Hiwot Yohannes Law Office

Hiwot Yohannes Law Office Lawyer (ጠበቃና የህግ አማካሪ)

12/05/2025

የወንጀል ክስ መቃወሚያ (objection to the charge)የወንጀል ስነ ስርአት ህግ ቁጥር አንቀጽ ፣130 የክሱን ማመልከቻ ስለመቃወም ሀ.በዚሁ ነገር ክስ በሌላ ፍርድ ቤት ተጀምሮ በቀጠሮ ያለ መሆኑን ወይም ለ.በዚሁ ክስ ቀድሞ ተከሶ ነጻ የወጣ ወይም የጥፋተኝነት ውሳኔ የተስጠበት ሐ.ክስ የቀረበበት ወንጀል በይርጋ ህግ የታገደ ወይም በምህረት አዋጁ ምህረት ይቅርታ የተደረገለት መ.ከሌሎች ወንጀለኞች ጋር በተከስስ ጊዜ ለብቻው ከሌሎች ተነጥሎ ባይታይለት የሚጎዳ መሆን። ሠ.ክሱን ለማቅረብ በህጉ መስረት ፈቃድ ያልተስጠ መሆኑ ረ.ለሌላው ችሎት የቀረበው ክስ ሳይፈጸም በዚህ የወንጀል ክስ ውሳኔ ሊስጥ የማይገባ መሆኑ። ስ.ለፈጸማቸው ተግባሮች ሀላፊ የመሆን በተመለከተ በ131 በተመለከተ መስረት

02/07/2024

#የመፋለም ክስ ( petitory action)

ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡

ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡

ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።

በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)

N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።

02/07/2024

ውል በተናጠል መሰረዝ /አንደኛው ተዋዋይ ወገን በተናጠል ውሉን መሰረዝ/ Unilateral Cancelation of Contact
====================
አንደኛው ተዋዋይ ወገን የፍታብሓር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን መሠረት በማድረግ ውልን በተናጠል ለመሠረዝ የሚችለው ከሚከተለት ሶስት ሁኔታዎች አንደኛው የተሟላ መሆኑን ለማስረዳት ሲችል ነው፡፡
• የመጀመሪያው ባለዕዳው በውሉ ላይ በተመለከተው መሠረት የውሉን ግዴታ የሚፈፅምበት ቁርጠኛ ጊዜ በውሉ ላይ በግልፅ ተመልክቶ እንደሆነና በውሉ ላይ የተገለፀው ቁርጥ የሆነ የውል መፈፀሚያ ጊዜ ያለፈ እንደሆነ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ አንደኛው ተዋዋይ ወገን በተናጠል ውሉን ለመሰረዝ የሚችል መሆኑን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1775(ለ) ድንጋጌዎች በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
• ሁለተኛው ምክንያት ባለዕዳው ውሉን ያልፈፀመበትን ምክንያትና ሌሎች የአካባቢ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ዳኞች ባለዕዳው ውሉን የሚፈፅምበት የችሮታ ጊዜ ከሰጡት በኋላ ባለእዳው በዳኛ ውሣኔ በተሰጠው የችሮታ ጊዜ ውስጥ ግዴታውን ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1770 ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡
• ሶስተኛው ባለገንዘቡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 በተደነገገው መሠረት ሌላኛው ተዋዋይ (ባለዕዳው) በውል የገባውን ግዴታ የሚፈፅምበትን ጊዜ በመግለፅ ማስጠንቀቂያ የሰጠ ሲሆንና በማስጠንቀቂያው በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳይፈፅም ሲቀር መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ለመረዳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ተዋዋይ ወገን ሌላኛው ተዋዋይ ወገን በውሉ መሠረት እንዲፈፅም ለመጠየቅና ማስጠንቀቂያ ለመስጠት የሚችለው በመጀመሪያ እሱ የበኩሉን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም የተዘጋጀ ሲሆን እንደሆነ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1857 በግልፅ ይደነግጋል፡፡
ስለሆነም ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ መሠረታዊ ዓላማና ግብ እንደዚሁም የድንጋጌውን የተፈፃሚነት ወሰን ለመረዳት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 ድንጋጌዎች ጋር በማጣመር መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ስንመዝነው አንደኛው ተዋዋይ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 ሌላኛው ተዋዋይ ውሉን እንዲፈፅምለት ለመጠየቅ፤ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 ድንጋጌዎች መሠረት የውል መፈፀሚያ ጊዜ ግልፅ ማስጠንቀቂያ በመስጠትና በፍትሐብሔር ቁጥር 1787 በተደነገገው መሠረት ውሉን በተናጠል ለመሠረዝ በመጀመሪያ በእሱ በኩል በውል የተጣለበትን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ በማስረጃ ለማረጋገጥ የቻለ መሆን እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌዎችን ይዘትና መሠረታዊ ግብ በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሕግ አውጭው በውል ለገባው ግዴታ ተገዥ በመሆን በእሱ በኩል ያለውን ግዴታ ያልፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑን በበቂ ሁኔታ ለማረጋገጥ ያልቻለ አንድ ተዋዋይ ወገን ሌላኛውን ተዋዋይ ወገን ቀድሞ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውሉን በተናጠል እንዲሰርዝ በማሰብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን አውጇል ተብሎ አይገመትም፡፡ አንድ ተዋዋይ የውሉን መፈፀሚያ የጊዜ ገደብ በመግለጽ ለሌላኛው ወገን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውል በተናጠል ለመሰረዝ የሚችለው በመጀመሪያ እሱ በውሉ የገባውን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 57280 ቅጽ 13፣ ፍ/ህ/ቁ. 1770፣ 1771፣ 1774፣ 1757፣ 1787

