Mohammed mohamud legal Consultant

Mohammed mohamud legal Consultant ጠቃሚ እና ምክር ያዘሉ ወቅታዊ የህግ ጉዳዮችን በዚህ ገጽ ላይ ያገኛሉ። ገጹን ፎሎ እና ላይክ በማድረግ በዚህ ገጽ ላይ ዩሚለቀቁ ጠቃሚ መረጃዎችን ያግኙ።

21/11/2022

Very Important Issue!

በ ሰ/መ/ቁ. 123123 ቅጽ 21 በተሰጠ የህግ ትርጉም ከሳሽ ያቀረበው ክስ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 92 የተደነገገውን አስገዳጅ መስፈርት የማያሟላ መሆኑን በማረጋገጥ ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤት በሰጠው ትዕዛዝ መዝገቡ ከተዘጋ ምንም አይነት ክስ እንዳልቀረበ የሚያስቆጥርና የይርጋ ጊዜ የማቋረጥ ውጤት የሌለው ነው።

የሰ/መ/ቁ 123123 - በክስ አቀራረብ ሥርዓት ላይ ጉድለት ያለበት መሆኑ ተረጋግጦ የተዘጋ መዝገብ ምንም አይነት ክስ እንዳልቀረበ የሚያስቆጥርና የይርጋ ጊዜ የማቋረጥ ውጤት የሌለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 278 (2) (ሀ) እና (3)

ክስ ስታቀርብ ክሱን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 92 ማረጋገጥ ከረሳህና በሬጅስትራርም ሳይታረም መዝገቡ ለችሎት ከቀረበ ፍርድ ቤቱ ስነ-ስርዓት አላሟላም በሚል መዝገቡን ይዘጋዋል። ቀጥሎ ያለው መፍትሔ ሌላ ክስ ማቅረብ ነው። አዲሱ ክስ ደግሞ የይርጋ ጊዜን አያቋርጥም።
(Abyssinia law)

19/10/2022

❗የመንደር ውል አደጋዎች

የመንደር ውል ሕጋዊ ነው አይደለም የሚለውን ሙግት እረፍት እንስጠውና ወደ አንድ ቁልፍ ነጥብ እንሻገር።

የመንደር ውል ይዞብን የሚመጣው ፈተና ምንድነው?

1/ አንድ የቤት ገዥ በመንደር ውል ከተዋዋለ በኋላ ያን ይዞ ክፍለ ከተማ ሄዶ ስም ይዙርልኝ ቢል ተቀባይነት የለውም።

2/ አንድ ቤት ገዥ ቤቱን በመንደር ውል ገዝቶ አገር ሰላም ብሎ እየኖረ ድንገት የ3ኛ ወገን ጥያቄ ቤቱ ላይ ቢነሳ ለከፍተኛ ቀውስ ይጋለጣል። ይህም ከሻጭ ባል/ሚስት የሚመጣ፣ "ውሉ ውድቅ ይደረግልኝ" የሚል ጥያቄ ሊሆን ይችላል።

በመንደር ውል ያገባ/ያላገባ ሰነዶች ጋር ተያይዞም ብዙ አሳሳቢ ጉዳዮች አሉ። ኋላ ላይ በሚመጣ መቃቃር ፍቺ ቢኖር ገዢ ከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ ይገባል።

አንድ ቤት ገዥ አገር ሰላም ብሎ ቤት በመንደር ውል ገዝቶ እየኖረ፣ የሻጭ ባል/ሚስት ሽያጩ አይመለከተኝም ይፍረስልኝ ብትል/ቢል፣ ቤት ገዢ ከፍተኛ የፋይናንስና የሥነ ልቡና ጉዳት ይደርስበታል።

