በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት "በፈቃደኝነት ለይ የተመሰረተ ግብር እና ታክስ የመክፈል ኃላፊነቱን በአግባቡ የሚወጣ ታማኝና ታታሪ
ማህበረሰብን በመገንባት ለተሻለ ነገ እንሰረለን::!!"

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በእስካሁኑ 21 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስተወቀ።
18/05/2026

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በእስካሁኑ 21 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስተወቀ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ እስከ አሁን 21 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ዘጋቢ ፡ አብደላ በድሩ #ደሬቴድ የቪዲዮና .....

https://www.facebook.com/share/18P6oESVnc/
13/05/2026

https://www.facebook.com/share/18P6oESVnc/

የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብር የሚከፍሉት በሚከተለው አኳኋን ይሆናል፣

ከተያዘው የግብር ዓመት በፊት ማለትም የ2017 ግብር ዘመን በነበረው የከፈሉትን ግብር 25%(ሃያ አምስት በመቶ) ከሐምሌ ወር መጨረሻ ጀምሮ በሚቆጠር በየሶስት ወሩ የሶስት ወሩ በተጠናቀቀ በ30 (ሰላሳ) ቀናት ውስጥ አስቀድመው መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡
በዚህ መሠረት፡-
👉የመጀመሪያ ዙር ክፍያ ጊዜ ከህዳር 01 እስከ 30 ይሆናል፣
👉የሁለተኛ ዙር ክፍያ ጊዜ የካቲት 01 እስከ 30 ይሆናል፣
👉የሶስተኛ ዙር ክፍያ ጊዜ ከግንቦት 01 እስከ 30 ሲሆን በየግብር ዓመቱ ሐምሌ ወር መጨረሻ ሊከፍሉ ከሚገባው ግብር ላይ በየሶስት ወሩ የከፈሉት ተቀንሶ ቀሪውን ይከፍላሉ፡፡

የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ መያዝ ግዴታ የለለባቸው ሲሆን በፍቃደኝነት መያዝ ይችላሉ፡፡ የያዙት የሂሳብ መዝገብ ተቀባይነት ካገኘ የሚከፍሉት ግብር በሂሳብ መዝገባቸው ሠንጠረዥ ሐ መሰረት ይሆናል፡፡

ከላይ የተጠቀሰው ቢኖርም ለመጀመሪያ ጊዜ የገቢ ግብር የሚከፍሉ አዲስ ግብር ከፋዮች የመጀመሪያውን የግብር ዓመት በተመለከተ ዓመታዊ ግብር የሚከፍሉት በሚከተለው አኳኋን ይሆናል፤

ሀ) የደረጃ "ሀ" አዲስ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ገቢያቸውን ማስታወቅ ባለባቸው ጊዜ በግብር ዓመቱ ሊከፍሉት የሚገባውን ግብር መክፈል አለባቸው፡፡

ለ) የደረጃ "ለ" አዲስ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1 ቀን እስከ ሐምሌ 30 ቀን ባለው ጊዜ ዉስጥ ግብሩን መክፈል አለባቸው::

  በማረቆ ልዩ ወረዳ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ ታላቅ የልማት ታሪክ እየተጻፈ ይገኛል። የዚህ ታሪካዊ አሻራ አካል ለመሆን የልዩ ወረዳው የገቢዎች ጽህፈት ቤት ባልደረቦች ለገራድ ቢመዶ አጠቃላ...
10/05/2026




በማረቆ ልዩ ወረዳ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ ታላቅ የልማት ታሪክ እየተጻፈ ይገኛል። የዚህ ታሪካዊ አሻራ አካል ለመሆን የልዩ ወረዳው የገቢዎች ጽህፈት ቤት ባልደረቦች ለገራድ ቢመዶ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ የሚውል 100,000(አንድ መቶ ሺህ) ብር ከመደበኛ የደመወዝ መዋጮ ባሻገር ድጋፍ አድርገዋል።

የጽህፈት ቤቱ ሰራተኞች የገንዘብ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ የሆስፒታሉን ግንባታ ሂደት በአካል ተገኝተው የጎበኙ ሲሆን፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነትም አሳይተዋል።

ስላደረጋችሁት አርአያነት ያለው ድጋፍ በማረቆ ልዩ ወረዳ መንግስትና ህዝብ ስም ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!

ገራድ ቢመዶን እኛ ካልሰራነው ማን ይሰራዋል? ዛሬ የምናደርገው እያንዳንዱ አስተዋፅኦ ለነገው ትውልድ የህይወት ዋስትና ነው። የእርሶንም አሻራ ዛሬውኑ ያሳርፉ!
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አካውንት (CBE) 1000662416324
(Garad Bimedo General Hospital)

የደረጃ “ለ” ግብር ክፋዮች የሩብ ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜያት
09/05/2026

የደረጃ “ለ” ግብር ክፋዮች የሩብ ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜያት

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት:

Share