Voice of Justice - የፍትህ ድምፅ

Voice of Justice - የፍትህ ድምፅ we are the voice of judges, prosecutors and victims of injustice in our justice system.

VOJ is established by different groups of prosecutors, judges, legal practitioners, and attornys for the aim of changing the problems incurred in our justice system specially in Amhara Region. we are also struggling the maladministration of the justice organs specially Courts and General Attorney organs. we are fighting for the creation of strong, independent and accountable justice organ.

⚖️⚖️⚖️በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መሠረት አንድን ሸቀጥ ማከማቸት ወይም ማጓጓዝ ወንጀል የሚሆነው ሸቀጡ እጥረት ያለበት መሆኑ በሚኒስቴሩ በወጣ የሕዝብ ማስታወቂያ ሲገለጽ ብቻ ነው ሰመቁ ...
26/04/2026

⚖️⚖️⚖️በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መሠረት አንድን ሸቀጥ ማከማቸት ወይም ማጓጓዝ ወንጀል የሚሆነው ሸቀጡ እጥረት ያለበት መሆኑ በሚኒስቴሩ በወጣ የሕዝብ ማስታወቂያ ሲገለጽ ብቻ ነው ሰመቁ 266087

የክርክሩ መነሻ 👉🏿አመልካች በመኪና የፓልም የምግብ ዘይት ጭነው ሲጓጓዙ በፖሊስ ተያዙ። ዓቃቤ ሕግ አመልካቹን በሁለት ወንጀሎች ከሰሰ፦
👉የመጀመሪያ ክስ፦ በገበያ ላይ እጥረት ያለበትንና በመንግሥት ድጎማ የሚቀርብን ዘይት ከመደበኛው የንግድ አሠራር ውጪ ማጓጓዝ።
👉ሁለተኛ ክስ፦ ድርጊቱን ሕጋዊ ለማስመስል የሐሰት ደረሰኝ መጠቀም።
👉የሥር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ቅጣት
• አመልካቹ ጥፋተኛ ነው ተብሎ 4,500.00 ብር መቀጮ እንዲከፍል።
👉ዘይቱን ሲያጓጉዝበት የነበረው መኪና በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መሠረት ለመንግሥት እንዲወረስ።
✅✅✅✅✅የሰበር ሰሚ ችሎት ትንተና እና ውሳኔ
👉ሕጋዊነት (Principle of Legality)፦ አንድ ድርጊት ወንጀል ሊባል የሚችለው በሕግ በግልጽ "ወንጀል" ተብሎ ሲደነገግ ብቻ ነው።
👉የመንግሥት መመሪያ፦ በወቅቱ የነበረው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር የምግብ ዘይት እንደማንኛውም ሸቀጥ በነፃነት እንዲዘዋወር እና ሽያጩ እንዳይስተጓጎል መመሪያ አውጥተው ነበር።
👉እጥረት አለመታወጁ፦ በሕጉ መሠረት አንድን ዕቃ ማጓጓዝ ወንጀል የሚሆነው "እጥረት ያለበት መሆኑ በሕዝብ ማስታወቂያ ሲገለጽ" ነው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ግን እንዲህ ያለ ማስታወቂያ አልወጣም።
👉የመኪና መወረስ፦ መኪና ሊወረስ የሚችለው ዕቃ ለመደበቅ ተሻሽሎ ከተሠራ ወይም ባለቤቱ ወንጀል መሆኑን እያወቀ እንዲፈጸም ከፈቀደ ብቻ ነው። በዚህ ጉዳይ ግን ድርጊቱ ራሱ ወንጀል ሆኖ አልተገኘም==