የመንደር ውሉን ይዞ ፍርድ ቤት ቢሄድም አትስተናገድም ባይባልም፣ ከሻጭ ገንዘቡን መልሶ የማግኘት ዕድሉ ጠባብ ነው የሚሆነው።

እንዲህ ዓይነት በርካታ ጉዳዮች ያጋጥማሉ፣ ሽያጭ ውሉ አይመለከትኝ የሚሉ የትዳር አጋሮች ይኖራሉ። በቤተሰብ ሕጉ ከ500 ብር በላይ የሚደረግ ሽያጭ የሁለቱንም ይሁንታ ማግኘት አለበት፤ በዚህ የተነሳ የመንደር ውል ያልታሰበ ጣጣ ይዞ ይመጣል። ብቻ በአጠቃላይ በመንደር ውል ገዥው በራሱ ላይ የሚጋብዘው አደጋ የትየሌሌ ነው።

በመንደር ውል ስንዋዋል አንዳንድ ጊዜ ይሆናሉ ብለን የማንጠብቃቸው ነገሮችም እንደሚከሰቱ መዘንጋት የለብንም። ለምሳሌ በመሀል ሞት አለ። ከአገር መውጣት አለ። ውክልና ማንሳት አለ። በሰው ላይ ነገ ምን እንደሚደርስ ማን ያውቃል?

በመንደር ውል የተፈራረመ ሻጭ ቢሞት የውርስ ጉዳይ ይከተላል፣ ጋብቻ ቢፈርስ የቤተሰብ ክርክር ውስጥ ይገባል፣ ወራሾች ቤቱ በሕገ ወጥ ውል የተፈጸመ ነው ብለው ሊያሳግዱት ይችላሉ። ጣጣው ብዙ ነው።

04/10/2022

የተበዳይን ዓይን በማጥፋት የ8 ሺህ ብር የሞባይል ስልክ የወሰደው ተከሳሽ በከባድ የውንብድና ወንጀል በፅኑ እስራት ተቀጣ
------------------------------------------------------
የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ወዳጀ ልንገርህ አንለይ በተባለው ተከሳሽ ላይ የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 671/2/ ስር የተመለከተውን ተላልፏል ሲል በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ መስርቶበት ክርክር ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

የዐቓቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 ሰዓት ሲሆን በቦሌ ክ/ከ/ ወረዳ 09 ልዩ ቦታው ቀጠና 01 አካባቢ የግል ተበዳይ ብናየው ጋሻው ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ እያለ መንገድ ላይ ጠብቆ የጭንቅላቱን በድንጋይ በበምታትና በጩቤ ግራ አይኑ በመውጋት የግራ ዓይኑ ሙሉ በሙሉ እንዲጠፋ በማድረግ እንዳይከላከል ጥቃት ካደረሰበት በኋላ የግል ተበዳይ ይዞት የነበረውን ሳምሰንግ ሞባይል የዋጋ ግምቱ 8,000/ስምንት ሺህ/ ብር የሚገመት ቀምቶ ይዞ በመሮጥ ላይ እያለ በአካባቢው ሰዎች የተያዘ በመሆኑ በፈፀመው ከባድ የውንብድና ወንጀል ተከሷል፡፡

ተከሳሽ በችሎት ቀርቦ ክሱ ደርሶትና ተነቦለት የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ” እኔ ድርጊቱን አልፈፀምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም ”ሲል ክዶ የተከራከረ ሲሆን ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሳሽን ጥፋተኝነት ለፍርድ ቤቱ ያስረዱልኛል ያላቸውን ዝርዝር የምስክሮች ቃል እና የሰነድ ማስረጃዎችን በበቂ ሁኔታ ለችሎቱ በማስረዳቱ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም ተከሳሽ የዐቃቤ ህግን ክስ እና ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻሉ የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት በተከሳሽ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፏል።

በዚህም መሰረት ተከሳሽ ከዚህ በፊት የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት߹ መሆኑን ጨምሮ ሰባት የቅጣት ማቅለያዎች ተይዘውለት በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ።
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር

