይት በደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት ተካሄደ

ዒድ አል ዓድሐ ሙባረክ!መልካም በዓል!
26/05/2026

ዒድ አል ዓድሐ ሙባረክ!
መልካም በዓል!

⚖️ የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ለባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞችና ፀሐፊዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እና የሥራ ማስጀመሪያ መድረክ አደረገግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ...
25/05/2026

⚖️ የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ለባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞችና ፀሐፊዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እና የሥራ ማስጀመሪያ መድረክ አደረገ

ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት
፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤ //// //// ፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤

የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ከከተማ አስተዳደሩ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ፣ በከተማዋ በሚገኙ 20 ቀበሌዎች ለተዋቀሩ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሐፊዎች ያዘጋጀው የአቅም ግንባታ ሥልጠና እና የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል፡፡
ከግንቦት 13 እስከ 14 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በቆየው በዚህ ሥልጠና ላይ 100 የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች፣ 20 ጸሐፊዎች እና 5 አበጋሮች ተሳትፈዋል፡፡
📌 የመድረኩ ክብር እንግዳ የነበሩት የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓቶችን ማጠናከር በክልሉ መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ገልጸዋል። አፈ-ጉባኤዋ አክለውም፣ የባህል ፍርድ ቤቶች በማቋቋሚያ አዋጁ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የሴቶች እና የሕፃናትን መብት ማስከበር ላይ ልዩ ትኩረት አድርገው መሥራት እንዳለባቸው በአጽንዖት አሳስበዋል።

📌የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ዳኛቸው በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የባህል ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሕግ ሥርዓት ጎን ለጎን ፍትሕን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ያላቸውን የማይተካ ሚና አብራርተዋል።

📌የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ምትኬ ወርቁ በበኩላቸው፣ የሃይማኖት እና የባህል ፍርድ ቤቶች በሕገ-መንግሥቱ ዕውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ጠቅሰው፣ የክልሉ መንግሥት ከሕግ ማዕቀፍ ማውጣት ጀምሮ ተቋማቱን በማደራጀት ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

📌 የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ተሾመ በላይ እንደገለጹት፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሕግ ሥርዓት ጎን ለጎን የፍትሕ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። እነዚህ ተቋማት ማኅበረሰባዊ አለመግባባቶችን በውይይትና በዕርቅ በመፍታት፣ ሕዝባዊ ትስስርና አንድነት እንዳይላላ በማድረግ ረገድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን አብራርተዋል። በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ይህ ፕሮግራም እንዲሳካ ላደረገልን የገንዘብ ድጋፍ ፍርድ ቤቱ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ አክለውም የተዘጋጀው ሥልጠና ዋና ዋና ዓላማዎች ጠቁመዋል፦
⚖️ የሕግ ግንዛቤን ማሳደግ፦ በቀበሌ ደረጃ የተዋቀሩ የባህል ዳኞች ያላቸውን የሕግ እውቀት ይበልጥ ማበልጸግ፤
⚖️ አሠራርን ማዘመን፦ የሰነድ አያያዝ እና የፀሐፊነት ተግባራትን በዘመናዊና ስልታዊ መልኩ እንዲመሩ ማስቻል፤
⚖️ ቅንጅታዊ አሠራርን መፍጠር፦ ከመደበኛው የፍትሕ አካላት ጋር የተናበበና የተቀናጀ የሥራ ግንኙነት መመሥረት።
ይህ በቀበሌ ደረጃ የሚከናወን የዳኝነት ሥርዓት የማኅበረሰቡን እንግልት፣ ጊዜና ወጪ ከመቀነሱም በላይ፣ ጉዳዮች በአጭር ጊዜና በሰላማዊ መንገድ ተቋጭተው ለከተማዋ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ሁሴን አህመድ በበኩላቸው፣ ምክር ቤቱ የባህል ፍርድ ቤቶችን ወሳኝ ምሰሶነት በመረዳት የበጀትና መሰል ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝና ወደፊትም ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ስልጠናውን የሰጡት የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ በሆኑት አቶ መንገሻ እያሴ ሲሆኑ

⚖️ የባህል ዳኞች የሕግ ግንዛቤያቸውን እንዲያሳድጉ፣
⚖️ የሰነድ አያያዝ እና የፀሐፊነት ተግባራትን በዘመናዊ መልኩ እንዲመሩ፣
⚖️ ከመደበኛው የፍትሕ አካላት ጋር ተቀናጅተውና ተናበው መሥራት እንዲችሉ ለማስቻል እንደሆነ አስገንዝበዋል።

የሥልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፣ የተሰጠው ሥልጠና የሕግ ግንዛቤያቸውን እንደሚያሳድግላቸው እና ህብረተሰቡን ያለአስፈላጊ እንግልት እና ወጭ እንደሚያስቀሩ ገልጸው፤ በቀጣይ አገልግሎታቸው በገለልተኝነት፣ ያለአድልዎ፣ ዕርቅን በማስቀደም ማኅበረሰባቸውን በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።© #ኮምቦልቻ

ይህ የቴሌግራም ቻናል የኮምቦልቻ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በዚህ ቻናል ፡- ✅ ፍርድ ቤቱ የሚያከናውናቸውን አስተማሪ ፣ የሚሰሩ ስራዎች አስቼኳይና አስፈላጊ መረጃዎችን የሚጋሩበት...

የወረዳ ፍርድ ቤቶች በአካባቢያቸው የሚገኙ የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎችንና ጸሐፊዎችን ሥልጠና በመስጠት ወደ ሥራ እያስገቡ ይገኛሉ ⚖️🌍(የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)የወረዳ ፍርድ ቤ...
25/05/2026

የወረዳ ፍርድ ቤቶች በአካባቢያቸው የሚገኙ የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎችንና ጸሐፊዎችን ሥልጠና በመስጠት ወደ ሥራ እያስገቡ ይገኛሉ ⚖️🌍
(የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)

የወረዳ ፍርድ ቤቶች በአካባቢያቸው የሚገኙ የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎችንና ጸሐፊዎችን በማሰልጠን የሥራ ማስጀመር መርሀግብር እያከናወኑ ይገኛሉ።

የባሕል ፍርድ ቤቶች ማለት በሰዎች መካከል አይቀሬ የሆኑ አለመስማማቶች በሚፈጠሩበት ጊዜ የአካባቢውን ወግና ባሕል መሠረት አድርገው እርቅ የሚያወርዱ ኅብረተሰቡ ራሱ በባለቤትነት መርጦ የሚሰይማቸው አማራጭ የፍትሕ መስጫ ተቋማት ናቸው።
እነዚህ የባሕል ፍርድ ቤቶች ለኅብረተሰቡ ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው፦

✅ፍትሕን ወደ ቀዬው ማምጣት፦ ለማኅበረሰቡ ውድ ጊዜን፣ ወጪንና እንግልትን የሚቀንስ የፍትሕ ተደራሽነት መሣሪያ ነው።

ቀላልና ተደራሽ የፍትሕ አገልግሎት፦ ለክልሉ ማኅበረሰብ ተደራሽ፣ ወጪ ቆጣቢ እና ቀለል ያለ ሥነ-ሥርዓት የተከተለ የፍትሕ አገልግሎት እንዲያገኙ ያደርጋል።

✅ዕርቅን መሠረት ያደረገ ማኅበራዊ ትስስር፦
በይቅርታና በዕርቅ ግንኙነቶችን በመጠገን ዘላቂ ሰላምን ያሰፍናሉ።

✅አገር በቀል እውቀትን ማሳደግ፦ የማኅበረሰባችንን ጥበባዊ እሴቶችና እውቀቶች ለፍትሕ አገልግሎት ማዋል፣ መፍትሄውም በተጨባጭ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ያደርጋል።

ላቂ ሰላም፦ የሕግ ውሳኔ አሸናፊና ተሸናፊ ሲፈጥር፣ የባሕል ፍርድ ቤቶች ግን በዕርቅ የቆሰለ ግንኙነትን ይተካሉ፤ ማኅበራዊ ትስስርን ያጠናክራሉ።
ማኅበረሰቡ በራሱ የሕይወት ተሞክሮ እና እሴቶች ላይ የተመሠረተ ፍትሕን እንዲያገኝ የሚያስችል በመሆኑ የፍትሕን ተቀባይነት ከፍ ያደርገዋል።

✅ የጋራ ተሳትፎ፦
የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች የሚመረጡት በራሱ ማኅበረሰቡ ተሳትፎ በመሆኑ በባሕል ፍርድ ቤት ሥርዓቱ ላይ ያለውን የሕዝብ እምነትና ባለቤትነት ይጎለብታል።

