02/12/2025
“የጎራዴ ስልነቱ እና ጥንካሬው በፈሰሰበት እሳት እና በወደቀበት መዶሻ ልክ ነው!”
ተጠልፎ ወድቆ ወርቅ አፍሶ እንደሚነሳ ሰው እድለኛ ማነው? እሳት እና መዶሻስ ጎራዴን ስል ያደርጉት የለምን? ሰውስ ከመከራው ደንዳና በትር ምርኩዙን ያበጅ የለምን?... ከስቃዩ ጨካኝ ክንድስ የተፈተነና የነጠረ ጥበብን ይካን የለምን? ማን ነው እሳት ሳይበላው መዶሻ ሳያነኩተው ስል መኾን የሚቻለው?
መልካም ምሽት ይሁንላችሁ
ኢሳያስ ለማ