03/10/2022




==========================
የእርሻ መሬት ውርስ አስመልክቶ ክልሎች ያወጡት የእርሻ መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጆች የተለያየ ይዘት ያላቸው ናቸው፡፡ ከዚህ አንጻር የእርሻ መሬት የመጠቀም መብት በውርስ የማስተላለፍ መብትና በእርሻ መሬት ላይ ያሉ ንብረቶች የመውረስ መብት አንድና ተመሣሣይ አድርጐ በማየት የመወሰን፣
የፍትሐብሔር ህጉ የውርስ ህግ ድንጋጌዎች ተፈፃሚነት የላቸውም በማለት በግልፅ በተደነገገበት ትግራይ ክልል ጭምር የእርሻ መሬትን ውርስ በፍታብሔር ድንጋጌዎች አንፃር አይቶ የመወሰን ሁኔታ መኖሩና፣
ስጦታን በተመለከተ በስውርና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ መሬቱን ለመሸጥ ለመጠቀም የሚሞክሩ ሰዎች ያሉ መሆኑና የስጦታ ውሉ በቀበሌ አስተዳደር ወይም በወረዳ ዲስክ የሚፀድቅበትና የሚመዘገብበት ሁኔታ መኖሩን በዚህ ምክንያት ክርክር ሲነሣ እውነቱ ሣይጣራና ህጉ ሣይገናዘብ የሚሰጡ ውሣኔዎች መኖራቸው፣

በሌላ በኩል መሬት በውርስ ወይም በስጦታ አግኝቻለሁ በማለት የሟች አርሶ አደር ህፃናት ልጆች፣ ሚስት፣ ተጧሪ አያትና አባት ይዞታውን እንዲለቁ የሚቀርቡ ክሶች የሚስተናገዱና አልፎ አልፎ ህፃናቱ የመሬት ይዞታ እንዲያስረክቡ የማስገደድ ውሣኔዎች የሚሰጡ በመሆኑ በዚህ በኩል እየተራዘሙ የመጡ ክርክሮችን በማየት ለመገንዘብ ይቻላል፡፡

#የሌሎች ችግሮች መገለጫና ገፅታ

ባልና ሚስት ከመጋባታቸው በፊት በየአካባቢያቸው የያዙት የእርሻ መሬት ያላቸው ሆኖ እያለ ባል ወይም ሚስት ለብቻ በኖሩበት አካባቢ ያለው ተጋቢ ያለውን የይዞታ መሬት የመጠቀም መብት እንዲካፈል የሚቀርብ ክስና የሚደረግ ክርክር በዚህ ረገድ የሚሰጥ ውሣኔ ያለ መሆኑ፣ በተለይም በመሬቱ ላይ ያለውን ሀብት /ሰብል ተክል ወይም ዛፍ/ እና መኖሪያ ቤት የመካፈል መብትና በይዞታ መሬት የመጠቀም መብት ተለይተው የማይወስኑ መሆኑ፣ ባል ሚስት ከማግባቱ በፊት ይዞት የነበረው የእርሻ መሬት፣ ሚስት ባል ከማግባቷ በፊት ይዛው የነበረው የእርሻ መሬት በፊት የእርሻ መሬት አብሮ ለሚኖረው ለሌላኛው ተጋቢ መሬቱን የመጠቀም መብት የማካፈል ግዴታ አለበት ወይስ የለበትም? በመሬቱ ላይ ያለውን ንብረት /መኖሪያ ቤት ሰብል ተክልና ዛፍ/ የመካፈል መብትና የመሬት ይዞታን የመጠቀም መብት የሚለው ላይ የህግ ማዕቀፎቹ ግልፅ አለመሆኑና በውሣኔ አሰጣጥ ሂደትም የሚታዩ ችግሮች፣
የእርሻ መሬት የመጠቀም መብት ቀሪ የሚሆነው አንድ ሰው ያለ በቂ ምክንያት በራሱ ፈቃድ አካባቢውን መሬቱን ለቅቆ ሁለት ዓመትና ከዚያ በላይ ከሄደ መሆኑ በየህጎቹ ተገልጿል፡፡ አንድ አርሶ አደር መሬቱን ከሁለት ዓመት በላይ ከለቀቀ መንግስት መሬት ለሌላቸው አርሶ አደሮች በመሬት ሽግሽግ እንደሚሰጥ የፌዴራል እና የክልል የህግ ማዕቀፎች የሚደነግጉ ቢሆንም ይህ ጉዳይ ከይርጋ ድንጋጌዎች ጋር አንድና ተመሣሣይ ተደርጐ የሚጠቀስና የሚተረጉም ውሣኔ የሚሰጥ መሆኑ፣
ከእርሻ መሬት የመጠቀም መብት ጋር በተያያዘ መንገድ በፍታብሔር ህጉ ስለ ይዞታ፣ ስለ ውርስ እና ስጦታ ውል የተደነገጉ ድንጋጌዎች የጉዳዩን ልዩ ባህሪ ባላገናዘበ ሁኔታ የሚተረጎሙ መሆኑ፣
በቀበሌ ውሣኔ እንዲሰጡ ስልጣን የተሰጣቸው አካላት ለተከራካሪዎች መጥሪያ ሳይደርስ፣ የመከላከያ ማስረጃ ሣያቀርቡ፣ እውነቱን ሣያጣሩ የሚወስኑ መሆናቸውና በፍርድ ቤቶች በክርክር ሂደት የሚፈፀሙ የሥነ ስርአት ጥሰቶች ያሉ መሆናቸው፣