02/07/2024

በጠበቃ ተወክሎ ፍቺ ክስ ማቅረብ እና መከራከር ይቻላል?

⚖️የሰ/መ/ቁ.150408፡-ጋብቻ ለመፈጸም በልዩ ሁኔታ በውክልና እንደሚቻል ህጉ እየፈቀደ የፍቺ ጥያቄ ፍርድ ቤት የባልና ሚስትን ክርክር በሚያይበት ጊዜ እንደነገሩ ሁኔታ አስፈላጊ ሁኖ ካገኘው ባልና ሚስቱን በአንድነት ወይም በተናጠል ሲያነጋግር ወይም ጉዳዩን ሲመረምርና ምስክር ሲሰማ በዝግ ችሎት ያስችላል የሚለውን የቤተሰብ ህጉን ድንጋጌ አንቀጽ 110/ በመጥቀስ ጋብቻና ፍች በውክልና ሊጠየቅ አይችልም በሚል የሚቀርብ ክርክር ተገቢነት የለዉም፡፡

⚖️ምክንያቱም ፍርድ ቤቱ ተጋቢዎችን በአካል የሚያነጋግራቸው አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እንጂ የግድ ማነጋገር እንዳለበት የሚደነግግ ባለመሆኑ እና ጋብቻ በእንደራሴ መፈጸም በመርህ ደረጃ የማይቻል ቢሆንም ከተጋቢዎች አንደኛው ጋብቻውን ለመፈጸም ፈቃዱን በማያሻማ ሁኔታ በመግለጽ በግንባር ለመገኘት የማያስችለው ከባድ ምክንያት ሲያጋጥመው ጉዳዩ ለፍትህ ሚኒስትሩ ቀርቦ ሲረጋገጥ ጋብቻውን በእንደራሴ አማካኝነት መፈጸም እንደሚቻል በግልጽ በተሻሻለው የፌደራል ቤተሰብ ህግ አንቀጽ 12 ተደንግጓል፡፡

⚖️በመሆኑም የተሰጠው የውክልና ማስረጃ ይዘት በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.58 እና በፍ/ብ/ህ/ቁ.2199 ተወካዩ ፍቺን ጨምሮ በማናቸውም ጉዳዮች ወክሎ ለመከራከርም ሆነ ሌላ የህግ ባለሙያ ለመወከል እንደሚችል በውክልና ሰነዱ ላይ በግልጽ የተመለከተ ከሆነ ፍች በዉክልና በ አይጠየቅም ተብሎ ሊከለከል አይገባም፡፡

02/07/2024

የውል ይርጋ
---------------
1)የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1810(2) ላይ የተመለከተው የይርጋ ገደብ ተፈፃሚ የሚሆነው ውል በፈቃድ ጉድለት ወይም በችሎታ ማጣት የተነሳ እንዲፈርስ ጥያቄ የቀረበ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህቁ 1810 የሰ/መ/ቁ 48012 ቅፅ 12
2)በውል ግንኑነት ውስጥ የራስን ግዴታ ሳይወጡ ሌላው ወገን ግዴታውን አልተወጣም በሚል የሚቀርብ ክስ ተቀባይነት የሌለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1757 በሰ/መ/ቁ 39568 በቅፅ 12
3)የማይንቀሳቀስ ንብረት ሻጭ በዉሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ለገዢ ያላሳወቀ እንደሆነ ገዥ ውሉ እንዲፈፀምለት የመጠየቅ መብቱ በ10 ዓመት ይርጋ የሚታገድበት ስለመሆኑ 1845;1789:1731:1732 የሰ/መ/ቁ 38935 ቅፅ 12
4)የፍትሐብሄር ጉዳዮች የ ይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ግዴታውን ለመጠየቅ ተገቢ ከሆነው ጊዜ ጀምሮ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1846 የሰ/መ/ቁ 36756 ቅፅ 12
5)የፀና የውል ግዴታ የገባ ሰው ውሉ በፍርድ እንዲሰረዝ ለመጠየቅ የሚችለው ሌላኛው ተዋዋይ ወገን ግዴታውን በአግባቡ ያልፈፀመ(ያልተወጣ) እንደሆነ ወይም የፈፀመው ፍፁም ባልሆነ አኳኃን ከሆነ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1784;1785(2).(1)"የሰ/መ/ቁ 66935 ቅፅ 13 ላይ ሰፍሯል።

