በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ

በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ መረጃዎች ተደራሽ ይሆኑበታል

19/02/2026

#የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በክልሉ ውስጥ ያሉ ዳኞች ጥቅማ ጥቅም ማስከበሪያ የሚሆን ብር 27,596,010.00 በሲዳማ ክልል ምክር ቤት ማፅደቁን አረጋግጠናል!
🙏🙏🙏

⚖️በዜጎች ላብ እንጂ በዜጎች እንባ ላይ የሚገነባ ልማት ዘላቂ አይሆንም! #የፌደራል የካሳ አዋጅ ቁ/1336 አንቀጽ 2(5) "የፌዴራል መንግስቱ የሚያከናውናቸው የመሰረተ ልማት እና የማህበራ...
16/02/2026

⚖️በዜጎች ላብ እንጂ በዜጎች እንባ ላይ የሚገነባ ልማት ዘላቂ አይሆንም!

#የፌደራል የካሳ አዋጅ ቁ/1336 አንቀጽ 2(5)

"የፌዴራል መንግስቱ የሚያከናውናቸው የመሰረተ ልማት እና የማህበራዊ አገልግሎት ማስፋፋያዎችን በተመለከተ በፍርድ ቤቶች የሚሰጡ ጊዜያዊ ትዕዛዞች ማለትም የልማት ስራው እንዲታገድ፣ የፌዴራል መንግስት ተቋምን የባንክ ሂሳብ የማገድ ወይም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ የፌዴራል መንግስት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችን ተገደው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የሚሰጡ ትዕዛዞች እና በቀጥታ ከፌዴራል መንግስት ተቋማት የባንክ ሂሳብ ክፍያ እንዲፈጸም የሚያስገድዱ ትእዛዞች በሚያከራክረው ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ብቻ ይሰጣል" በሚል ተደንግጓል.
* ይህ የዳኞችን ህገመንግስታዊ ስልጣን እና የዜጐችን ፍትህ የማግኘት መብት አያጣብብም? የፍ/ቤት ፕሬዝዳንቶች ለአስፈፃሚው አካል ይበልጥ ቅርብ ስለሆኑ፤ በዚህ ምክንያት ዜጐች ካሣ ሳይከፈላቸው እና ንብረታቸውን እንኳ አፍርሰው ለመውሠድ በቂ ጊዜ ሳይሰጣቸው ሜዳ ላይ እየወደቁ ነው።
#ይባስ ብሎ አዋጁ ልማቱን የሚያሰራው የፌደራል ተቋም ከሆነ የልማት ተፈናቃዮች ክስ ማቅረብ የሚችሉት ፌደራል ፍ/ቤቶች ላይ ብቻ ነው በሚል የደነገገ ሲሆን ይህ በአንድ በኩል የክልል ከፍተኛ እና ጠቅላይ ፍ/ቤቶች በህገ መንግስት የተሰጣቸውን የውክልና ስልጣን የሚቃረን በሌላም በኩል በአንቀፅ 37 ስር ጥበቃ የተደረገለትን የፍትህ ተደራሽነት የሚገድብ በመሆኑ አዋጁ ኢ.ህገመንግስታዊ ነው። አሰፈፃሚ አካሉ ያልተገደበ ስልጣን እንዲኖረው ፍርድ ቤቶች ደግሞ ስልጣናቸው እንዲሸረሸር እና ዜጐች ፍትህ እንዳያገኙ ያደረገ ነው። ሀገራዊ ልማቶቻችን የግለሰብ መብቶችን ባከበረ መልኩ ይሁኑ!
Judicial Independence

 #የያሬድ ወልደየሱስ ልጆችን እንታደግ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇ባህር ዳር ላይ ከተዋጣው አጠቃላይ 109.645 ብር ውስጥ ለተለያዩ ወጭዎች ተከናውነው ቀሪው 36.450 ብር ከወጭ ቀሪ ሁኗል።  ይህ...
24/01/2026

#የያሬድ ወልደየሱስ ልጆችን እንታደግ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ባህር ዳር ላይ ከተዋጣው አጠቃላይ 109.645 ብር ውስጥ ለተለያዩ ወጭዎች ተከናውነው ቀሪው 36.450 ብር ከወጭ ቀሪ ሁኗል። ይህንን 36,450 ብር ቀሪ ገንዘብ ጀምበሬ ወርቄ እና አደራው አዲሱ የጋራ አካውንት 1000743048858 በሚል ከፍተን ገንዘቡን ገቢ አድርገናል። አሁንም ለእነዚህ ሶስት ልጆቹ ለሚታገዙበት የተከፈተ አካውንት በመሆኑ በየትኛውም አለም ያላችሁ ትብብራችሁ አይለየን።
👉ምንጭ አደራው አዲሱ
#የወንድማችን ነፍስ በሰላም ያሳርፍልን!

