በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ

በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ መረጃዎች ተደራሽ ይሆኑበታል

‹ሀላፊነት የማይሰማው ፍትሕ ሚኒስቴር እና   ባለቤት አልባው ዓቃቢያነ-ሕግ› #የሰመራውን ጉባዔ ለዓቃቢያነ ህጎች የደመወዝ ጥያቄን መልስ ይሰጣል ተብሎ በጉጉት ቢጠበቅም  ለባለሙያዎች እንደተ...
29/08/2026

‹ሀላፊነት የማይሰማው ፍትሕ ሚኒስቴር እና
ባለቤት አልባው ዓቃቢያነ-ሕግ›
#የሰመራውን ጉባዔ ለዓቃቢያነ ህጎች የደመወዝ ጥያቄን መልስ ይሰጣል ተብሎ በጉጉት ቢጠበቅም ለባለሙያዎች እንደተቋም መልስ ሊሰጥ የማይችል ሆኖ ተጠናቋል። ሌሎች ተቋማት ከፌደራል እስከ ክልል የደምወዝና ጥቅማጥቅም መብት ቢያስከብሩም ፍትሕ ሚኒስቴር ግን ለክልል ፍትሕ ቢሮዎች እናት ተቋም መሆን የማይችል እንዲሁም የፍትሕ ስርዓት ማዕዘንነቱን አጥቷል። ዓቃቢያነ ሕጎችም ባለቤት አልባ የማይሰሙና የማይደመጡ ሆነዋል።
👉ዓ/ህጎች ስለቀጣይ በማህበራችሁና በሌሎች አማራጭ መንገዶች መብታችሁን ለማስከበር እራሳችሁን አዘጋጁ!

ለኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴርለአብክመ ርዕሰ መስተዳድርለአብክመ ፍትህ ቢሮጉዳዩ:- የዓቃቢያነ ሕግ ሃገራዊ የደመወዝ ጭማሪን የመለከታል 🌼​ባለፈው 2017 ዓ.ም በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጅ...
23/08/2026

ለኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር
ለአብክመ ርዕሰ መስተዳድር
ለአብክመ ፍትህ ቢሮ
ጉዳዩ:- የዓቃቢያነ ሕግ ሃገራዊ የደመወዝ ጭማሪን የመለከታል

🌼​ባለፈው 2017 ዓ.ም በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጅግጅጋ ከተማ በተካሄደው 7ኛው የፍትህ ሚኒስቴር እና የክልል ፍትህ ቢሮዎች የጋራ ጉባኤ ላይ "ጠንካራ የፍትህ አካላት ቅንጅት ለተረጋገጠ የህዝብ አመኔታ" በሚል መሪ ቃል ሰፊ የምክክር መድረክ መካሄዱ ይታወቃል።
🌼በዚሁ መድረክ ላይ የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ እንደ ሀገር የተከናወኑት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሪፎርሞች በፍትህ ዘርፉ ላይም መሰረታዊ ለውጦችን ማምጣታቸውን ገልጸው ነበር።

🌼​በዚህ ሳምንት በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰመራ ከተማ በሚካሄደው 8ኛው የጋራ ጉባኤ ላይም የፍትህ ስርዓቱን በላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ይበልጥ ይጠበቃል።

🌼 ነገር ግን የፍትህ አካላት ቅንጅትና የህዝብ አመኔታ እውን ሊሆን የሚችለው፣ የፍትህ ማስከበር ስራውን በግንባር ቀደምትነት የሚያስፈጽሙት ዓቃቢያነ ሕግ በቂ የኢኮኖሚና የሙያ ዋስትና ሲኖራቸው ብቻ ነው። በተጨማሪም እንደ ሃገር የተጨመራቸውን የደመወዝ ጭማሪ እንደ ሌሎች አቻ ሙያ እና ተቋማት ተፈፃሚነቱ የውሃ ሽታ ሁኖ ሳይቀር ነው።

🌼​ጠንካራና ገለልተኛ የፍትህ ተቋም ለመገንባት፣ የዓቃቢያነ ሕግ መብትና ጥቅማጥቅም የሚከበረው በቅሬታና አቤቱታ ሳይሆን ቀድሞ በግንባር ቀደምትነት ሊሟላ ይገባል።

🌼 በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል የሚገኙ ዓቃቢያነ ሕግ ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሪው ከሌሎች ዘግይቶ እስካሁን ባለመፈጸሙ ምክንያት ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ሞራላዊ ተጽዕኖ የደረሰባቸው ይመስላል።

