ካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/Kamba Town First Instance Court

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • ካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/Kamba Town First Instance Court

ካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/Kamba Town First Instance Court Kamba Town F/I/C Media Communication affairs

14/10/2025
የተከበራችሁ የፍ/ቤቱ ተገልጋዮችና የከተማው ነዋሪዎች የካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ከነሐሴ 1 2017ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2018ዓ.ም ድረስ የተወሰኑ ጉዳዮችን ብቻ እያዬ በከፊ...
08/08/2025

የተከበራችሁ የፍ/ቤቱ ተገልጋዮችና የከተማው ነዋሪዎች የካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ከነሐሴ 1 2017ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2018ዓ.ም ድረስ የተወሰኑ ጉዳዮችን ብቻ እያዬ በከፊል ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ እናሳውቃለን።

የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ከነሐሴ 1 ጀምሮ እስከ መስከረም 30 ድረስ በከፊል ዝግ ሆኖ ይቆያል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የካምባ ከተማ መጀመሪያ   ደረጃ ፍ/ቤት በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት ከ998 በላይ የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ተሰጠ።የካምባ ከተማ መጀመሪያ   ደረጃ ፍ/ቤት በ2017ዓ...
11/07/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት ከ998 በላይ የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ተሰጠ።

የካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ሰነድ ቀርቦ ውይይት በተደረገበት መድረክ የካምባ ከተማ መ/ደ/ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አክሊሉ ካሌብ እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ በፍትሐብሔር እና በወንጀል 1,011መዛግብት ቀርበዋል።

ከእነዚህ ከቀረቡ መዛግብት መካከል 998 መዛግብቶች ላይ ውሳኔ በመስጠት የዕቅዱን 98.7% መፈፀም ተችሏል ብለዋል። በተለያዩ የዳኝነት ሥራዎች ከ414,745 ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉንም ገልፀዋል ፡፡ የማጣራት አቅም 100%፣ በስታንዳርድ የመወሰን አቅም 99%፣የፋይሎች መጨናነቅ ወደ 1.01መቀነሱን፣ውጤታማነት መዝገብ የማፅናት አቅም 99%መሆኑን አክለው ገልፀዋል።

ያለ እድሜ ጋብቻ፣ አስገድዶ መድፈር፣ በሴቶች ላይ አካላዊ ጉዳት ማድረስ፣ ቀለብ የመሳሰሉ የክስ መዝገቦች ጉዳዮች፣ ሸማቾች፣ ህብረት ሥራ፣ የማይክሮ ፋይናንስ ብድር አመላለስ በበጀት ዓመቱ ውሳኔ የተሰጠባቸው መዝገቦች ውስጥ በልዩ ችሎትና ልዩ ኩረት ተሰጥቶ ስለተሰራ በአብዛኛው 100% አፈፃፀም መመዝገቡን ገልጸዋል።
አማራጭ ሙግት የዕርቅ አፈፃፀም 256 መዝገብ 100% ሲሆን የተገልጋይ እርካታና አመኔታ ከማረጋገጥ አንፃር የተሻለ አፈፃፀም የታየበት ዓመት መሆኑን፣ ለ16ሰዎች ነፃ የህግ ድጋፍና ለ432ሰዎች የነፃ ህግ ምክር ተሰጥቶ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ5891 ለሚበልጡ ባለ ጉዳዮችና ተገልጋዮች የንቃተ ህግ ትምህርትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች መሰጠቱንም አክለው ገልፀዋል።
በመጨረሻም የበጀት አፈፃፀም የተሻለ መሆኑን በማንሳት አስፈፃሚ መንግስት ላደረጉት ድጋፍ ከፍ ያለ ምስጋና በፍ/ቤቱና በሠራተኛው ስም በማቅረብ ቀጣይ የተሻለና ከፍ ያለ ደጋፍና ቅንጅት በሚፈልገው በፍ/ቤቱ ህንፃ ቆሞ የቀረውን ለማስቀጠል ቆርጠው ድጋፍ እንድያደርጉም ጥሪ በማቅረብ የአገልግሎት አሰጣጡን ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ ላይ የተደገፈ ቀልጣፋ ለማድረግ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን የማሟላት ክፍተት የነበረውን በመቅረፍ ረገድ በቅንጅት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚፈልግ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ከአጠቃላይ ሰራተኞችና ክትትል አቀራረብ ፖሊሶች የተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ላይ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ላይ ጥልቅ ውይይት ተደርጎ ምላሽ በመስጠት በ2018ዓ.ም ዕቅድ ላይ መክረው በቀጣይ በጀት ዓመት ፍርድ ቤቱ የውሳኔ አቅሙን በማሳደግ እና አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በመጨረሻ በዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞች ማበረታቻና ሰርቲፍኬት በመሸለም እና ሠራተኛው ከፍሎ ያጠናቀቀውን የህዳሴው ግድብ ማስጨረሻ የተቆጠበ ቦንድ በማስረከብ ተጠናቋል።