02/07/2024

ከዳግም ዳኝነት /review of judgement/ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጣቸው አስገዳጅ ውሳኔዎች

✅ቅጽ 6 የሰ/መ/ቁ 08751
በፍብ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 6 መሠረት ፍርድ ከተሰጠ በኋላ የተሰጠውን ፍርድ ሊያስለውጥ የሚችል አዲስ ማስረጃ መገኘቱ ብቻውን ዳግም ዳኝነት እንዲታይ የማያስችል ሲሆን ፍርዱን እንደገና ለማየት የተገኘው ማስረጃ ሀሰተኛ ሰነድ፣ በሀሰት የተሰጠ የምስክር ቃል፣ መደለያ ወይም ወንጀል ጠቀስ ተግባር ሆኖ ይህ አዲስ የተገኘው ማስረጃ የውሳኔውን መሠታዊ ይዘት የሚነካ መሆን አለበት። አዲስ የተገኘው ማስረጃ ፍርድ ቤቱ በጭብጥነት ይዞ ውሳኔ ከሰጠበት ጉዳይ ውጭ ከሆነ ጉዳዩ በዳግም ዳኝነት ሊታይ አይችልም።

✅ቅጽ 9 የሰ/መ/ቁ 42871
የዳግም ዳኝነት አቤቱታ በፍብ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 6 መሰረት የቀረበለት ፍርድ ቤት ዳኝነቱ ድጋሜ ሊታይ ይገባል ወይም አይገባም በማለት በሚሰጠው ውሳኔ ላይ አመልካች የሰበር አቤቱታ ከሚያቀርብ በስተቀር ይግባኝ የማቅረብ መብት የለውም።

✅ቅጽ 9 የሰ/መ/ቁጥር 43821
በዚህ መዝገብ ቁጥር የሰበር ችሎት በመ/ቁጥር 16624 የያዘውን አቋም ማለትም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 6 መሰረት የዳግም ዳኝነት ጥያቄ መቅረብ ያለበት ይግባኝ ከመቅረቡ በፊት እንጂ በይግባኝ ቀርቦ ውሳኔ ባገኘ ጉዳይ አይደለም በማለት የሠጠው የሕግ ትርጉም በመለወጥ የዳግም ዳኝነት ጥያቄ ጉዳዩ በይግባኝ ታይቶ ውሳኔ ከተገኘ በሁዋላም ቢሆን በቁጥር 6 ስር የተመለከቱት መመዘኛዎች ተሟልተው እስከተገኙ ድረስ መቅረብ እንደሚችል ገልጾ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡

✅ቅጽ 15 የሰ/መ/ቁ 93137
በሀሰተኛ ማስረጃ ወይም በመደለያ ምክንያ ባለጉዳዩን የሚጎዳ ውሳኔ የተሰጠው በሰበር ችሎት ከሆነ የዳግም ዳኝነት ጥያቄ በመርህ ደረጃ የሚስተናገደው ውሳኔውን ለሰጠው ፍርድ ቤት ቢሆንም አንድ ጉዳይ በዳግም ዳኝነት በሚታይበት ግዜ ፍሬነገርን የማጣራትና ማስረጃን የመመዘን ሒደት ስለሚያካትት ፍሬነገርን የማጣራትና ማስረጃን የመመዘን ስልጣን ደግሞ ለሰበር ችሎት ያልተሰጠው በመሆኑ የደግም ዳኝነት ጥያቄ በሰበር ችሎት ሊስተናገድ አይችልም። ስለዚህ የዳግም ዳኝነት አቤቱታው ሊስተናገድ የሚገባው ፍሬነገርን የማጣራትና ማስረጃን የመመዘን ስልጣን በተሰጣቸው ፍርድ ቤቶች መሆን አለበት።

✅ቅጽ 19 የሰ/መ/ቁ 104028
በፍብ/ስ/ሰ/ህ/ አንቀፅ 6 ስር የተመለከቱት አስፈላጊ መስፈርቶች በተሟሉበት ሁኔታ አንድ ክስ በይርጋ መዘጋቱ ዳግም ዳኝነት ጥያቄውን ላለማስተናገድ እንደበቂ ምክንያት የማይወሰድበት ነው።

02/07/2024

የጋብቻ ውል በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት እና በ4(አራት) ምስክሮች 2(ሁለት) በባል ወገን 2(ሁለት) በሚስት ወገን ካልፈረሙበት በስተቀር ውጤት እንደማይኖረዉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ.174623 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቶበታል።

Address

Adis

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hiwot Yohannes Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share