የመሬት ሽግሽግ ይዞታው የተሰጠው ለእኔ ነው ለእኔ ነው በሚል ምክንያት የሚከራከሩ ሰዎችን መብት በማስረጃ አጣርቶ በመወሰን በኩል መረጃዎች በአግባቡ የማይያዙና ተጣርተው የማይወሰኑ መሆናቸው፣


በመሬት ኪራይ ሰበብ የእርሻ መሬት ሽያጭ የሚፈፀምበት፣ በእርሻ መሬት ላይ ቤት የሚሠራበት፣ የኪራይ ውሉም ከመሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን በተመለከተ ያወጡትን የህግ ማዕቀፎች በሚፃረር ሁኔታ ያለሚስት ወይም ያለ ባል ፈቃድ የማከራየትና ከዚህ ጋር ተያይዘው በሚቀርቡ ክርክሮች ውሳኔ አሰጣጥ ችግሮች ያሉ መሆኑ፣

አንዳንድ አካባቢ ከዚህ በፊት በውሣኔ ያለቁ ጉዳዮች ባለመቀበል ወይም የተሰጡ ውሣኔዎች በአግባቡ ባለመፈፀማቸው ምክንያት የሚቀርቡ ክርክሮች በአግባቡ እልባት የማያገኙ መሆናቸው

የመሬት አጠቃቀም መብት አስመልክቶ የሚነሱ ችግሮች መገለጫና ዋና ዋና ገፅታዎች እንደሆነ ለማየት ይቻላል፡፡

#የመፍትሔ ሀሳቦችና ማጠቃለያ

የእርሻ መሬት ይዞታን መነሻ በማድረግ በሚደረጉ ክርክሮች የሚከሰቱ ችግሮች መግለጫ ከላይ የተገለፀው ሲሆን፣ ችግሮቹ ከእርሻ መሬት ይዞታና ተጠቃሚነት ጋር ህይወቱ ጥብቅ ቁርኝት ያለው አርሶ አደር ከፊል አርብቶ አደር እና አርብቶ አደር ህይወት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ያላቸው ናቸው፡፡ ስለሆነም ችግሮቹን ለመቅረፍ፡-