28/06/2025

👉የምስክርነት ግዴታና በችሎት የማጣራት አግባብነት በተመለከተ:-
በመሰረቱ አንድ ሰው ለምስክርነት ከተቆጠረ በፍ/ቤት መጥሪያ ትዕዛዝ እንደደረሰው ማሰብና ማወቅ ያለበት ለትክክለኛ ዳኝነት/ፍትሐዊ እውነተኛ ፍርድ እንዲሰጥ ዳኛውን እንድረዳ ፈጣሪ በፈጠረው አይኔና ጆሮዬ በሰጠኝ ሰላም ጤናና ጊዜ እድል ሰጥቶኛል በሚል ፅኑ እሳቤ ፍ/ቤት ሊቀርብ እንጂ የቆጠረውን ለማገዝ ቃለማሃላ ፈፅሞ መዋሸት ሆነ ለመመስከር አለመቅረብ በወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያከትል ህብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል። ለአንድ ጉዳይ ለምስክርነት የተቆጠረ ሰው በፍርድ ቤት ጥሪ መሠረት ቀርቦ የመመስከር ግዴታ ያለበት ሲሆን ምስክሩ ሊቀርብ ካልቻለም ፍርድ ቤቱ ተገቢ መስሎ በታየው መንገድ ትዕዛዝ በመስጠት ምስክሩ በሕግ አግባብ ተገዶ ወይም ታስሮ እንዲቀርብ በማዘዝ ምስክርነቱን በመስማትና ተገቢ ነው ካለም በሌላ ማስረጃም ጭምር በማጣራት ከውሳኔ በፍት ሙሉ ማጣራት በማድረግ የቀረበለት ጉዳይ ላይ ተገቢውን ዳኝነት ሊሰጥ የሚገባ ስለመሆኑ፣👉የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 116፣118(2)(ለ) እንዲሁም የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 22 በሰበር መዝገብ ቁጥር 153610 መመልከት ይቻላል። በመሆኑም ማንም ሰው በዳኝነት ፍትህ ስርዓት ላይ መስረጃ ሆኖ ተቆጥሮ ሆነ ሳይቆጠር ለማጣራት በፍ/ቤት መጥሪያ ሲደርሰው አንድም እውነት እንዲፈረድ እድለኝነት እድለኝነት ሊሰማው እንጂ እንዳይደናገጥ፣ እንዳይዋሽ ለህሊናው የተገዛ ከፍተኛ ኃላፍነት በዳኛውና ሌሎች ህግ ባለሙያዎች ልክ ሊሰማውና ልያግዝ እንዲገባ ግዴታም ጭምር ነው!!። ከፍ/ቤቱ!!

የታገተ ህፃን በብርበራ ትዕዛዝ ተገኘ!!👉የካምባ ከተማ ፖሊስ በቀን 10/10/2017ዓ.ም በጠየቀው መሠረት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ቴክኒካዊ ብርበራ እንዲደረግ ትዕዛዝ በተሰጠው መሠረት ፖሊስና...
17/06/2025

የታገተ ህፃን በብርበራ ትዕዛዝ ተገኘ!!
👉የካምባ ከተማ ፖሊስ በቀን 10/10/2017ዓ.ም በጠየቀው መሠረት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ቴክኒካዊ ብርበራ እንዲደረግ ትዕዛዝ በተሰጠው መሠረት ፖሊስና ፍ/ቤቱ ከህብረተሰቡ ጋር በጥምረት በተሰራው ስራ የ 3ዓመት ህፃን ናታን ቦጋለ በአንድ ግለሰብ ቤት ታስሮ ካለበት ከ19:00 ሰዓት ቦኋላ በመገኘቱ ወላጆች ፣ ቤተዘመድና ህብረተሰቡ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በቀጣይ ህብረተሰቡ ከእንደዚህ አይነት ድርጊቶች ህፃናትን በንቃት እንዲጠብቅና ከፍትህ አካላት ጋር በትብብር እንዲሰራ የፍ/ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ አክሊሉ ካሌብ አሳስበዋል።

