በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት "በፈቃደኝነት ለይ የተመሰረተ ግብር እና ታክስ የመክፈል ኃላፊነቱን በአግባቡ የሚወጣ ታማኝና ታታሪ
ማህበረሰብን በመገንባት ለተሻለ ነገ እንሰረለን::!!"

በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የህዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።( ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም) የማዕከላዊ ኢትዮጵ...
05/09/2026

በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የህዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።

( ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የሴክተር ጉባኤ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

ቢሮው ''ጠንካራ የፍትህ ሥርዓት ለጠንካራ ሀገረ-መንግስት ግንባታ'' በሚል መሪ ቃል የ2018 አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ነው ከባለድርሻና ከህዝብ ክንፍ አካላት ጋር እየመከረ ያለው።

የቢሮው ሀላፊ አቶ አክመል አህመዲን በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት በክልሉ የህግ የበላይነት በማስከበር የህዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በቅንጅት በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት መጥቷል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ውጤቶች ከለፉት ዓመታት ለውጥ የታዬባቸው መሆኑን የተናገሩት ሀፊው በበጀት ዓመቱ በድርድር እና በክስ ከ378 ሚሊዮን ብር በላይ ማስመለስ ተችሏል ብለዋል።

በፍትህ ትራንስፎርሜሽን የመሠረተ ማህበረሰብ ፍትህ አንዱ በመሆኑ ይህን ተግባር ወደ መሬት በማውረድ የባህላዊ ፍርድ ቤት አዋጅ በማጽደቅ ወደ ተግባር ተገብቷል ብለዋል።

ይህም በፍርድ ቤት የጉዳዮች መጨናነቅ ከመቀነሱም በላይ በተከራካሪ ወገኖች መካከል እርቀ ስለም በማዉረድ አብሮ የመኖር ባህል እንድዳብር አድርጓል ብለዋል።

የባለጉዳዮችንም ውጣውረድ እና ወጪ የሚቀንስ በመሆኑ በመሆኑ ቀጣይም በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ እንድቀጥል ተገቢው ክትትል እና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የፍትህ ተደራሽነትንም ለማረጋገጥ ቢሮው ሁለት ምድብ ጽ/ቤት በሆሳዕና እና በወልቂጤ ከተማ በመክፈት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ልማዳዊ አሠራር ተቋሙን ለብልሹ አሰራር በመዳረግ የተቋሙን እምነት የሚሸረሽር መሆኑን የገለፁት አቶ አክመል አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማዘመን በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ የአንድ መሶብ የአገልግሎት ማዕከላት ላይ የፍትህ ተቋማትን አገልግሎቶች የማስገባት ስራው ተጠናክሮ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይ ከመሬት ወረራና ብልሹ አሰራር፤የጥላቻ እና ሀሰተኛ ማህበራዊ ሚዲያ በላይ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ጠንካራ የምርመራ ሥራ በመስራት የተመዘበረ ሀብት የማስመለስና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በመድረኩ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ ዶ/ርን ጨምሮ የክልል፣የዞንና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ ባለሙያዎች፤ ባለድርሻ አካላት እና የህዝብ ክንፍ አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

👉የክ መ ኮ

ምክር ቤቱ ለ2019 ዓ.ም 818 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በጀት አጸደቀ==========ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ( የማ/ል/ወ/መ/ኮ) ፦ ቆሼየማረቆ ልዩ ወረዳ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛው ...
05/09/2026

ምክር ቤቱ ለ2019 ዓ.ም 818 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በጀት አጸደቀ
==========

ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ( የማ/ል/ወ/መ/ኮ) ፦ ቆሼ

የማረቆ ልዩ ወረዳ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛው ዙር 13ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቆሼ ከተማ አካሂዷል።

ምክር ቤቱ 4ኛው ዙር 13ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቆሼ ከተማ በማካሄድ ላይ ባለበት ለ2019 በጀት ዓመት 818 ሚሊዮን 107 ሺህ 715 ብር በጀት አጽድቋል።

የማረቆ ልዩ ወረዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው የጉባኤ ውሎ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን ተመልክቶ ከተወያየ በኋላ በጀቱን በሙሉ ድምጽ ማጽደቁ ታውቋል።

በዚህም ለ2019 በጀት ዓመት የልዩ ወረዳውን የሥራ እቅዶች ለማስፈጸም የሚውለው ጠቅላላ በጀት 818 ሚሊዮን 107 ሺህ 715 ብር ሆኖ ጸድቋል።

05/09/2026
ለታክስ ሕግ ተገዥ ያለመሆን መገለጫዎችነሐሴ 23/2018ለታክስ ሕግ ተገዥ አለመሆን ማለት የግብር እና የቀረጥ ግዴታዎችን በትክክለኛው መንገድ አለመወጣት ነው፡፡ለታክስ ህግ ተገዥ ያለመሆንን ...
29/08/2026

