05/08/2026
®በዳኞች አስተዳደር አብይ ጉባዔ የሚወሰን የዳኞች የስንብት ዉሳኔ ምክር ቤት ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት ፍርድ ቤት ቀርቦ የመታየቱ ጉዳይንም ይህ የህገ መንግስት ትርጉም ያካትተው ይሆን?
® የዳኞች የስንብት ውሳኔ ምክር ቤት ከመቅረቡ በፊት በይግባኝም ሆነ በሰበር ቀርቦ እንዳይመዘን የተደረገበት አመክንዬ ምንድን ነው?
~~~
የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 1ኛ መደበኛ ጉባዔ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም መ/ቁ 142/17 በሰጠው ውሳኔ፣ ማንኛውም የመንግስት አካል የሚያወጣቸው ሕጎች የትኛውም መስሪያ ቤት ወይም የስራ ሃላፊ በሠራተኞች ላይ የሚሰጠው የስንብት ውሳኔ በፍርድ ቤት ወይም በዳኝነት አካላት ዘንድ ቀርበው እንዳይታዩና ውሳኔ እንዳያገኙ መከልከል ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37(1) ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው ተፈጻሚነት እንዳይኖራቸው የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ አስተላልፏል፡፡