እውነተኛው ባለይዞታ ማን ነው የሚለው ፍሬ ጉዳይ በቀበሌ መሬት አስተዳደር ኮሚቴ ወይም በሽማግሌ በፍሬ ጉዳይ ደረጃ ጊዜ ሰጥተው አጣርተው የሚወስኑበት ሁኔታ ያለ ቢሆንም አልፎ አልፎ የሚፈጠሩ ችግሮች ያሉ በመሆኑ ፍሬ ጉዳዩን በይግባኝ ደረጃ በማጣራት በመጀመሪያ ደረጃ ክርክር ወቅት ፍርድ ቤቱ ወይም ምትክ ዳኛ በማሰየም ደጋፊ የፅሑፍ ማስረጃዎች በማየትና በመመርመር በመመዘን በመወሰን ብዙዎቹን ችግሮች ለመቅረፍ ጥረት ማድረግ ይገባል፡፡

የመሬት ክርክር አርሶ አደሩ በቂ መጥሪያ ሣይደርሰው፣ መከላከያ ማስረጃ ሣያቀርብ ቴክኒካል የሆኑ የሥነ ሥርዓት ጉዳዮችን መሠረት በማድረግ የሚሰጡ ውሣኔዎች አርሶ አደሩን ከመሬቱ የማፈናቀል ውጤት የሚያስከትል በመሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መስጠትና አርሶ አደር በሌለበት የሚታይ ጉዳይም ቢሆን እውነቱን ለማጣራትና ለመወሰን ተገቢውን ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የየክልሎቹ የህግ ማዕቀፎች መሠረታዊ መርሆች ልዩ ባህሪና ይዘት በመረዳት የህጎቹን ግብና ዓላማ መሠረት በማድረግ ህጎቹን መተርጎምና በተለይም ግለሰብ መቃወሚያ የማያደርጋቸው ጉዳዮች ይርጋ ህግ ጋር በማቀላቀልና ሌሎቹንም የህግ አተረጓጎም ግድፈቶችን በማረምና ለውሣኔ መሠረት የሆኑ የፌዴራልና የክልል የህግ ማዕቀፎች ድንጋጌዎችና ይዞታቸውን በማጣቀስ ውሳኔ መስጠት ይገባል፡፡
ለፍርድ ቤት የሚላኩ የፅሑፍ ማስረጃዎች እና ሰነዶች ትክክለኛነት ማጣራት ተቃራኒ ማስረጃዎች ከመንግስት አካላት ሲልኩ ዕውነቱን ለማወቅና ለማጣራት የሚያስችሉ የተለያዩ የማጣሪያ መንገዶች መጠቀምና አጣርቶ መወሰን፣
በአስተዳደር አካላት በኩል መረጃዎች በአግባቡ እንዲያዙ እንዲጠበቁ የማድረግ አስፈላጊነትን በተመለከተም በአንድ ወይም በሌላ መልኩ በሚዘጋጁ ፕሮግራሞች ግንዛቤው እንዲያዝና አሰራሩ እንዲዘረጋና እንዲለመድ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በየአካባቢው የሚታዩ ችግሮችን መነሻ በማድረግ በማጥናትና በማጠቃለል የጥናት ውጤቶችን ከመፍትሄ ሀሳቦች ጋር ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
በየአካባቢው ወጥተው ሥራ ላይ ስለዋሉ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ህጎች ደንቦችና መመሪያዎች አርሶ አደሩ መብቱንና ግዴታውን እንዲረዳ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የገጠር የእርሻ መሬት በነፃ የማግኘት መብት፣ ከእርሻ መሬት ያለመፈናቀል መብት እና መሬቱን የመጠቀም መብት ህገ መንግስታዊ ጥበቃ እና ዋስትና የተሰጠው መብት ነው፡፡ አንድ አርሶ አደር በተለያየ ምክንያት አላግባብ ይህ መብቱን ካጣ የእሱና የቤተሰቡ የመኖር ዋስትው አደጋ ላይ የሚወድቅ መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር ማንኛቸውም አርሶ አደር ጉዳዩ በአግባቡ ባለማጣራቱ ምክንያት ከሚደርስበት የፍትህ እጦት እና እሱና ቤተሰቡ የኑሯቸው ህልውና እንዳይናጋ ለማድረግ በሙያችን ዕውነቱን ለማውጣት እና ትክክለኛ ፍትህ ለመስጠት አስፈላጊውን ጥረትና ትጋት ማድረግ ያስፈልገናል፡፡

