20/02/2026
1⃣. ጋብቻው በየትኛውም ዓይነት የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓት ቢፈጸም በጋብቻ ላይ ፍቺ ለመወሰን ሥልጣን ያለው ፍርድ ቤት ብቻ ነው።
2⃣. አንድ ወንድ እና አንዲት ሴት ለረጅም ጊዜያት ተለያይተው ቢኖሩም፤ ሌላ ትዳር ቢመሰርቱም ጋብቻቸው በፍርድ ቤት እስካልፈረሰ ድረስ በሕግ አግባብ ባልና ሚስት እንደሆኑ ይቆጠራሉ።
3⃣. ፍቺ ለመጠየቅ ጋብቻ መኖሩን ማስረዳት ቀዳሚ ግዴታ ነው። በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል ጋብቻ አለ ለማለት የጋብቻ ምስክር ወረቀት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል። የጋብቻ ምስክር ወረቀት በሌለ ጊዜ የሰው ምስክሮችን በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል።
4⃣በሕግ አግባብ 2 ዓይነት ፍቺ አለ። 1ኛው.የስምምምነት ፍቺ ሲሆን 2ኛው. አንደኛው ተጋቢ የፍቺ አቤቱታ አቅርቦ ውሳኔ የሚያሰጥበት ፍቺ ነው። ሁለቱም የግዴታ ለፍርድ ቤት የሚቀርቡ መሆን አለባቸው።
5⃣ጋብቻ በሁለቱ ተጋቢዎች ፍላጎት እና ነፃ ፈቃድ ላይ ብቻ የተመሰረተ በመሆኑ አንደኛው ተጋቢ ፍቺውን አልፈልግም ቢል ወይም ፍርድ ቤት ባይቀርብም ፍርድ ቤቶች የፍቺ ውሳኔ ከመስጠት የሚከለክላቸው አይደለም።
©ቴዎድሮስ አብዲሳ
በማናቸውም የፌደራል ፍርድ ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ
☎️09 10 61 69 50
📍አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ🇪🇹