 #በአማራ ክልል  ዛሬም የህግ ባለሙያዎች ሞት እንደቀጠለ ነው! የአሟሟቱን ሁኔታ ተጣርቶ ለወዳጅ ዘመዶቹ ሊነገራቸው ይገባል! #ያሬድ ወልደየስ ነፍስህ በሰላም ትረፍ
24/01/2026

#በአማራ ክልል ዛሬም የህግ ባለሙያዎች ሞት እንደቀጠለ ነው! የአሟሟቱን ሁኔታ ተጣርቶ ለወዳጅ ዘመዶቹ ሊነገራቸው ይገባል!
#ያሬድ ወልደየስ ነፍስህ በሰላም ትረፍ

06/01/2026

#የደሞዝ ጭማሪና የፍትህ ባለሙያው😔
በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ አመት ውስጥ ሁለት ጊዜ የደሞዝ ጭማሪ ተደርጓል። #ለዳኞችና ለዓቃቢያነ-ህጎች የተደረገ የደሞዝ ጭማሪ ግን የለም!
#ለዓቃቢያነ-ህጎች የተደረገው ጭማሪም በሀገር አቀፍ ወጥ በሆነ መንገድ እየተፈፀመ አይደለም!
👉በክልልና በዞን የደሞዝ ጭማሪ የደረሳችሁ ዓቃቢያነ-ህጎች ካላችሁ መረጃውን በውስጥ መስመር ወይም ኮሜንት ላይ አስቀምጡልን!

29/12/2025

👉እንደ-ሀገር የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎቾ ደሞዝና ጥቅማጥቅም ለተመሳሳይ ስራ ተመሳሳይ የሆነ ክፍያ የማግኘት መሰረታዊ መብት ሊሆን ይገባል!

👉የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዓቃቢያነ-ህጎች በተሻሻለው የደመወዝ ጭማሪ መሰረት  እንዲከፈላቸው ተፅፏል!
23/12/2025

👉የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዓቃቢያነ-ህጎች በተሻሻለው የደመወዝ ጭማሪ መሰረት እንዲከፈላቸው ተፅፏል!

19/12/2025

የዳኞች ደሞዝ (የሕግ ጉዳይ)
ሰሞኑን ዳኞች ከፌደራል ፍርድ ቤቶች በብዛት ሥራ ሲለቁ ይስተዋላል፡፡ ሌላው ቀርቶ ከመጨረሻው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ከአንድ ዓመት ወዲህ የተለያዩ ዳኞች ሥራ ለቀዋል። ከሥራ የሚልቁበት አንዱና ዋናው ምክንያት የደሞዝ ማነስ ነው። በሌላው የአፍሪካ ሀገር ግን ዳኝነትን የሚያክል የተከበረ ሥራ ለቆ መውጣት ያልተለመደ ነው።

እስኪ የሀገራችንን እና የሌሎች አፍሪካ ሀገሮችን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ደሞዝ እናነጻጽር። የ6 አፍሪካ ሀገሮች (ኬንያ፣ ግብፅ፣ ሞዛምቢክ፣ ታንዛንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ቻድ) የጠቅላይ ፍርድ ቤቶቻቸውን ደሞዝ እንመልከት።

1. ኬንያ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $ 2,170 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 65,000 – 80,000 ነው። ይህ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 33 እጥፍ ነው።
2. ግብፅ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $ 4,320 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 16,000 – 22,000 ነው። ይህ የዳኞች ደሞዝ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 4.5 እጥፍ ነው።
3. ሞዛምቢክ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $1,370 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 25,000 – 35,000 ነው። ይህ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 21.9 እጥፍ ነው።
4. የታንዛኒያ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $ 1,320 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 45,000 – 60,000 ነው። ይህ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 39.8 እጥፍ ነው።
5. ደቡብ አፍሪካ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $ 6,770 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 150,000 – 200,000 ነው። ይህ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 25.9 እጥፍ ነው።
6. ቻድ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በዶላር $ 690 ነው። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ አማካይ ደሞዝ በዶላር ሲመነዘር 15,000 – 20,000 ነው። ይህ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 25.4 እጥፍ ነው።

ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም እንዲሉ ከላይ የተጠቀሱት ሀገሮች የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ዓመታዊ የደሞዝ ገቢ ይለያያል፡፡ ከፍተኛ ተከፋዮች የደቡብ አፍሪካ ዳኞች ሲሆኑ በዓመት ከ200 ሺህ እስከ 300 ሺህ ዶላር ጋር የሚመጣጠን ደሞዝ ይከፈላቸዋል፡፡ ከስድስቱ ሀገራት መካከል ዝቅተኛው ተከፋዮች የቻድ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሆኑ በአማካይ በዓመት ከ15,000 እከ 20,000 ዶላር የሚገመት መጠን ያለው ገንዘብ ይከፈላቸዋል፡፡ ሆኖም በአማካይ የነፍስ ወከፍ ገቢያቸውን 20 እና 25 እጥፍ የሚከፍሉ መሆኑ ሀገራቱን ያመሳስላቸዋል፡፡ ከሀገራቱ ውስጥ ታንዛንያ 39.8፣ ኬንያ ደግሞ 33 እጥፍ በመክፈል ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ዓመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ 1,260 ዶላር ሲሆን ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞቿ እንደ ኬንያ 33 እጥፍ ቀርቶ 25 እጥፍ እንኳን ብትከፍል የአንድ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ደሞዝ (25 X $1,260 = $31,500 ወይም አሁን ባለው ምንዛሪ በብር 31,500 X 170 = 5,355,000 (አምስት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት ሺህ) ይሆን ነበር፡፡ ጽድቁ ቀርቶብኝ በወጉ በኮነነኝ እንዲሉ የአንድ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ዓመታዊ ገቢ 5 ሚሊዮን ቀርቶ 5 መቶ ሺህ እንኳን አይደርስም፡፡

ሀገርን ጥሩ ሀገር ከሚያሰኙት ዋና ዋና ነገሮች አንዱ የሕግ መከበርና የትክክለኛ ፍርድ መገኘት ነው፡፡ ትክክለኝ ፍርድ የሚኖረው ዕውቀቱና ልምዱ እንዲሁም ሥነ ምግባሩና ፍላጎቱ ያለው ዳኛ በቦታው ላይ ሲቀመጥ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ በሥራ ላይ ያሉትን ዳኞች ሥራቸውን ጥለው እንዳይወጡ ይዞ የሚያቆያቸው እንዲሁም ከውጪ ያሉትን ባለሞያዎች ስቦ የሚያመጣ ደሞዝ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ዳኞች ግር ብለው እንዳይወጡ እና ፍርድ ቤቱም የሀገር አለኝታ የሆነ ተቋም እንዲሆን ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ልምድ በመቅሰም እንደ እራሳችን ዐቅም ለዳኞች ደሞዝ ማሻሻል ይገባል፡፡
(ታምራት ኪዳነማርያም)

15/12/2025

⚖️ (Bond) እና (Suretyship) አንድ ናቸውን?
🏛️ አሁን ፀንቶ ባለው የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም አሰጣጥ፣ ቅድመ ሁኔታ ያልተቀመጠበት የዋስትና ሰነድ (Unconditional/Demand Guarantee) ከዋናው ውል (Underlying Contract) የተለየና ራሱን የቻለ ሰነድ (Independent Instrument) መሆኑ ከሞላ ጎደል ተቀባይነት አግኝቷል።

✅ ስለሆነም ሰነድ አውጪው ባንክ፣ ዋስትና ተቀባዩ ወገን ግዴታውን ስለመፈጸሙ ወይም አለመፈጸሙ የማጣራት ኃላፊነት የለበትም። ከዋስትና ሰነዱ ቃል ጋር የሚስማማ የክፍያ ጥያቄ (Complying Demand) ከዋስትና ተጠቃሚው ከቀረበለት፣ አውጪው ተቋም ክፍያ ለመፈጸም ይገደዳል። በዚህ ረገድ የነበሩ ብዥታዎች ጠርተዋል ማለት ይቻላል።

⚠️ ዋናው የህግ አተረጓጎም ችግር ያለው "በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሰረተ የዋስትና ሰነድ" (Conditional Guarantee Bond) ላይ ነው።

በዚህ ረገድ የሰበር ችሎት፣ እንዲህ ዓይነቱ ሰነድ በፍትሐ ብሔር ሕጉ "የዋስትና ውል" ድንጋጌዎች የሚገዛ እንደሆነ በተደጋጋሚ አቋሙን አንጸባርቋል። ይህ አቋም ግን መሰረታዊ የፅንሰ-ሀሳብ ጥያቄዎችን ያስነሳል።