Tsegaye Demeke - Lawyer

  team led by Tourism Minster H.E Ambassador Nassise Chali arrives in Assosa for the world tourism day celebration! Upon...
22/09/2022

team led by Tourism Minster H.E Ambassador Nassise Chali arrives in Assosa for the world tourism day celebration!

Upon arrival at the Assosa Hidase airport, H.E Ambassador Nassise was accorded a warm welcome by the regional president Ashadli Hassen and the regional higher officials. World tourism day will be celebrated in the region for the coming three days and there is the prospect that it will unveil many hidden tourism products of the regional state.



 !!!
21/09/2022

!!!

21/09/2022
04/09/2022


========================
አንድ ሰው በህጋዊ መንገድ የያዘውን ይዞታ ለህዝብ ጥቅም ስፈልግ እንዴት እንደሚለቅ በህጉ በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ይህ ህግ ሳይከበር በዘፈቀደ ግለሰቦችን አስነስተው ይዞታው ሲወሰድ እናያለን። ይህ አለግባብ ስለሆነ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ህጉን ከማስፈጸም በፊት የዜጎችን መሠረታዊ መብት የሚመለከት ስለሆነ ህጉን ጠንቅቀው የሚያውቁ መሆን አለባቸው። ይህ የህግ አሰራር ሳይጠበቅ በፖሊስ አስፈራርቶ ወይም አስሮ ንብረት መውሰድ ሥልጣን አላግባብ መጠቀም ነዉ። ማንኛውም የመንግሥት አካል ሥራውን ሲያከናውን የመንግስት ህግ ሳይከተል በዘፈቀደ ወይም በህግ ከተፈቀደው ሥልጣን ውጪ መፈጸም ይሆናል። አንድ ሰው ይዞታውን ልለቅ የሚችለው ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱ ሁኔታዎች ከተፈጸመ በኃለ ነው።
የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣ አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 26-27 እንደሚከተለው ተመልክቷል።
1. የከተማ ቦታ የማስለቀቅ ሥልጣን
አግባብ ያለው አካል ከቦታው ለሚነሳው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በቅድሚያ እንዲከፈል በማድረግ የከተማ ቦታ ይዞታን ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የማስለቀቅና የመረከብ ሥልጣን ይኖረዋል።
#በሚወሰድ እርምጃ ምክንያት ተነሺ ለሚሆነው ሰው መጠኑ በክልሉ ወይም በከተማው አስተዳደር የሚወሰን ምትክ ቦታ በከተማው ውስጥ ይሰጠዋል።
#የከተማ ቦታ በሊዝ የያዘ ሰው የሊዝ ውሉን ባለማክበሩ፣ የቦታ አጠቃቀሙ ከከተማው ፕላን ጋር ሊጣጣም የሚችል ባለመሆኑ ወይም ቦታው መንግሥት ለሚያካሂደው የልማት ሥራ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የሊዝ ዘመኑ ከማለቁ በፊት ይዞታውን እንዲለቅ አይደረግም። #አግባብ ያለው አካል በሕገ ወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 27 መሠረት የማስለቀቂያ ትዕዛዝ መስጠትና ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ የሰባት የሥራ ቀናት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ብቻ ለባለይዞታው በአካል በመስጠት ወይም በቦታው በሠፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ሥልጣን ይኖረዋል።
2. የማስለቀቂያ ትዕዛዝ
#የከተማ ቦታ ይዞታ እንዲለቀቅ ሲወሰን ይዞታው የሚለቀቅበት ጊዜ፣ ሊከፈል የሚገባው የካሣ መጠን እና ሊሰጥ የሚችለው የምትክ ቦታ ስፋትና አካባቢ ተጠቅሶ የማስለቀቂያ ትዕዛዝ ለባለይዞታው በጽሁፍ ይሰጣል።
#መሠረት የሚሰጠው የማስጠንቀቂያ ጊዜ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች በሚወጡ ደንቦች ይወስናል፤ ሆኖም በማንኛውም ሁኔታ ከ90 ቀናት ያነሰ ሊሆን አይችልም።
የሚለቀቀው የከተማ ቦታ ይዞታ የመንግሥት ቤት የሰፈረበት ከሆነ የማስለቀቂያ ትዕዛዙ የሚደርሰው ቤቱን ለሚያስተዳድረው አካል ይሆናል።
#የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የተላለፈበት ቤት ተከራይቶ ከነበረ ትዕዛዙ የደረሰው አካል የማስጠንቀቂያ ጊዜው ከማብቃቱ በፊት የኪራይ ውሉን ለማቋረጥ የሚያስችል እርምጃ መውሰድ አለበት።