ለታክስ ሕግ ተገዥ ያለመሆን መገለጫዎች

ነሐሴ 23/2018
ለታክስ ሕግ ተገዥ አለመሆን ማለት የግብር እና የቀረጥ ግዴታዎችን በትክክለኛው መንገድ አለመወጣት ነው፡፡

ለታክስ ህግ ተገዥ ያለመሆንን ከሚያሳዩ መገለጫዎች ውስጥ፡-

👉ደረሰኝ አለመቁረጥ፣
👉 በግብር ከፋይነት አለመመዝገብ፣
👉 ግብርን በወቅቱ አለማሳወቅ እና አለመክፈል፣
👉 የተሳሳተ መግለጫ መስጠት (ገቢን ማሳነስ እና ወጪውን ማብዛት)
👉 የማይገባውን ተመላሽ መጠየቅ፣
👉 አላግባብ በተደጋጋሚ ኪሳራ ማሳወቅ፣
👉 የግብር ቅናሽ ማድረግ፣
👉 የሽያጭ መመዝገቢያን ማሽን በአግባብ አለመጠቀም በዋናነት ከሚጠቀሱት መካከል ናቸው::

መስተዳድር ምክር ቤቱ ዛሬ በካሄደዉ  ስብሰባ በተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፣ሆሳዕና ፣ ነሐሴ 22፣ 2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ መስተዳድር ምክር ...
28/08/2026

መስተዳድር ምክር ቤቱ ዛሬ በካሄደዉ ስብሰባ በተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፣

ሆሳዕና ፣ ነሐሴ 22፣ 2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ በካሄደዉ መደበኛ ስብሰባ፦ በቀረቡለት የኢንቨስትመንት ልማት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፤ በገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ደንብ ላይም ተወያይቶ ደንቡን አፅድቋል።

መስተዳድሩ ምክር ቤቱ በቀረቡለት አስራ ሦስት የኢንቬስትመንት ልማት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎች ላይ በዝርዝር በመወያየት እና በፕሮጀክቶቹ አስፈላጊነት ላይ መግባባት በመፍጠር ፕሮጀክቶቹ ወደ ልማት እንቅስቃሴ እንዲሸጋገሩ ወስኗል።

ከቀረቡት አስራ ሶስት የኢንቬስትመንት ልማት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎች መካከል ዘጠኙ በኢንዱስትሪ ፣ ሁለቱ በግብርና የተቀሩት ሁለቱ ደግሞ በአገልግሎት ዘርፎች ለመሠማራት የተዘጋጁ መሆናቸዉ ተጠቁሟል።

ከኢንቬስትመንት ልማት ፕሮጀክቶቹ መካከል ሶስቱ የዉጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንቶች መሆናቸዉም ተጠቅሷል ።

መስተዳድር ምክር ቤቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 32/2016 ማስፈፀሚያ ደንብ ላይም ተወያይቷል፤ ደንቡ ቀደም ሲል የወጣዉን የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 32/2016 ለማስፈጸም አስፈላጊ መሆኑ ተብራርቷል።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በደንቡ ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ አፅድቋል።

ክልሉ የገቢ አሰባሰብን ለማሳደግ የተጀመሩ ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር ስራ አጠናክሮ  መቀጠሉ ተገለጸ።20/12/2018 ቆሼየድጋፍ ክትትሉን የክልሉ የድጋፍ ቲም አባል ዛሬ በማረቆ ልዩ ወረዳ ...
26/08/2026

ክልሉ የገቢ አሰባሰብን ለማሳደግ የተጀመሩ ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር ስራ አጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።
20/12/2018 ቆሼ

የድጋፍ ክትትሉን የክልሉ የድጋፍ ቲም አባል ዛሬ በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ በመገኘት የገቢ አሰባሰብን ለማጠናከር የድጋፍና ክትትል ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

የድጋፍ ክትትል ቡድኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በለሙያ አቶ ኑርሀሰን መኪዩ እንዲሁም የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡስማን ተሰማ እንዲሁም የልዩ ወረዳ የገቢ ማኔጅመንት አካላት ተሳትፈዋል።

አቶ ኑርሀሰን መኪዩ በመድረኩ እንደገለጹት፣ የበጀት ዓመቱን የገቢ ዕቅድ በተሟላ መልኩ ለማሳካት የቅድመ ዝግጅት ሥራ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ የታክስ ሕግ ተገዥነትን ከማጠናከር ጀምሮ ሁሉም ማኔጅመንት እና በለሙያ የተቀናጀና የተጠናከረ ሥራ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል።

በውይይቱም የልዩ ወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ሀለፊ አቶ ኡስማን ተሰማ የነሐሴ ወር የእስካሁን ገቢ ያቀረቡ ና ያተመዘገበው የገቢ አፈጻጸም በመገምገም፣ ከሚጠበቀው የገቢ ደረጃ ጋር በማነጻጸር የቀረውን ክፍተት በፍጥነት በመለየት ዕቅዱን ለማሳካት በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ እና ቀጣይ ክልሉ ባስቀመጠው የድጋፍ ክትትል አቅጣጫ በተገቢው በመፈጸም በተባለው የጊዜ ሰሌዳ ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ ወደ ስራ የተገባ መሆኑን እና ድጋፉ ለቀጣይ ስራ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ በመግለጽ ስምሪት ለማኔጅመንቱ እና ባለሙያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

22/08/2026

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት:

Shortcuts

Share