ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት kolfe keranio youth and sport office

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት kolfe keranio youth and sport office

ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት  kolfe keranio youth and sport office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት kolfe keranio youth and sport office, Legal, Kolfe keranio betel, Addis Ababa.

ዜና ሹመት :-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አቶ አሰግደዉ ኃይለ ጊዮርጊስን ከየካቲት 20 /2018 ዓ.ም. ጀምሮ የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾሟል።ለተሾሙት አመ...
02/03/2026

ዜና ሹመት :-
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አቶ አሰግደዉ ኃይለ ጊዮርጊስን ከየካቲት 20 /2018 ዓ.ም. ጀምሮ የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾሟል።

ለተሾሙት አመራር መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

"የአድዋ አደራ፣ አንድነት ለሉዓላዊነትና ማንሰራራት"  በሚል መሪ ቃል 130ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን አስመልክቶ በክፍለ ከተማው ከወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።ኮልፌ ኮሙኒኬሽን የካቲ...
17/02/2026

"የአድዋ አደራ፣ አንድነት ለሉዓላዊነትና ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል 130ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን አስመልክቶ በክፍለ ከተማው ከወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን የካቲት 10/2018ዓ.ም

በክፍለ ከተማው አስተዳደር "የአድዋ አደራ፣ አንድነት ለሉዓላዊነትና ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የ130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ ከወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በውይይት መድረኩ አቶ ሳሙኤል አበበ የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅህት ቤት ኃላፊ በዓሉን የሚዘክር ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት የአድዋ ድል የኢትዮጵያውያን የነፃነትና የብሔራዊ ክብር መገለጫ መሆኑን ገልፀው ድሉ ለዛሬው ሀገራዊ ግንባታና ለነገው ብሔራዊ ከፍታ እንደ መነሻ ያገለግላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው ጨምረውም የአድዋ ድል በዓል ታሪክ የሚዘከርበት ብቻ ሳይሆን ወጣቶች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ጀግንነት የሀገራችንን ብልፅግና እውን በማድረግ ታሪክን ማስቀጠልና ታሪክን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

በመድረኩ ከሁሉም ወረዳ የተውጣጡ የወጣት አደረጃጀት አባላት የተሳተፉ ሲሆን አቶ ሳሙኤል አበበ የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅህት ቤት ኃላፊ ፣ የብልፅግና ፓርቲ የክፍለ ከተማው ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ ሰብሳቢ ወጣት ሀይማኖት ዝናቡ፣የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የክፍለ ከተማው ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ሲሳይ ሙሊሳ መድረኩን መርተውታል፡፡

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ሌሎች ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፦
https://linkmix.co/48811202

22/01/2026
ክፍለ ከተማ ዓቀፍ  15 ኛው የባህል ስፖርት ውድድር ፌስቲቫል ተካሔደ።ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ታህሳስ 13/ 2017ዓ.ምክፍለ ከተማ ዓቀፍ  15 ኛው የባህል ስፖርት ውድድር ፌስቲቫል የክፍለ ከተማ...
22/12/2024

ክፍለ ከተማ ዓቀፍ 15 ኛው የባህል ስፖርት ውድድር ፌስቲቫል ተካሔደ።

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ታህሳስ 13/ 2017ዓ.ም

ክፍለ ከተማ ዓቀፍ 15 ኛው የባህል ስፖርት ውድድር ፌስቲቫል የክፍለ ከተማው የወጣቶችና ስፖርት የባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ፅ/ቤቶች በጋራ የተዘጋጀ ነው።

በዛሬው እለትም በክፍለ ከተማው ወረዳ 07 ሮም ሜዳ በተካሔደው ክፍለ ከተማ ዓቀፍ 15ኛው የባህል ስፖርት ውድድርና ፌስቲቫል ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኒዕመተላህ ከበደ፣አቶ ሙልጌታ ጉልማ የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊና ሌሎች አመራሮች፣የስፖርት ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድር ውጤታማ ስፖርተኞችን የመለየት ስራ ይሰራልም ተብሏል ፡፡

የባህል ስፖርት ውድድሩ ፌስቲቫሉ ባህላዊ ስፖርቶች ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፉ ሚና እንደሚኖረው የተመላከተ ሲሆን ውድድሩም በገና ጨዋታ፤ገበጣ ባላ12፤18 ኩርባ፤ትግል ፤ቡቡ፤ፈረስ ሸርጥ እና በሌሎችም የባህል ስፖርት ዓይነቶች ውድድር ተካሔዷል።

