26/04/2026
⚖️⚖️⚖️በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መሠረት አንድን ሸቀጥ ማከማቸት ወይም ማጓጓዝ ወንጀል የሚሆነው ሸቀጡ እጥረት ያለበት መሆኑ በሚኒስቴሩ በወጣ የሕዝብ ማስታወቂያ ሲገለጽ ብቻ ነው ሰመቁ 266087
የክርክሩ መነሻ 👉🏿አመልካች በመኪና የፓልም የምግብ ዘይት ጭነው ሲጓጓዙ በፖሊስ ተያዙ። ዓቃቤ ሕግ አመልካቹን በሁለት ወንጀሎች ከሰሰ፦
👉የመጀመሪያ ክስ፦ በገበያ ላይ እጥረት ያለበትንና በመንግሥት ድጎማ የሚቀርብን ዘይት ከመደበኛው የንግድ አሠራር ውጪ ማጓጓዝ።
👉ሁለተኛ ክስ፦ ድርጊቱን ሕጋዊ ለማስመስል የሐሰት ደረሰኝ መጠቀም።
👉የሥር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ቅጣት
• አመልካቹ ጥፋተኛ ነው ተብሎ 4,500.00 ብር መቀጮ እንዲከፍል።
👉ዘይቱን ሲያጓጉዝበት የነበረው መኪና በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መሠረት ለመንግሥት እንዲወረስ።
✅✅✅✅✅የሰበር ሰሚ ችሎት ትንተና እና ውሳኔ
👉ሕጋዊነት (Principle of Legality)፦ አንድ ድርጊት ወንጀል ሊባል የሚችለው በሕግ በግልጽ "ወንጀል" ተብሎ ሲደነገግ ብቻ ነው።
👉የመንግሥት መመሪያ፦ በወቅቱ የነበረው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር የምግብ ዘይት እንደማንኛውም ሸቀጥ በነፃነት እንዲዘዋወር እና ሽያጩ እንዳይስተጓጎል መመሪያ አውጥተው ነበር።
👉እጥረት አለመታወጁ፦ በሕጉ መሠረት አንድን ዕቃ ማጓጓዝ ወንጀል የሚሆነው "እጥረት ያለበት መሆኑ በሕዝብ ማስታወቂያ ሲገለጽ" ነው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ግን እንዲህ ያለ ማስታወቂያ አልወጣም።
👉የመኪና መወረስ፦ መኪና ሊወረስ የሚችለው ዕቃ ለመደበቅ ተሻሽሎ ከተሠራ ወይም ባለቤቱ ወንጀል መሆኑን እያወቀ እንዲፈጸም ከፈቀደ ብቻ ነው። በዚህ ጉዳይ ግን ድርጊቱ ራሱ ወንጀል ሆኖ አልተገኘም==