ዛሬ በዋለው የወንጀል ችሎት በካምባ ሆስፒታል የመድሃኒት ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ!!በቁጥር 274/17 በቀን 22/8/2017ዓ.ም ዐቃቤ ህግ ባቀረበው ወንጀል ክስ ተከሳሾች የ...
29/05/2025

ዛሬ በዋለው የወንጀል ችሎት በካምባ ሆስፒታል የመድሃኒት ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ!!
በቁጥር 274/17 በቀን 22/8/2017ዓ.ም ዐቃቤ ህግ ባቀረበው ወንጀል ክስ ተከሳሾች የኢ/ፌ/ዲ/ሪ/ወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና 669(2)(ለ) ስር ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የህዝብና መንግስት ንብረት የሆነውን የገንዘብ ግምቱ 1,189.73(አንድ ሺ አንድ መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ብር ከ ሰባ ሦስት ሣንቲም) የሚያወጣ መድሃኒት በመንግስት ሥራ ምክንያት በእጃቸው የገባውን 17 Strip በ1ኛ ተከሣሽ የእጅ ቦርሳ ላይ በማስገባት ሊያወጡ ሲሉ በግድ የ1ኛ ተከሳሽ ቦርሳ ውስጥ ስለተገኘ ስለሆነ ከባድ ስርቆት ክስ ቀርቧል።
ተከሳሾች ፍ/ቤት ቀርበው የ1ኛ ጠበቃ ከባድ መሆን እንደሌለበት ያቀረበው መቃወሚያ በብይን ታልፎ የ2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ጠበቃ መቃዎሚያ ያላነሳ ስለሆነ የሦስቱን እምነት ክህደት ቃል ሲቀበል ወንጀሉን አልፈፀምንም በማለት ክደው ተከራክረዋል።
ፈ/ቤቱ የዐቃቤ ህግ ማስረጃና የተከሳሾች ማስረጃ በማዳመጥ መዝኖ ሦስተኛ ተከሳሽ ወ/ሮ እቴነሽ ኩሉን በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ149(2) መሰረት ነፃ በማውጣት፣ 1ኛ ተበሳሽ ሜሮን ቶና እና 2ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ደበበ ላይ በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ149(1) መሰረት ጥፋተኛ ናቸው በማለት ወስኗል።
ፍ/ቤቱ ቅጣት ሲሰራ ጥፋተኞችን ለማረም መሰሎችን ለማስተማር የህብረተሰቡን ጥቅምና ደህንነት በማስጠበቅ ዓላማ ቅጣት ሰርቷል። ፈ/ቤቱ ሊገኝ ከታሰበው ጥቅም አንፃር በማየት ቀላል እስራት ይዞ በቅጣት አወሳሰን መመሪያ 2/2006 አንቀጽ16 መሰረት ደረጃ 2 እርከን 13 ላይ በማረፍ የግራቀኝ አስተያየት ከሳሽ ዓቃቤ ህግ 3 ማክበጃ ካነሳው 2ተቀብሎ እርከን 15 ላይ በማረፍ የተከሳሾች ጠበቆች ካነሱት ለሁለቱም 1 ማቅለያ በመያዝ ወደ እርከን 14 ዝቅ በማለት በእርከኑ ስር ካለው ፍቅደ ስልጣን ጥፋተኞችን ያርማቸዋል ሌሎችንም ያስተምራል በማለት በ2 ዓመት ከ 8ወር ቀላል እስራት እንዲቀጡ ተውስኗል።

06/04/2025

የመንግስት ሰራተኞች የስነ-ምግባር ጥሰት እና የዲሲፕሊን እርምጃ አወሳሰድ

መግቢያ
ድስፕሊን የሚለው ቃል ስርዎ ቃሉ እንግሊዝኛ ቢሆንም ለተመሳሳይ አላማ በአማርኛም ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ከቃሉ አግባብ መረዳት እንደሚቻለው፣ ለአንድ ጥፋት የሚወሰድ የቅጣት እርምጃ መሆኑን መገመት ይቻላል። ቅጣት ያለጥፋት አይኖርም ተብሎ ይገመታል። ምንም እንኳን ሁልጊዜ ይህ ግምት ባይሠራም፣ በአመዛኙ ትክክል ይሆናል። ነገር ግን ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ተፈጸመ የተባለው ጥፋት በማስረጃ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህ ጠቅላላ አስተሳሰብ እንደተጠበቀ ሆኖ ከርእሱ አጻር፣ መታየት ያለበትን ጉዳይ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 አንቀጽ 96 እና ተከታዮቹ የተደነገገውን ቀጥለን እንመለከታለን።