በሮም ሜዳ በተካሔደው መርሃ ግብርም በብሄር ብሄረሰቦች የህብረት ትርኢት ደምቆ የተካሔደ ሲሆን በሽብርቅ ወረዳ 01፣11፣07 ከ1 እስከ 3 በመውጣት ከእለቱ የክብር እንግዶች የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ፕሬስ ሪሊዝ"የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል ቃል የፊታችን እሁድ ክፍለ ከተማ አቀፍ ማስ ስፖርት እንደሚካሄድ የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡ ኮል...
09/11/2024

ፕሬስ ሪሊዝ

"የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል ቃል የፊታችን እሁድ ክፍለ ከተማ አቀፍ ማስ ስፖርት እንደሚካሄድ የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም

ፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ህዳር 01/2017 ከጧቱ 12:00 ጀምሮ ቤተል እሳት አደጋ አከባቢ የፌደራል ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የወረዳ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጨምሮ ከ50 ሺህ በላይ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎችና የስፖርት ማህበረሰብ በተገኙበት ክፍለ ከተማ አቀፍ ማስ ስፖርት የአካል እንቅስቃሴ ይካሄዳል፡፡

ዝግጅቱን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የፅ/ቤቱ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል አበበ "የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን የማስ ስፖርት እና ልዪ ልዪ ትሪኢቶችና ሁነቶች እንደሚካሄዱ ገልፀው በእለቱም በክፍለ ከተማው የሚገኙ አባላት፣ የወጣትና ሴት አደረጃጀቶችን ጨምሮ መላው ነዋሪዎች በቦታው ተገኝተው የአካል እንቅስቃሴ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፏል ።

የወጣቶችን ተጠቃሚነትንና ተሳትፎ  ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ።  ኮልፌ ኮሙኒኬሽን መስከረም 28/2017 ዓ.ም    በክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት የ2016 በጀት አመት ማጠቃሊያ አ...
09/10/2024

የወጣቶችን ተጠቃሚነትንና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ።

ኮልፌ ኮሙኒኬሽን መስከረም 28/2017 ዓ.ም

በክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት የ2016 በጀት አመት ማጠቃሊያ አመታዊ ምዘና የእውቅና እና ሽልማት መርሀ-ግብር ተከናውኗል፡፡

በመድረኩም በባለፈው 2016 በጀት አመት የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎችና የ2017በጀት አመት 1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም የክፍለ ከተማው አመራሮች፣የክፍለ ከተማና የወረዳ የፅ/ቤቱ ባለሙያዎችና የስፖርት ማህበረሰብ ክፍሎች በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

የክፍለ ከተማው ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ቦጋለች ተድላ በመርሀ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር የወጣቶችን ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በስራ ዕድልና በሌሎች ዘርፎች ለማሳደግ በቅንጅት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ይህንንም አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በተለይም በክፍለ ከተማው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋፋት አለባቸው ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል አበበ በበኩላቸው ወጣቱ የሚህበረሰብ ክፍል በበርካታ ማህበራዊ በጎ ፍቃድ ተግባራት ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ሲሉ ተናግረው ባሉ የስራ ዕድል ፈጠራ ፀጋዎች ላይ ተጠቃሚ እንዲሆን እንሸራለን ሲሉ አስታውቀዋል።

አቶ ሳሙኤል አያይዘውም የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በአላት በሰላም ተከብረው እንዲያልፉ ሚናቸውን ለተወጡ ወጣቶችና ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመርሀ-ግብሩ ላይ በተጠናቀቀው በጀት አመት የላቀ ውጤት በማጥጣት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ለክፍለ ከተማና ለወረዳ ባለሙያዎችና ቡድኖች፣በማስ ስፖርት ተሳትፎ ጠንካራ ለሆኑ ወረዳዎችና ትምህርት ቤቶች፣ለወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት እንዲሁም ባለፈው በጀት አመት በተደረገ ምዘና 1ኛ ወረዳና 01፣2ኛ ወረዳ 04ና 3ኛ ወረዳ 08 ስፖርት ፅህፈት ቤት የዋንጫ ሽልማት የተሰጣቸው ሲሆን ለባለድርሻ አካላት፣ለክፍለ ከተማው ፌዴሬሽኖች፣ለአሰልጣኞችና ለወጣት አደረጃጀቶች የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቷል።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦
https://linktr.ee/kolfecommunication

የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት  የአሰልጣኝ ሰለሞን አንቼ መታሰቢያ የሀ-17 ታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር አካሄደ።መስከረም 19/2017 ዓ.ም ኮልፌ ቀራንዮ ወረ...
29/09/2024

የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት የአሰልጣኝ ሰለሞን አንቼ መታሰቢያ የሀ-17 ታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር አካሄደ።