❓ አንድ የዋስትና ሰነድ "በሁኔታ ላይ የተመሰረተ" ነው ሲባል ምን ማለት ነው?
በተለመደው የፍትሐ ብሔር ሕግ "የዋስትና ውል"፣ ዋሱ ዋናው ባለዕዳ ግዴታውን እንዲፈጽም በሚቀርብ ክስ ላይ ተከራካሪ ሆኖ፣ ለዋስትናው መነሻ በሆነው በዋናው ውል አፈጻጸም ላይ የመከራከር መብት አለው። ለብቻው በተከሰሰ ጊዜም ቢሆን በዋናው ውል በሚደረገው ክርክር ተሳታፊ ነው።

👉 ለምሳሌ “ተቋራጩ እንደ ውሉ ስለፈጸመ ተጠያቂነት የለብኝም” በሚል በዋናው የግንባታ ውል አፈጻጸም ላይ ማስረጃ እያቀረበ መከራከር ይችላል። ተከራክሮ ካሸነፈ፣ ከተጠያቂነት ነጻ ይሆናል።

ነገር ግን፣ ይህ ዓይነት ክርክር በሁኔታ ላይ በተመሰረተ የዋስትና ሰነድ (Bond) ላይ ተፈጻሚ ሊሆን ይችላልን?

🏗️ የመልካም ስራ አፈጻጸም ዋስትናን (Performance Bond) በምሳሌነት እንውሰድ። እርግጥ ነው የዋስትና ሰጪው የመክፈል ግዴታ የሚኖረው ዋናው ባለዕዳ እንደ ውሉ አለመፈጸሙ ሲረጋገጥ ነው። ነገር ግን፣ ያ ማለት ዋስትና ሰጪው (ባንኩ ወይም ኢንሹራንሱ) በዋስትና ሰነዱ ተጠቃሚ (ለምሳሌ፡ አሰሪው) እና በባለዕዳው (ለምሳሌ፡ ስራ ተቋራጩ) መካከል በሚደረግ የውል አፈጻጻም የፍርድ ቤት ክርክር ላይ ገብቶ ሊከራከርና ሊፈረድበት ይገባል ማለት አይደለም።
በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የዋስትና ሰነድ (Conditional Bond) ላይ በዋነኛነት መረጋገጥ ያለበት፣ በሰነዱ ላይ ክፍያ ለመፈጸም ስምምነት የተደረገበት "ሁኔታ" (Condition) መሟላቱ ብቻ ነው።
🔹 ምሳሌ፡ በዋስትና ሰነዱ ላይ “የባለዕዳው (ተቋራጩ) ተጠያቂነት በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ውሳኔ ከተረጋገጠ ክፍያ ይፈጸማል” ተብሎ ከተቀመጠ፣ ልክ ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሲቀርብለት ዋስትና ሰጪው ክፍያ ሊፈጽም ይገደዳል፤ ምክንያቱም የሰነዱ ሁኔታ ተሟልቷልና።

🔹 ሁኔታው “የገላጋይ መሀንዲስ (Adjudicator) ውሳኔ” ከሆነ ደግሞ፣ ውሳኔው ሲቀርብለት የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል።

ስለሆነም የዋስትና ሰነድ (Guarantee Bond) ሲባል፣ ቅድመ ሁኔታ ኖረውም አልኖረውም፣ ዋስትና ሰጪው በሰነዱ ቃል ላይ ብቻ ተመስርቶ የክፍያ ግዴታ የሚገባበት Security Instrument እንጂ፣ እንደ መደበኛ ዋስ ወደ ዋናው ክርክር የሚገባበት ውል አይደለም።

🔄 የሰበር ችሎት እርስ በርስ ያልታረቀ አቋም

የሰበር ችሎት፣ የዋስትና ሰነድን (Bond) ከዋስትና ውል ጋር አቻ አድርጎ የሚሰጠው ትርጉም፣ በተግባር የማይታረቁ ጭብጦች ሲነሱ መዋዥቅ ይስተዋልበታል። ለምሳሌ በሰበር መዝገብ ቁጥር 40186 እና 36935 ላይ የተሰጡትን ውሳኔዎች እንመልከት።

