Mulatu Biresaw

Mulatu Biresaw በዚህ ፔጄ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት አስተምህሮዎችና የገዳማትና አድባራት ታሪካቸው ከዚህም በተጨማሪ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ድንቅ የሆኑ ታሪኳ ይቀርባሉ።

ሰአሊለነ ቅድስት
29/04/2026

ሰአሊለነ ቅድስት

.                      📖 ከታች በፎቶ የምትመለከቱት ቤተክርስቲያን ዳዋ ጥሰው፣ጤዛ ልሰው፣ድምፀ አራዊት ታግሰው፣ጸባ አጋንንት ታግሰው፣ደንጊያ ተንተርሰው ለዓለም፣ለሀገር፣ለወገን፣...
25/04/2026

.
📖 ከታች በፎቶ የምትመለከቱት ቤተክርስቲያን ዳዋ ጥሰው፣ጤዛ ልሰው፣ድምፀ አራዊት ታግሰው፣ጸባ አጋንንት ታግሰው፣ደንጊያ ተንተርሰው ለዓለም፣ለሀገር፣ለወገን፣ለፍጥረቱ ሁሉ ከሚጸልዩት ስውራን ቅዱሳን አባቶች ውስጥ በመድኃኔዓለም ፈቃድ ጥንታዊት በሆነችው በወጨፎ ማርያም ገዳም በስተምስራቅ በቤቴልሄም በኩል በመምጣት በዚህችው ታላቅ ገዳም ተደርቦ ይኖር የነበረው የመድኃኔዓለም ፅላት በስተምስራቅ በኩል የራሱ ቦታ ስላለው መጪው ትውልድ ቤተክርስቲያን ሰርቶ የመድኃኔዓለም ፅላት እንደሚገባ በገዳሟ ለሚያገለግሉት ለአንዱ ካህን ትንቢት ከተነገረለት ከ ፵(40) ዓመታት በኋላ ቤተክርስቲያኑ ተሰርቶ የመድኃኔዓለም ፅላት ገብቶ እራሱ መድኃኔዓለም በገቢረ ተዓምራቱ ቦታውን ባርኮ የቀደሰው የመላኩ የቅዱስ ዑራኤል ፅላትና የፃዲኩ የአቡነ ዘርዓብሩክ ፅላት ጭምር ተደርበው ቅዳሴው እየተከበረ የሚገኘው ደብረ ቀራኒዮ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በአገው ግምጃቤት ከተማ በስተምስራቅ በኩል ይገኛል። በዚህችም ቤተክርስቲያን በስፋት የአብነት ትምሀርት እየተሰጠ ይገኛል ከዚህም በተጨማሪ በዚህችው ቅፅረ ቤተክርስቲያን ባዕታቸውን አፅንተው ቤተክርስቲያኗን እያገለገሉ የሚገኙ አበው ወእማት መነኮሳቶች ይገኛሉ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየኝ። ሚያዝያ/17/2018 ዓ/ም በሙላቱ ቢረሳው ተፃፈ

በታላቋ ገዳም በወጨፎ ማርያም ገዳም ስም በተሰየመው የዩቲዩብ ቻናል በመግባት   የሚለውን በመጫን በዘማሪ መሰረት ወርቁ እጅግ ግሩም ድንቅ የሆኑ ያሬዳዊ ጥዑመ ዝማሬዎችን አዳምጡ ።      ...
01/04/2026

በታላቋ ገዳም በወጨፎ ማርያም ገዳም ስም በተሰየመው የዩቲዩብ ቻናል በመግባት የሚለውን በመጫን በዘማሪ መሰረት ወርቁ እጅግ ግሩም ድንቅ የሆኑ ያሬዳዊ ጥዑመ ዝማሬዎችን አዳምጡ ። ሙላቱ ቢረሳው መጋ/፪፫/፪፻፩፰