🌼ጉዳዩን በበላይነት የማስፈጸም ስልጣንና ኃላፊነት ያለው የፍትህ ሚኒስቴር በዚህ ጉባኤ ላይ ለችግሩ ዘላቂና ግልጽ የመፍትሔ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ በትልቅ ተስፋ እንደሚጠበቅ ይታመናል።

🙏​በመሆኑም እኔ እንደ አንድ ዜጋ የምጠቁመው:-

✍️ ​የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር በየደረጃው ያሉ ዓቃቢያነ ሕግ የሚያነሱትን የደመወዝ ጭማሪና የጥቅማጥቅም ጥያቄ የፍትህ ሪፎርሙ ዋና አካል በማድረግ፣ በዚህ 8ኛው የጋራ ጉባኤ ላይ የመጨረሻና አዎንታዊ መፍትሔ እንዲሰጥበት፤

✍️​የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር በክልሉ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥና የፍትህ ተደራሽነት እንዳይቆዝም፣ የዓቃቢያነ ሕግን የኑሮ ሁኔታና የመብት ጥያቄ ቀድመው ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመመካከር በዚህ ጉባየ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥበት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ፤

✍️​የአብክመ ፍትህ ቢሮ ዓቃቢያነ ሕግ በርካታ የአገልግሎትና የኢኮኖሚ ፈተናዎች እያሉባቸው ያስመዘገቡትን ከፍተኛ የ2018 በጀት ዓመት ስኬትና የላቀ አፈጻጸም በጉባኤው ላይ በግልጽ በማሳየት፣ የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ የላቀ የሞራልና የሙያ አደራቸውን እንዲወጡ፤

✍️​የአማራ ዓቃቢያነ ሕግ የሙያ ማህበር የጉባኤውን መካሄድ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ የዓቃቢያነ ሕግን ድምፅና ጥያቄ የሚያንጸባርቅ ይፋዊ የማሳሰቢያ ደብዳቤ ለጉባኤውና ለሚመለከታቸው አካላት እንዲያደርስ በማድረግ ቀድሞ እንዲታሰብበት ማድረግ፣

✍️እንደ እኔ ግምት ​የፍትህ ተቋማት ጥንካሬ የሚለካው በስራቸው ባሉ ባለሙያዎች መረጋጋትና ብቃት በመሆኑ፣ ይህ 8ኛው የጋራ ጉባኤ የዓቃቢያነ ሕግን አንገብጋቢ ጥያቄዎች በመመለስ የተጣለበትን ሀገራዊ አደራ እንደሚወጣ እተማመናለሁ።
አመሠግናለሁ
Via Aderaw Addisu

Nuremberg⚖️🔨⚖️የጎንደር ዩኒቨርስቲ የህግ ት/ት ቤት ተማሪዎች አለምአቀፍ ምስለ ችሎት ውድድር ኢትዮጵያን በመወከል በመወዳደር ላይ ይገኛሉ።ውድድሩ በጀርመን ኑረምበርግ ይካሄዳል። ይህች...
24/07/2026

Nuremberg⚖️🔨⚖️
የጎንደር ዩኒቨርስቲ የህግ ት/ት ቤት ተማሪዎች አለምአቀፍ ምስለ ችሎት ውድድር ኢትዮጵያን በመወከል በመወዳደር ላይ ይገኛሉ።
ውድድሩ በጀርመን ኑረምበርግ ይካሄዳል። ይህች ከተማ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የናዚ መሪዎች የተዳኙበት ታሪካዊ ስፍራ ናት። የመጨረሻ ዙር የምስለ ችሎት ውድድሮችም ብዙ ጊዜ በታሪካዊው Nuremberg Palace of Justice ውስጥ ይካሄዳሉ።
የኑረምበርግ (Nuremberg) Moot Court Competition ከሌሎች የMoot Court ውድድሮች የሚለየው ምንድን ነው?
የኑረምበርግ Moot Court Competition በዓለም ላይ ካሉ ታዋቂ የሕግ የፍርድ ቤት ማስመሰያ (Moot Court) ውድድሮች አንዱ ሲሆን፣ በተለይም ዓለም አቀፍ የወንጀል ሕግ (International Criminal Law) ላይ ያተኮረ መሆኑ ከሌሎች ውድድሮች የሚለየው ዋና ባህሪው ነው።
1. በዓለም አቀፍ የወንጀል ሕግ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው
አብዛኞቹ Moot Court ውድድሮች በሕገ መንግሥት ሕግ፣ በዓለም አቀፍ ሕግ ወይም በንግድ ጉዳዮች ላይ ያተኩራሉ። ነገር ግን Nuremberg Moot Court የሚመለከተው፦
• የዘር ማጥፋት (Genocide)
• በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች (Crimes Against Humanity)
• የጦር ወንጀሎች (War Crimes)
• የጥቃት ወንጀል (Crime of Aggression) እንደዚህ ያሉ ከባድ ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን ነው።
2. ሦስት ወገኖችን ይወክላሉ
ብዙ Moot Court ውድድሮች ሁለት ወገኖች (Applicant እና Respondent) ብቻ አላቸው።
ነገር ግን Nuremberg Moot Court ተሳታፊዎች ሦስት የተለያዩ ሚናዎችን ይወስዳሉ፦
• ዐቃቤ ሕግ (Prosecutor)
• ተከሳሽ መከላከያ (Defense Counsel)
• የተጎጂዎች ሕጋዊ ተወካይ (Legal Representatives of Victims)
ይህም በእውነተኛው የICC ሂደት ውስጥ የሚኖረውን ሥርዓት ያንጸባርቃል።
Again Good luck to University of Gondar!!!