ዓላማ
የዲስፕሊን ቅጣት ዓላማ የመንግሥት ሠራተኛው በፈጸመው የዲስፕሊን ጉድለት ተፀፅቶ በአመለካከቱና በሥነ-ምግባሩ እንዲታረምና ብቁ ሠራተኛ እንዲሆን ለማስቻል ወይም የማይታረም ሆኖ ሲገኝ ለማሰናበት እንደሆነ በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 አንቀጽ 96 ላይ ተደንግጓል፡፡ የዲስፕሊን ጉድለት የፈፀመ የመንግስት ሰራተኛ እንደ ጥፋቱ ክብደት የቃል ማስጠንቀቂያ፤ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ፤ እስከ አሥራ አምስት ቀን ደመወዝ የሚደርስ መቀጮ፤ እስከ ሦስት ወር ደመወዝ የሚደርስ መቀጮ፤ እስከ ሁለት ዓመት ለሚደርስ ጊዜ በሥራ ደረጃ እና ደመወዝ ዝቅ ማድረግ፤ ከሥራ ማሰናበት ቅጣቶች ሊወሰንበት እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 97 ላይ ተደንግጓል፡፡

የዲሲፕሊን ጥፋት አይነቶች
አዋጁ ሁለት አይነት የዲሲፕሊን ጥፋት አይነቶች እንዳሉ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ቀላል እና ከባድ የዲሲፕሊን ጥፋት ናቸው፡፡ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ቅጣቶች ማለትም የቃል ማስጠንቀቂያ፤ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ፤ እስከ አሥራ አምስት ቀን ደመወዝ የሚደርስ መቀጮ ለቀላል የዲሲፕሊን ጥፋቶች የሚጣሉ ሲሆን እስከ ሦስት ወር ደመወዝ የሚደርስ መቀጮ፤ እስከ ሁለት ዓመት ለሚደርስ ጊዜ በሥራ ደረጃ እና ደመወዝ ዝቅ ማድረግ፤ ከሥራ ማሰናበት ቅጣቶች ለከባድ የዲሲፕሊን ጥፋቶች የሚጣሉ ቅጣቶች ናቸው፡፡ ከሥራ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ በማድረግ የተቀጣ የመንግሥት ሠራተኛ የቅጣት ጊዜውን ሲያጠናቅቅ ሠራተኛው ከሚሰራበት ሥራ መደብ እና ደረጃ ቀጥታ ግንኙነት ባለው ጥፋት ምክንያት ከስራ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ ብሎ እንድሰራ ተቀጥቶ ካልሆነ በስተቀር ከመቀጣቱ በፊት ይዞት ከነበረው የሥራ መደብ ጋር ተመሳሳይ ክፍት የሥራ መደብ ካለ ያለምንም ተጨማሪ የደረጃ ዕድገት ሥነ-ሥርዓት፣ ከመቀጣቱ በፊት ይዞት ከነበረው የሥራ መደብ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ክፍት የሥራ መደብ ካልተገኘ ክፍት የሥራ መደቡ በተገኘ ጊዜ ያለምንም ተጨማሪ የደረጃ ዕድገት ሥነ-ሥርዓት፣ በሥራ መደቡ ላይ እንደሚመደብ ተደንግጓል፡፡

በአዋጁ አንቀጽ 97(5) መሰረት የመንግሥት ሠራተኛ በዲስፕሊን ከተቀጣ በኋላ ቅጣቱ በሪከርድነት ሊቆይና ሊጠቀስበት የሚችለው፣ ቀላል የዲስፕሊን ቅጣት ከሆነ ቅጣቱ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ ለሁለት ዓመት፣ ከባድ የዲስፕሊን ቅጣት ከሆነ ቅጣቱ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ ለአምስት ዓመት እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

ከባድ የዲስፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች ምን ምን እንደሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 98 ላይ በዝርዝር ተቀምጧል፡፡ በዚህም፡-
ሕጋዊ ትዕዛዝን ባለማክበር፣ በቸልተኝነት፣ በመለገም፣ ወይም ሆነ ብሎ የአሠራር ሥነ-ሥርዓት ወይም የመንግስትን ፖሊሲ ባለመከተል በሥራ ላይ በደል ማድረስ፤
ጉዳዮችን ሆን ብሎ ማዘግየት ወይም ባለጉዳዮችን ማጉላላት፤
ተቋምን አደጋ ላይ በሚጥል ተግባር መሠማራት ወይም ሥራ

Address

KAMBA
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ካምባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/Kamba Town First Instance Court posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category