28/08/2022



#የአካል ጉዳት /የስራ ላይ ጉዳት ጥቅም የስራ ላይ ጉዳቶች በአራት ይከፈላሉ:-
ሀ/ ዘለቄታዊ ሙሉ መሰራት አለመቻል፣
ለ/ ዘለቄታዊ በከፊል መሰራት አለመቻል፣
ሐ/ ጊዜያዊ መስራት አለመቻል እና
መ/ ሰራተኛውን ለሞት የሚበቃ አደገኛ ጉዳት

ኢንሹራንስ ያለመቻል / የአካል ጉዳት ሲከሰት, ዋስትና ያለው ሠራተኛ ቢያንስ 10% የሥራ አቅም ማጣት እና ሥራ መሥራት የማይችል ከሆነ የመድን ባለዕዳው የአንድ ወር ሰራተኛ 47% ይከፈላል፡፡ የጉዳት ክፍያው ከእርጅና ጡረታው ካነሰ ወይም እኩል ከሆነ ለሰራተኛው መድን የተገባለት የወርሃዊ መነሻ ደመወዝ እስከ 70% ከእርጅና ጡረታው ለሰራተኛው ይከፈለዋል፡፡ ሰራተኛው የደረሰበት ጉዳት ቋሚና ለዘለቄታውም የማያሰራው ከሆነ የዓመታዊ ደመወዝ አምስት እጥፍ በአንድ ጊዜ ይከፈለዋል፡፡ /የአምስት አመት ደመወዝ/፡፡

ከጉዳት በፊት የመደበኛው ደመወዝ 47% በጥቅሉ በ60 ወሮች ይባዛል፡፡

የደረሰውን ጉዳት መጠን በመገመት ለደረሰው የአካል ጉዳት የሚፈለው፡- የዘላቂ ከፊል የአካል ጉዳቱ ሠራተኛው ላይ 10% የመሥራት ችሎታውን ቀንሶ ነገር ግን ሠራተኛው ለመሥራት ከቻለ ነው፡፡ ለግል ሠራተኛ ዘላቂ ላልሆነ የአካል ጉዳት 100% አማካይ የሠራተኛው ወርሃዊ ገቢ ለሦስት ወር ይከፈላል፡፡ ለተከታታይ 3 ወራት የወር ደመወዝ 75% እና ቢያንስ 5ዐ% ለተከታታይ ስድስት ወራት ይከፈለዋል፡፡

ጥቅማ ጥቅም የሚከፈለው ለ12 ወራት ወይም የአካል ጉዳት የደረሰበት ሠራተኛ ከጉዳቱ ሙሉ ለሙሉ ሲድን ወይም ጉዳቱ ዘላቂ የአካል ጉዳት መሆኑ ሠርቲፊኬት ሲሰጠው ነው፡፡