መሠረታዊ መርሆዎች📜✨
1️⃣ ፈቃደኝነት
የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች ጉዳዮችን የሚመለከቱት ግራ-ቀኙ ወገኖች ሳይገደዱ በነፃ ፍላጎታቸው ተስማምተው በሚያቀርቡት መሠረት ነው።

2️⃣ ሰብአዊ መብትና እኩልነት፦

ባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ውሳኔ የሚሰጡት
የሴቶችን እኩልነት በማረጋገጥ፣ ከአድልዎ የጸዳ፣ በዘር፣ በሃይማኖትና በሀብት ልዩነት በማይፈጥር ሁኔታ ነው።

ወረዳ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢያቸው የባሕል ፍርድ ቤት   ሽማግሌዎች እና ጽሀፊዎች የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና በመስጠት አገልግሎቱን በይፋ በማስጀመር ላይ ናቸውባህርዳር ፣ ግንቦት 17/2018 (...
25/05/2026

ወረዳ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢያቸው የባሕል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች እና ጽሀፊዎች የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና በመስጠት አገልግሎቱን በይፋ በማስጀመር ላይ ናቸው

ባህርዳር ፣ ግንቦት 17/2018 (የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጥናት ለለያቸው 15 አማራጭ ያለመግባባት መፍቻ ዘዴዎች እውቅና በመስጠት የክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች እንዲሆኑ መወሰኑ ይታወቃል።

ለባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና ከሰጠበት እለት ጀምሮ የባሕል ሽማግሌዎችን በማስመረጥ እና ስራ በማስጀመር ሂደት ላይ የሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ በእስካሁኑ ሂደት 1149 በሚሆኑ ቀበሌዎች ላይ የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሽማግሌዎች ያስመረጠ ሲሆን፣ ሽማግሌዎችን ያስመረጡ ወረዳ ፍርድ ቤቶች አስፈላጊውን ስልጠና በመስጠት የባሕል ፍርድ ቤቶችን በይፋ ስራ በማስጀመር ላይ ናቸው።

በባህርዳር እና አካባቢዋ፣ በደቡብ ወሎ ዞን እና በሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ስር የሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ለባሕል ፍርድ ቤቶች ሽማግሌዎችና ጽሀፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ ላይ ናቸው።

የባሕል ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡ ወጪ፣ ጊዜ እና ጉልበት ቆጣቢ አገልግሎት በአቅራቢያው እንዲያገኝ ያላቸውን ከፍተኛ ጠቀሜታ በመረዳት ሌሎችም የወረዳ ፍርድ ቤቶች ሽማግሌዎችን እና ጽሀፊዎችን በመምረጥ እና አስፈላጊውን የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ፈጥነው ስራ እንዲጀምሩ ለማድረግ የየአካባቢው ወረዳ ፍርድ ቤቶች፣ ነዋሪዎች እና ሌሎች አጋርና ባለድርሻ አካላት የተለመደ ስራቸውን እና ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤታችን ያሳስባል።© የአብክመ ጠቅላይ ፍርድቤት

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በሃይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ ፤==========//============ግንቦት 17/2018 ዓ.ም...
25/05/2026

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በሃይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ ፤
==========//============
ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (ሀይቅ )
**********************
በሀይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋመ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ከUNDP peace support Facility በተገኘ የበጀት ምንጭ ከግንቦት 17-19/2018 ዓ.ም ለተከታይ ሶስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በዛሬው ቀን ተጀምሯል ።

ስልጠናውን የተሁለደሬ ወረዳ ፍ/ቤት ኘሬዝደንት አቶ ደረጀ ደምሴ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት ሲሆን የተሁለደሬ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ
አህመድ መሀመድ ለተሳታፊዎች መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የሀይቅ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ክንዱ ዓሊ እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

ስልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ባዘጋጀው የስልጠና ማንዋል መሰረት የተሁለደሬ ወረዳ ፍ/ቤት የፍትሐብሔር ዳኛ የሆኑት አቶ ዑስማን መሀመድ ናቸው ።

የሚሰጠው ስልጠና የአብክመ የባህል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህን አዋጅ ለማስፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ላይ ያተኮረ በመሆኑ ስራቸውን ለመጀመር የሚያስችል በቂ ግብዓት የሚያገኙበት ይሆናል።© የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድቤት

  ልምድ! 🎉 👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈  #በዳኝነትና በፍትህ መዋቅር ውስጥ ለበርካታ ዓመታት በታማኝነትና በብቃት ሲያገለግሉ የቆዩት  #አቶ ሀሩን ደሳለኝ ያካበቱትን ሰፊ የችሎት ልምድ፣...
23/05/2026

ልምድ! 🎉

👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈👈

#በዳኝነትና በፍትህ መዋቅር ውስጥ ለበርካታ ዓመታት በታማኝነትና በብቃት ሲያገለግሉ የቆዩት #አቶ ሀሩን ደሳለኝ ያካበቱትን ሰፊ የችሎት ልምድ፣ የአመራር ክህሎትና ጥልቅ የህግ እውቀት ይዘው የጥብቅና እና የህግ ማማከር አገልግሎት ለመስጠት ወደ ጥብቅናው ዓለም በይፋ መቀላቀላቸውን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን።

#አቶ ሀሩን ደሳለኝ በህግ ሙያ የተጓዙበትን የስኬት መንገድ እና ለደንበኞቻቸው የሚሰጡትን አስተማማኝ ዋስትና የሚያሳዩ ዋና ዋና መገለጫዎች፦

🎓

#ከወሎ ዩኒቨርሲቲ በሕገ-መንግስታዊ ህግ (Constitutional Law) የማስተርስ (LL.M) ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ውጤት ያጠናቀቁ ሲሆን፣ Administration of regional state Council Election under Federal system of Ethiopia: Comparative Analysis with Spain and Indian federal system በሚል እርዕስ ሀገራችን አጋጥሟት በነበረው 6ኛ ዙር ምርጫ ላይ በትግራይ እና በፌዴራል መንግስቱ መካከል የተፈጠረውን የምርጫ አስተዳደር ጉዳይ ጋር በተያያዘ የተዋጣለት የምርምር ስራ በመስራት Excellent thesis result በማምጣት የ LLM ድግሪውን በህገመንግስት ያገኘ።

#የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ደግሞ በህግ (LL.B) ከዲላ ዩኒቨርሲቲ በስኬት አጠናቀዋል።

⚖️ #የዳኝነት፣ የአመራር እና የፍትህ አስተዳደር ልምድ

#የክልል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመሆን ፍርድ ቤትን በበላይነት የመምራት፣ የማስተዳደር፣ የሰው ኃይል የመመልመል እና ስትራቴጂካዊ የሥራ ዕቅዶችን የማስፈጸም ከፍተኛ የአመራር ሚና ተወጥተዋል።

#የፍትሐብሔር እና የወንጀል ጉዳዮች አስተባባሪ እና ዳኛ በመሆን በተለያዩ የፍርድ ቤት የሥራ ክፍሎችን በውጤታማነት አስተባብረዋል።

#በአማራ ክልል የህግ ምርምር ኢንስቲትዩቱ የ 9ኛ ዙር ሰልጣኝ እና ከክፍል ሰልጣኞች 1ኛ ደረጃን ከጠቅላላ ሰልጣኞች 2ኛ ደረጃን በመያዝ በከፍተኛ ውጤት እና የእውቅና ሽልማት የተመረቀ፣

#በአማራ ክልል የህግ ምርምር ኢንስቲትዩት "ፍትሕ መፅሄት" ላይ የምርምር ስራ ያሳተመ

#የሰሜን ወሎ ዞን የዳኞች አስተዳደር ንዑስ ጉባኤ እና የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር የማዕከላዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።

#የብዙ ዓመታት የችሎት ተሞክሮ፣ የፍርድ ቤቶች የአመራር ጥበብ እና ጥልቀት ያለው የሕግ ምርምር እውቀት ያላቸው አቶ ሀሩን ደሳለኝ፤ መብትና ጥቅማችሁን በህግ አግባብ ለማስከበርና አስተማማኝ የህግ ከለላ ለመስጠት ዝግጁ ናቸው!

#እናንተም ለማንኛውም የህግ ማማከር እና የጥብቅና አገልግሎት በሚከተሉት አድራሻዎች ማግኘት ይችላሉ፦

📞 ስልክ፦ (+251) 945910917

📧 ኢሜይል፦ [email protected]

📍 ዋና አድራሻ፦ ደሴ፣ ወሎ፣ ኢትዮጵያ

Address

Bahrdar Giyorgis

Telephone

0583210017

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአብክመ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድቤቶች ዳኞች እና ዐቃቢያን ህግ ድምፅ.""". posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category