LAW Firm of Ethiopia

LAW Firm of Ethiopia በዚህ ገፅ፥ የሕግ መረጃዎችን፥ሕጎችንና መመሪያዎችን እንለዋወጣለን። ልምድና ዕውቀታችንን እንካፈልበታለን። 945888893

23/06/2026
23/06/2026

የሻንቶ ከተማ መጀመረያ ደረጃ ፍ/ቤት በዛቻ ወንጄል የተከሰሰውን ተከሳሽ በየቀኑ 1:00 ሰዓት ለ15 ተከታታይ ስራ ቀናት ፍ/ቤት ቅጥር ግብ የማስዋብ ሥርና ለችግኝ ጉድጓድ እንድቆፍር ዉሳኔ አሳለፈ ።
ተከሳሽ ወጣት አስፈው አየለ የወ/ል ህግ አንቀፅ 580 ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ በቀን 20/9/2018 ዓ.ም የወላጅ አባት የሆነውን ግል ተበዳይ በመዛቱ የዛቻ ወ/ል ክስ ቀርቦበት ፍ/ቤቱ ጉዳዩን በማስረጃ በማጣራት ችሎቱ በቀን 8/10/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ጥፋተኝነት ውሳኔ ከሰጠ በኃላ ተከሳሽን ያስተምራል በማለት አማራጭ ቅጣት በቀን 1:00 ሰዓት ለ 15 ሥራ ቀናት ፍ/ቤት ቅጥር ግብ ውስጥ ችግኝ ለመትከል ጉድጓድ እንድቆፍርና ግብ የማስዋብ ስራ እንድሰራ ውሳኔ ሰጥተዋል ።
የሻንቶ ከተማ ፖሊስ ውሳኔ ተከታትለው እንድያስፈፅም ትዕዛዝ ተሰጥቷል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት The South Ethiopia Supreme Court

The challenges faced by women and children are significant, and your determination to address these issues head-on is tr...
23/06/2026

The challenges faced by women and children are significant, and your determination to address these issues head-on is truly commendable.🙏🙏 Congratulations!💪💪

17/06/2026
17/06/2026
08/06/2026
ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳን በተመለከተ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ‎‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኦሮሚያ ክልል በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳ የዳኝነ...
05/06/2026

ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳን በተመለከተ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ

‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኦሮሚያ ክልል በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈከንሳ የዳኝነት ሥራቸዋን በሕግና በሙያ ሥነ-ምግባር መሠረት በማከናወን ላይ እያሉ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በባለጉዳይ በተፈጸመ የጦር መሣሪያ ጥቃት ሕይወታቸው በማለፉ የተሰማን ሐዘን ጥልቅ ነው::

‎የዳኞች ደህንነትና ነፃነት የፍትሕ ሥርዓቱ መሠረታዊ ዋስትና ሲሆን፣ ዳኞች ከማንኛውም ዓይነት ዛቻ፣ ጫና ወይም ጥቃት ነፃ ሆነው የሕግ ተግባራቸውን ማከናወን ይገባቸዋል። ሆኖም የተፈጸመው ድርጊት በአንድ ዳኛ ላይ የተፈጸመ ወንጀል ብቻ ሳይሆን በሕግ የበላይነት፣ በዳኝነት ነፃነት እና በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተቃጣ ከባድ ጥቃት እንደሆነ እንረዳለን።

‎እንዲህ አይነቱ በዳኞች ወይም በሌሎች የፍትሕ ሥርዓት ተዋናዮች ላይ የሚፈጸሙ የኃይል ድርጊቶች የሕግ የበላይነትን ለማዳከም የሚደረጉ ተግባራት እንደሆኑ በማመን በጽኑ እናወግዛለን።

‎ፍርድ ቤቱ ይህንን አሳዛኝ ድርጊት በጽኑ እያወገዘ፤ ጉዳዩ በሚመለከታቸው የሕግ አስከባሪ አካላት በፍጥነት፣ በተሟላ እና በግልጽ ሁኔታ እንዲጣራ እና ተጠያቂዎችም በሕግ ፊት እንዲቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

‎በተጨማሪም በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ዳኞችና ሌሎች የፍትህ ዘርፍ ባለሙያዎች ደህንነት እንዲጠናከር እና ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይደገሙ አስፈላጊ የጥበቃ እርምጃዎች እንዲወሰዱ እያሳሰብን፤ ፍርድ ቤቱ ለሟች ዳኛ ወርቄ ፈከንሳ ቤተሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ለመላው የፍትሕ ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።

‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
‎ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
👇

Address

Arba Minch'

Telephone

+251912670051

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when LAW Firm of Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to LAW Firm of Ethiopia:

Share