መስከረም 19/2017 ዓ.ም
ኮልፌ ቀራንዮ ወረዳ 07 ኮሙኒኬሽን

የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በወረዳ 07 ሮም ሜዳ አራት ሀ-17 ታዳጊዎች የእግር ኳስ ቡድኖች የፍጻሜ ውድድር አካሄዱ።
የውድድር ግጥሚያ ያደረጉ ሀ-17 ታዳጊዎች እግር ኳስ ቡድኖች መካከል
አዲስ ተስፋ V ከሰለሞን አንቼ በፔናሊቲ አዲስ ተስፋ የእግር ኳስ ቡድን ሲያሸንፍ
ቤተል ፓሽን V ከቤተል ድሪመር 2 ለ 1 በሆነ የነጥብ ውጤት ማሸነፍ በመቻላቸው ቤተል ፓሽን ታዳጊ እግር ኳስ ቡድን የዋንጫ እና የሜዳልያ አሸናፊ መሆን ችሏል።

ሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ደማቅ ከተማ አቀፍ የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደመስከረም 19 ቀን 2017ዓ.ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደ...
29/09/2024

ሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ደማቅ ከተማ አቀፍ የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ

መስከረም 19 ቀን 2017ዓ.ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ኢሬቻ ማስ ስፖርት በሚል በመሪ ሀሳብ ከተማ አቀፍ የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በልደታ ክፍለ ከተማ አስተናጋጅነት ከሜክሲኮ ወደ ሳር ቤት በተሰራው የኮሪደር ልማት ላይ አካሄደ።

በአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና በእግር ጉዞው ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ኢሬቻ ማስ ስፓርት ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ኢሬቻን በባለቤትነት የሚያከብሩበት መሆኑን ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ ከመሆኑ ባሻገር በዓሉ ስፓርት ለጤንነት ከሚሰጠው ዋጋ ባልተናነስ ስለ ጤና አብዝቶ የሚጸለይበት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ኢሬቻ ወጣት፣ አዛውንት፣ ህፃን፣ አዋቂ ሳይል፣ በሀይማኖት ሳይለያይ፣ በፖለቲካ ሳይነጣጠል ሁሉም ማህበረሰብ በአንድነት የሚያከብረው የአብሮነት መገለጫ ነው ያሉት አቶ በላይ ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለም ቅርስ የሆነውን ኢሬችን ስናከብር ለእድገታችን፣ለሰላማችን እና ለአንድነታችን በጋራ መቆማችንን ለማሳየት ነው ብለዋል።

የህብረተሰቡን በተላይ የወጣቱን የዘወትር ጥያቄ የሆነውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ በከተማ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ያሳወቁት አቶ በላይ በከተማችን እየተሰሩ ባሉ የኮሪደር ልማቶች ላይ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተካተው መሰራታቸው የዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ሀላፊ አቶ ማቲዮስ ሰቦቃ በበኩላቸው ኢሬቻ የአብሮነት የአንድነት የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት መገለጫ በዓል መሆኑን ተናግረው በአዲስ አበባ በዓሉን በአማረ በደመቀ እና በሰለም ለማክብረ እየተሰሩ ላሉ ሁለንተናዊ ስራዎች ምስጋና አቅርበዋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በስተላለፋት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው የብዙሐን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ የህብረተሰቡን ጤና ከመጠበቅ ባሻገር የኢሬቻ በዓልን ይበልጥ ለአለም ለማስተዋወቅ የሚረዳ ነው ብለዋል።

የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተካሄደው የብዙሐን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ ፕሮግራም ላይ የአዲስ አበባ ከተማ እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ታዳጊዎች፣ ወጣቶች የስፖርት ቤተሰቦች እና ከአዲስ አበባ አጎራባች ከተማች የመጡ ወጣቶች ተሳትፈውበታል።

የ2017 የኢሬቻ በዓል ”ኢሬቻ ለባህላችን ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ በመጪው ቅዳሜ መስከረም 25 በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንደሚከበር በዝግጅቱ ተገልጽዋል

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን
👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014

👍👍👍ትዊተር

https://twitter.com/compose/tweet
👍👍👍ቲክቶክ

https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/

👍👍👍ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/
👍👍👍 ኢሜል

[email protected]

28/02/2024
መረጃየኮ/ቀ/ክ/ከተማ ሀ-13 እና ሀ-15 የጨዋታ መረጃ የክፍለ ከተማው እግር ኳስ ፌዴሬሽን የውድድር አዘጋጅና ስለስርአት ኮሚቴኮልፌ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚዩኒኬሽን
20/02/2024

መረጃ
የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ሀ-13 እና ሀ-15 የጨዋታ መረጃ
የክፍለ ከተማው እግር ኳስ ፌዴሬሽን የውድድር አዘጋጅና ስለስርአት ኮሚቴ
ኮልፌ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚዩኒኬሽን

Address

Kolfe Keranio Betel
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት kolfe keranio youth and sport office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category