ለመንግሥት ሠራተኞች 100% የተቀጣሪው ማዕከላዊ የወር ገቢው ሠራተኛው እስከዳነ ድረስ ወይም ሥራ እስከጀመረ ድረስ ወይም ዘላቂ የአካል ጉዳት መሆኑን መረጃ ሠርቲፊኬት እስኪሰጠው ድረስ ነው፡፡

ለሞት በሚያበቃ ጉዳት ወቅት ጥገኞች /ባል/ሚስት፣ ከ18 ዓመት በታች ያሉ ህፃናትና ህይወቱ ባለፈው ሰራተኛ ይደገፉ የነበሩ ወላጆች/ ጡረታ ያገኛሉ፡፡ ህይወቱ ያለፈው ሰራተኛ ሊያገኘው ይችል ከነበረው ጡረታ 50% የተገመገመው ዘለቂታው ሙሉ ጉዳት ከሆነ ለባል/ሚሰት ይከፈላል፡፡ እናት ወይም አባት የሞቱባቸው ህጋዊ ልጆች ለእያንዳንዳቸው 20% የጡረታ ክፍያ ያገኛሉ፡፡ ሁለቱንም ወላጆች በሞት ላጣ ልጅ 30% የጡረታ ክፍያ ያገኛል፡፡ በህይወት ያሉ የሟች ልጆች ክፍያ 100% የጉዳት ካሣ ክፍያ ሆኖ ይህም መጠኑ ሟቹ በህይወት ቢኖር ኖሮ የሚከፈለው የጉዳት ካሣ ክፍያ መጠን ነው፡፡

ምንጭ፡ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 95-112፣ የግል ድርጅቶች ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 715/2011 አንቀጽ 27-38;

#ምንጭ ISSA የሀገር ፕሮፋይል 2019

22/08/2022

?

1/ አንድ ሠራተኛ በዚህ አንቀጽ መሠረት ሳይከፋፈል የሚሰጥ የዓመት ፈቃድ ከክፍያ ጋር ያገኛል፡፡ የፈቃዱ ጊዜ በምንም ሁኔታ ከዚህ በታች ከተመለከተው ማነስ የለበትም:-

ሀ) ለመጀመሪያ የአንድ ዓመት አገልግሎት አስራ ስድስት (16) የሥራ ቀናት፤
ለ) ለአሠሪው ከአንድ ዓመት በላይ ለተበረከተ አገልግሎት ለእያንዳንዱ ሁለት የአገልግሎት ዓመታት አንድ የሥራ ቀን እየተጨመረ ይሰጣል፡፡

2/ በዓመት ፈቃድ ላይ የሚገኝ ሠራተኛ የሚከፈለው ደመወዝ ሥራ ላይ ቢሆን ኖሮ ሊከፈለው ከሚገባው ጋር እኩል ይሆናል፡፡

3/ ለዓመት ፈቃድ ብቁ የሚያደርገውን የአገልግሎት ጊዜ ለመወሰን ሲባል በድርጅቱ ለ 26 ቀናት የሠራ ሠራተኛ ለ አንድ ወር እንደሰራ ይቆጠራል፡፡

4/ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት የሥራ ውሉ የተቋረጠ ሠራተኛ ያልወሰደው የዓመት
ፈቃድ ታስቦ በገንዘብ ይከፈለዋል፡፡

5/ አንድ ሠራተኛ ያገለገለበት ጊዜ ከ አንድ ዓመት በታች ከሆነ በአገልግሎት ዘመኑ ልክ ተመጣጣኝ የሆነ ዕረፍት በዚያው በአገለገለበት ዓመት ይሰጠዋል፡፡

1156/2011 አንቀጽ 77

Address

Asosa

Telephone

+251913389759

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mohammed mohamud legal Consultant posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mohammed mohamud legal Consultant:

Share