24/04/2026

ተሽከርካሪዎ እንዳይወረስ በሰበር የተሰጠ ውሳኔ
~~
የፌዴራል ሰበር/መዝ/ቁ 204922
~~
በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀጽ 147 (3) ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ ሕጉ ኮንትሮባንድ የጫነ ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያዝዘው በተሽከርካሪው አካል ላይ የዕቃ መደበቂያ ተሰርቶበት መገኘቱ ሲረጋገጥ ብቻ መሆኑ የተወሰነበት የህግ ትርጉም
~~
አንድ ተሽከርካሪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ እንዲያስችል ተደርጎ አካሉ ተለውጦ (ሻግ ተበጅቶለት) ከተገኘ፣ ባለንብረቱ ድርጊቱን "አላውቅም" ቢል እንኳ ተሽከርካሪው ተወርሶ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን አጽንቷል።

በዚህ ረገድ ባለንብረቱ ስለ ድርጊቱ አስቀድሞ ማወቁ ወይም አለማወቁ በሕጉ ፊት ዋጋ የማይሰጠው በመሆኑ፣ ተሽከርካሪው የመንግስት ንብረት ሆኖ እንዲመዘገብ የተሰጠውን ውሳኔ ሰበር ሰሚ ችሎቱ አጽንቶታል።

ይህ ውሳኔ የመኪና ባለንብረቶች ለተሽከርካሪዎቻቸው ጥንቃቄና ክትትል እንዲያደርጉ የሚያሳስብ ጠንካራ የሕግ መልዕክት ያስተላልፋል።

በ7 (ሰባት) ዳኞች የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 246230መጋቢት 25/2018ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 186946 የተሰጠው ውሳኔ ‘‘በአንድ ቦታ ላይ ሁለት የተለያዩ ሰዎች የይዞታ ማ...
10/04/2026

በ7 (ሰባት) ዳኞች የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤
መዝገብ ቁጥር 246230
መጋቢት 25/2018

ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 186946 የተሰጠው ውሳኔ ‘‘በአንድ ቦታ ላይ ሁለት የተለያዩ ሰዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቢኖራቸው አንደኛው ቤት ቢሰራ ሌላኛው ወገን በይዞታዬ ላይ እየተቃወምኩኝ ቤት ስለሰራ ያፍርስልኝ በማለት መጠየቅ የማይችል መሆኑን’’ የሚገልጸው ውሳኔ ተለውጧል፡፡

7 (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት መዝገብ ቁጥር 246230
“በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ186946 በሚያዝያ 26/2013 ዓ.ም የተሰጠው አስገዳጅ ትርጉም እና ሌሎች መዝገቦች ላይ የተያዘዉ ተመሳሳይ አቋም ተለውጦ፤ በአንድ ባለይዞታ ሊመዘገብ የሚገባን የከተማ ይዞታ ከአንድ በላይ የሆነ የይዞታ ማረጋገጫ ወይም ካርታ ለተለያዩ ሰዎች ተደርቦ ተሰጥቶ ሲገኝ ለቦታው ባለመብትነት ቅድሚያ የሚሰጠው መጀመሪያ ያስመዘገበው ሰው ነው’’ በሚል ተተርጉመዋል፡፡

የተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ህጋዊነት እና ማስረጃ አቀራረብ ~~~በሰበር መ/ቁ 283524 በቀን 27/05/2018 ዓ.ም ~መኪና ሲገዙ ወይም ሲሸጥ በውልና ማስረጃ በኩል ሳያረጋግጡ በመንደር ውል ...
08/04/2026

የተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ህጋዊነት እና
ማስረጃ አቀራረብ
~~~
በሰበር መ/ቁ 283524
በቀን 27/05/2018 ዓ.ም
~
መኪና ሲገዙ ወይም ሲሸጥ በውልና ማስረጃ በኩል ሳያረጋግጡ በመንደር ውል መደረጉ ያለው እጣ ፈንታ በተለይም ግለሰቡ (ተጠሪ) ከአንድ ሻጭ (አመልካች) ጋር የመኪና ሽያጭ ውል ተፈራርመው፣ ከፊል ክፍያ ፈጽመውና መኪናውን ተረክበው ለዓመት ያህል ሲጠቀሙ ይቆያሉ ። ነገር ግን ሻጭ መኪናውን በሌላ ቁልፍ ከፍተው በመውሰድ "አልሸጥኩም፣ እንዲያስተዳድሩልኝ ውክልና ነው የሰጠኋቸው" በማለት በመካድ ተከራክረዋል ። በሰበር ሰሚ ችሎትም መኪና እንደ ተራ ንብረት ሳይሆን እንደ "ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት" የሚቆጠር በመሆኑ፣ ዝውውሩ በህግ ፊት እንዲጸና በሚመለከተው የመንግስት አካል ዘንድ መመዝገብና መረጋገጥ አለበት ። በተጨማሪም የመኪና ሽያጭ መኖሩን ለማረጋገጥ በሚመለከተው አካል የተረጋገጠ የሽያጭ ሰነድ ማቅረብ እንጂ በሰው ምስክር ብቻ ማረጋገጥ የማይቻል ስለመሆኑ።

≈≈ሰ/መ/ቁ.224265 ≈≈(ሕዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም)---ከሳሽ የሆነ ወገን አስቀድሞ የሚመጣውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አውቆ በክሱ ጊዜ ማስረጃ ማያያዝ ነበረበት ማለት የማይቻል እ...
25/03/2026

≈≈ሰ/መ/ቁ.224265 ≈≈
(ሕዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም)
---
ከሳሽ የሆነ ወገን አስቀድሞ የሚመጣውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አውቆ በክሱ ጊዜ ማስረጃ ማያያዝ ነበረበት ማለት የማይቻል እና ለቀረበበት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ማስተባበያ እንዲሆነው ከሳሽ የሆነ ወገን አስቀድሞ በክሱ ካቀረበው ማስረጃ በተጨማሪ ሌላ ማስረጃ ማቅረብ እንደሚችል የተሰጠ የህግ ትርጉም።

25/03/2026
የተከሰሰበት ድንጋጌ ከፍተኛ ቅጣት የሚያስቀጣ መሆኑ ብቻ ተከሳሽ በዋስትና ቢለቀቅ ቅጣቱን በመፍራት ግዴታውን አክብሮ ሊቀርብ አይችልም በሚል ዋስትናን ለመከልከል ምክንያት አይደለም።
25/03/2026

የተከሰሰበት ድንጋጌ ከፍተኛ ቅጣት የሚያስቀጣ መሆኑ ብቻ ተከሳሽ በዋስትና ቢለቀቅ ቅጣቱን በመፍራት ግዴታውን አክብሮ ሊቀርብ አይችልም በሚል ዋስትናን ለመከልከል ምክንያት አይደለም።

`````````*የሰ/መዝ/ቁ 266998*```````                 የካቲት 26/2018ዓ.ም #ላልተሰራ-ስራ-የሚከፈል-ደመወዝ-ስላለመኖሩ~~~በትግራይ ጦርነት ምክንያት ስራ በመቆሙ ...
07/03/2026

`````````*የሰ/መዝ/ቁ 266998*```````
የካቲት 26/2018ዓ.ም
#ላልተሰራ-ስራ-የሚከፈል-ደመወዝ-ስላለመኖሩ
~~~
በትግራይ ጦርነት ምክንያት ስራ በመቆሙ አሰሪው ሰራተኛውን ስራ ለማሰራት የማይችልበት በቂ ምክንያት በመሆኑ አሰሪው የስራ ዉሉን ባያቋርጥም ላልተሰራ ስራ ደመወዝ የሚከፈልበት አግባብ ስለሌለ በዚህ ወቅት የሚጠየቅ የደመወዝ ክፍያ የህግ መሰረት የሌለው ስለመሆኑ