📜 በነዚህ መዝገቦች ላይ ለቀረበው ክርክር፣ ሰነዱ በሁኔታ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ በፍትሐ ብሔር ሕጉ የዋስትና ድንጋጌዎች የሚገዛ "የዋስትና ውል" ነው የሚል አቋም ተያዘ። ሆኖም፣ አንድ የዋስትና ውል በሕጉ መሠረት በሁለት ምስክሮች ሊረጋገጥ ስለሚገባውና ይህ ስላልተሟላ ሰነዱ ህጋዊ ውጤት የለውም ለሚለው ፈታኝ ክርክር ምላሽ ሲሰጥ፣ ችሎቱ ቀድሞ የያዘውን አቋም በከፊል ሻር አደረገው። ችሎቱ "ምንም እንኳን የዋስትና ውል ቢሆንም፣ በባንክ አሠራር የሚሰጥ በመሆኑ በሁለት ምስክሮች ሊረጋገጥ አይገባውም" የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ።
🤔 ይሄ ደግሞ “ነው ግን አይደለም” ዓይነት ያልጠራ አቋም ነው። አንድ ሰነድ "የዋስትና ውል" ነው ከተባለ በኋላ፣ ለውሉ ህልውና አስገዳጅ የሆነውን የምስክሮች ቅድመ ሁኔታ ማስቀረት የሚቻልበት የህግ አግባብ የለም። ወይ ሰነዱ የዋስትና ውል ነው (ምስክር ያስፈልገዋል)፣ ወይም የዋስትና ውል አይደለም (ምስክር አያስፈልገውም)።

💡 መፍትሔው፡ Sui Generis (Of its own kind)

ከእንዲህ ዓይነቱ የህግ አተረጓጎም አጣብቂኝ መውጣት የሚቻለው፣ የዋስትና ሰነድ (Bond) ቅድመ ሁኔታ ኖረውም አልኖረውም፣ መደበኛ የዋስትና ውል እንዳልሆነ ጥርት ያለ አቋም በመያዝ ነው።
የችግሩ ምንጭ፣ በፍርድ ቤት በሚካሄድ ክርክር ላይ የሚነሱ አዳዲስ የንግድና የባንክ ጉዳዮችን በነባር የህግ ክፍሎች (በማጠጋጋት) እንዲሸፈኑ የማድረግ አባዜ ነው። ግልጽ መሆን ያለበት ጉዳይ፣ ለተወሰኑ ዘመናዊ የንግድ ሰነዶች በፍትሐ ብሔር ሕጉ ላይ ቀጥተኛ ሽፋን ላይኖር ይችላል። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሲከሰት፣ ፍርድ ቤቱ ክርክር የተነሳበትን የህግ ክፍል Sui Generis ("Of its own kind" / "In a class by itself") ብሎ መመደብ አለበት።

📌 በመሆኑም፣ የዋስትና ሰነድ (Guarantee Bond) የዋስትና ውል (Suretyship Contract) አይደለም፤ ይልቅስ ራሱን ችሎ የቆመ Security Instrument ነው
(Abraham Yohannes)

 , የፌደራል ጠበቆች ማህበር አመራሮች ምርጫ ውጤት ይፋ ሆኗል! #ፕሬዚዳንት ጠበቃ ተስፋዬ ደረሰ #ምክትል ፕሬዘዳንት ጠበቃ መሰረት አያሌው #ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች 1. ጠበቃ ዳዊት 2. ጠ...
13/12/2025

, የፌደራል ጠበቆች ማህበር አመራሮች ምርጫ ውጤት ይፋ ሆኗል!
#ፕሬዚዳንት ጠበቃ ተስፋዬ ደረሰ
#ምክትል ፕሬዘዳንት ጠበቃ መሰረት አያሌው
#ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች
1. ጠበቃ ዳዊት
2. ጠበቃ ነብዩ
3. ጠበቃ ጀሚላ
4. ጠበቃ ቤዛ
5. ጠበቃ ሰብስበው
6. ጠበቃ ቀለመወርቅ
7. ጠበቃ ሄኖክ
#መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ!

ማስተካከያ ተደርጓል! #ትናንት በለጠፍነው ጥቆማ መሰረት ፍትህ ሚኒስቴር በተገለፀው አግባብ የመመልመያ መስፈርቱን ማስተካከያ ተደርጎበታል!
07/12/2025

ማስተካከያ ተደርጓል!
#ትናንት በለጠፍነው ጥቆማ መሰረት ፍትህ ሚኒስቴር በተገለፀው አግባብ የመመልመያ መስፈርቱን ማስተካከያ ተደርጎበታል!

06/12/2025

#ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል
​ #ሐረሪ ሕዝብ ክልል
​ #ሶማሌ ክልል
​ #ሲዳማ ክልል
​ #ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት
​ #ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል
​ #ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት
​ #አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
​ #ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
ውስጥ የምንሰራ ዳኞችና ዓቃቢያነ ህጎች ጥቅማ ጥቅም ባለመስተካከሉ ምክንያት ስራችን በቁዘማ ሆኗል😌😌😌

Address

196
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category