እናንተ ቡሩካን

ወንጌል ዘዮሐንስ ፭፥፭፦፱ወሀሎ ህየ አሐዱ ብእሲ ዘሠላሳ ወሰመንቱ ዓመት እምዘ ደወየ።በዚያም ከታመመ ሠላሳ ስምንት ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበር።ወኪያሁ ርእዮ እግዚእ ኢየሱስ  ይሰክብ ወአ...
08/03/2026

ወንጌል ዘዮሐንስ ፭፥፭፦፱

ወሀሎ ህየ አሐዱ ብእሲ ዘሠላሳ ወሰመንቱ ዓመት እምዘ ደወየ።

በዚያም ከታመመ ሠላሳ ስምንት ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበር።

ወኪያሁ ርእዮ እግዚእ ኢየሱስ ይሰክብ ወአእመረ ከመ ጐንደየ ውስተ ደዌሁ ወይቤሎ ትፈቅድኑ ትሕየው።

ጌታችን ኢየሱስም ያን ሰው በአልጋዉ ተኝቶ ባየ ጊዜ በደዌ ብዙ ዘመን እንደ ቈየ ዐውቆ፥ “ልትድን ትወዳለህን?” አለው።

ወአወሥአ ውእቱ ድዉይ ወይቤሎ እወ እግዚኦ አላ ሰብአ አልብየ ከመ ሶበ ይትሀወክ ማይ ያውርደኒ ይየደየኒ ውስተ ምጥማቃት ወሶበ ጊዜ እመጽእ አነ ባዕድ ይቀድመኒ ወሪደ።

ድውዩም መልሶ፥ “አዎን ጌታዬ ሆይ፥ ነገር ግን ውኃዉ በተናወጠ ጊዜ ወደ መጠመቂያዉ የሚያወርደኝ ሰው የለኝም፤ እኔ በምመጣበት ጊዜ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል” አለው።

ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ተንሥእ ወንሣእ ዐራተከ ወሑር።

ጌታችን ኢየሱስም፥ “ተነሥና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” አለው።

ወሐይወ ሶቤሃ ውእቱ ብእሲ ወነሥአ ዐራቶ ወሖረ። ወሰንበት አሜሃ ይእቲ ዕለት።

ወዲያውኑም ያ ሰው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ ሄደ፤ ያች ቀንም ሰንበት ነበረች።

እንኳን አደረሳችሁ
02/02/2026

እንኳን አደረሳችሁ

.             ጥር 21 ቀን (አስተርእዮ ማርያም) እመቤታቸን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረፈችበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የእመቤታችንን ዕረፍት በማሰብ ታከብ...
30/01/2026

.

ጥር 21 ቀን (አስተርእዮ ማርያም) እመቤታቸን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረፈችበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የእመቤታችንን ዕረፍት በማሰብ ታከብራለች፡፡ አብ የመረጣት፣ ወልድ የተወለደባት፣ መንፈስ ቅዱስ ያከበራት ማኅደረ መለኮት (የመለኮት ማደሪያ) የከበረች እመቤት ያረፈችበት ዕለት ነው፡፡ ያቺ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ›› ያላት፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ ‹‹የጌታዬ እናት›› ብላ ያመሰገነቻት፣ ክቡር ዳዊት ‹‹ልጄ›› ብሎ የዘመረላት፣ ጠቢቡ ሰሎሞንም ‹‹እህቴ›› ብሎ የተቀኘላት፣ ለወንጌላዊው ዮሐንስ ‹‹እናትህ እነኋት›› የተባለችው የተወደደች እመቤታችን ያረፈችበት ዕለት ነው፡፡

ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝሙር፣ አፈ በረከት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ፣ ደገኛው ቅዱስ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ፣ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በሰዓታት፣ ቅዱሳን መላእክትን በምስጋና የመሰላቸው ቅዱስ ያሬድ በማኅሌት ያመሰገኗት ከንግግርና ከቋንቋዎች ሁሉ በላይ የሆነ ምስጢር የተፈፀመባት እመቤት ያረፈችበት ዕለት ነው፡፡ ዕረፍቷም በመልክአ ማርያም ‹‹ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ፡ ያለመጨነቅና ያለፃእር ከሥጋዋ ለተለየች ነፍስሽ ሰላምታ ይገባል›› እንደተባለው ያለመጨነቅና ያለፃእር ነበር፡፡ ያለ አንዳች መጨነቅ ጌታን የወለደቸው እመቤት ያለ አንዳች መጨነቅ ቅድስት ነፍስዋን ከክብርት ሥጋዋ ተለይቶ በቃለ አቅርነት በዝማሬ መላእክት ጌታችን አሳርጓታል፡፡ እርሷ፡-ሦስት ዓመት በእናት በአባቷ ቤት፣ አስራ ሁለት ዓመት በቤተመቅደስ፣ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ጋር፣ አስራ አምስት ዓመት በዮሐንስ ቤት፣ በአጠቃላይ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ኖራ ዐርፋለች፡፡ለዚህም በህይወተ ሥጋ በኖረችበት ዘመን ልክ ቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴ ማርያምን በ64 አንቀጽ ከፍሎ 64 ጊዜ ሰአሊ ለነ ቅድስት ብለን እንድናመሰግናት አድርጓል፡፡
ልመናዋ ፍቅሯ አማላጅነቷ የልጅዋም ቸርነት በሁላችን ላይ አድሮ ይኑር፡፡ አሜን፡፡

.   ❤❤እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ❤❤የማቴዎስ ወንጌል ፫÷፲፮-፲፯ መልካም በዓል                         ጥር ፲/፭/፪፻፲፰ ዓ.ም                       ...
18/01/2026

. ❤❤እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ❤❤


የማቴዎስ ወንጌል ፫÷፲፮-፲፯

መልካም በዓል
ጥር ፲/፭/፪፻፲፰ ዓ.ም በሙላቱ የተፃፈ

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳች።በዚህም በዓል በመላው ዓለም ለሚኖሩ ለደቂቀ አዳም በሙሉ ሰላም፣ፍቅርና ጤና ይኖር ዘንድ መልካሙን ሁሉ እመኛለ...
07/01/2026

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳች።
በዚህም በዓል በመላው ዓለም ለሚኖሩ ለደቂቀ አዳም በሙሉ ሰላም፣ፍቅርና ጤና ይኖር ዘንድ መልካሙን ሁሉ እመኛለሁ።
ከሙላቱ ቢረሳው ተፃፈ

.           🌼አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌው🌼“ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ:- የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት...
24/12/2025

. 🌼አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌው🌼
“ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ:- የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት ባጠፋን ነበር” በማለት የእመቤታችንን ቃል ኪዳን አማናዊነት ይገልጸዋል፡፡

.                🌻......አዝዋ ማርያም......🌻 📖 ባህርዳር ጣና ሐይቅ ዘጌ በሚባለው ደሴት ውስጥ ትገኛለች የተመሠረተችው በ13ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በ 1307 ዓ.ም ሲሆን ...
23/12/2025

. 🌻......አዝዋ ማርያም......🌻

📖 ባህርዳር ጣና ሐይቅ ዘጌ በሚባለው ደሴት ውስጥ ትገኛለች የተመሠረተችው በ13ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በ 1307 ዓ.ም ሲሆን ገዳሟን የመሠረቱት አቡነ በትረ ማርያም ናቸው።
📖 ወንጌላዊው ሉቃስ ከሳላቸው ሶስቱ ስዕሎች ውስጥ አንደኛዋ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል በአዝዋ ማርያም ትገኛለች።

❤ገዳሟን በመሳለም የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ መልካም እመኛለሁ። 14/04/2018

Address

Bahir Dar
1763

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mulatu Biresaw posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category