👉 የግል ተበዳዩ ድርጊቱ ሕገ-ወጥ መሆኑን እያወቀ የወንጀል ፍሬ ተካፋይ ነኝ በሚል ስሌት ውስጥ ገብቶ ንብረቱን ቢያጣ ሕጉ እንደ ንጹህ ተበዳይ ስለማይቆጥረው የማታለል ወንጀል ተፈፅሟል ለማለ...
07/03/2026

👉 የግል ተበዳዩ ድርጊቱ ሕገ-ወጥ መሆኑን እያወቀ የወንጀል ፍሬ ተካፋይ ነኝ በሚል ስሌት ውስጥ ገብቶ ንብረቱን ቢያጣ ሕጉ እንደ ንጹህ ተበዳይ ስለማይቆጥረው የማታለል ወንጀል ተፈፅሟል ለማለት የሚቻል አይደለም።
👉የሰ/መዝገብ ቁጥር 231232
~~~~ቅፅ 28~~~~~

~~~ሰ/መ/ቁ.214515~~~ ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ/ም            ያልታተመ~~የቤት ሽያጭ ውልን መነሻ በማድረግ ተከሳሽ ውልና ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጽ/ቤት ቀርበው ...
07/03/2026

~~~ሰ/መ/ቁ.214515~~~
ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ/ም
ያልታተመ
~~
የቤት ሽያጭ ውልን መነሻ በማድረግ ተከሳሽ ውልና ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጽ/ቤት ቀርበው ውል እንዲፈርሙልኝ፣ ፈርመው ቤቱን ወደ ከሳሽ ስም እንዲያዞሩ፣ ቤቱን በውሉ መሰረት እንዲያስረክቡኝ የሚል ክስ መነሻው ውል ይፈርሙልኝ በሚል የሚቀርብ ክስ በመሆኑ በፍ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 231(1)(ሀ) መሰረት የክስ ምክንያት የለዉም፡፡
~~
እንዲህ አይነት ክስም ከመነሻውኑ ከሳሽ ዉል የሌለው መሆኑን በማመን ያቀረበው ከመሆኑ በላይ ውል በተዋዋይ ወገኖች ነጻ ፍቃድ የሚፈጸም ሆኖ እያለ ተከሳሾች በፍርድ ሃይል ተገደው በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት ቀርበው እንዲዋዋሉ የሚያደርግ ውጤት ያለዉ ስለሆነ የክስ ምክንያት የለውም።

~~~~የቅርብ ውሳኔ~~~~በዋስትና የመለቀቅ መብት~~`~~ተከሳሽ የዋስትና ግዴታውን እንደማይፈጽም የሚያረጋግጥ በቂ ምክንያት ስለመኖሩ በአመላካች ማስረጃ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ:-        ...
07/03/2026

~~~~የቅርብ ውሳኔ~~~~
በዋስትና የመለቀቅ መብት
~~`~~
ተከሳሽ የዋስትና ግዴታውን እንደማይፈጽም የሚያረጋግጥ በቂ ምክንያት ስለመኖሩ በአመላካች ማስረጃ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ:-
*የተበዳይ ዕድሜን አነስተኛነት፣
*ወንጀሉ ከፍ ያለ ቅጣት የሚያቀጣ መሆኑን፣
*ወንጀሉ በማ/ሰቡ ዘንድ የተወገዘ ስለሆነ ተከሳሽን ከወዲሁ በዋስ መልቀቅ አስተማሪ አይደለም" የሚሉ ድምዳሜዎች ላይ በመድረስ ዋስትናን መንፈግ የዋስትና መብትን ሕገ መንግሥታዊ መርህነትን ሸርሽሮ ወደ ልዩ ሁኔታነት የሚቀይር እና የተከሳሽንም ከፍርድ በፊት ጥፋተኛ ሆኖ ያለመቆጠር መብትን የሚጥስ በመሆኑ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት ስለመሆኑ የተሰጠ የህግ ትርጉም።
~~~ሰ/መ/ቁ. 292349 ~~~
~~(የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም) ~~

Address

Justice
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Voice of Justice - የፍትህ ድምፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category