ለአሸናፊዎቻችን 1ኛ. የፖርቹጋል ከስፔን(ለ3 አሸናፊዎች የ1000 ሽ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ) 2ኛ. የፈረንሳይ ከስፔን(ለ3 አሸናፊዎች የ500 መቶ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ) እና የዛሬ...
15/07/2026

ለአሸናፊዎቻችን
1ኛ. የፖርቹጋል ከስፔን(ለ3 አሸናፊዎች የ1000 ሽ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ) 2ኛ. የፈረንሳይ ከስፔን(ለ3 አሸናፊዎች የ500 መቶ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ) እና የዛሬዉን አርጀንቲና ከእንግሊዝ(ለ3 አሸናፊዎች የ700 መቶ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ) እንዲሁም ቀጣይ የፍፃሜዉን(የሽልማቱ መጠን ለወደፊቱ የሚገለፅ) በትክክል ለገመታችሁና ለምትገምቱ አሸናፊዎቻችን የካርድ ስጦታዉን በተመሳሳይ ቀን የፍፃሜዉ እለት የምንሰጥ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡
ዛሬም ይገምቱ ይሸለሙ!
ለ3 አሸናፊዎች የ700 መቶ ብር ካርድ ለእያንዳንዳቸዉ እንሞላለን፡፡
ከአድሚን ኮሚቴዉ!

ይገምቱ ይሸለሙ⚽️ለሶስት አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸዉ የ500(አምስት መቶ) ብር ካርድ እንሞላለን፡፡
14/07/2026

ይገምቱ ይሸለሙ⚽️
ለሶስት አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸዉ የ500(አምስት መቶ) ብር ካርድ እንሞላለን፡፡

ከህግ ጉዳይ እንዉጣ!ይገምቱ ይሸለሙ! ለሶስት አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸዉ የ 1000(አንድ ሽ) ብር ካርድ እንሞላለን፡፡
06/07/2026

ከህግ ጉዳይ እንዉጣ!
ይገምቱ ይሸለሙ! ለሶስት አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸዉ የ 1000(አንድ ሽ) ብር ካርድ እንሞላለን፡፡

ለተመረጣችሁ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ፡፡በአብክመ ለዞን ዐቃቢ-ሕግነት የደረጃ እድገት የተጠቃለለ ውጤት!
06/07/2026

ለተመረጣችሁ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ፡፡
በአብክመ ለዞን ዐቃቢ-ሕግነት የደረጃ እድገት የተጠቃለለ ውጤት!

"ስለ ዐቃቤያነ ህጎች ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ ጉዳይ" በጋራ መስራት ወደ ውጤትና ስኬት ይመራል! ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ከተከበሩት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተማርነው ትልቅ ትም...
05/07/2026

"ስለ ዐቃቤያነ ህጎች ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ ጉዳይ"
በጋራ መስራት ወደ ውጤትና ስኬት ይመራል!
ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ከተከበሩት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተማርነው ትልቅ ትምህርት አለ። በጋራ በመተባበርና በቁርጠኝነት መስራት ማንኛውንም ችግር መፍታት እንደሚቻል በተግባር አሳይተዋል።
እንደሚታወቀው፣ መንግስት ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁሉም የመንግስት ሰራተኞች ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህ መሰረት፣ የፍትህ አካላት ባለሙያዎችን የሚያካትት መሆኑ በመመሪያ ቁጥር 1110/2018 በግልጽ ተደንግጓል።
ነገር ግን፣ ዳኞችና ዐቃቤያነ ህጎች የደመወዝ ጭማሬው ሳይተገበር ቆይቷል። ባለሙያዎቹም በተደጋጋሚ ጥያቄያቸውን ለሚመለከተው አካል አቅርበዋል።
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ያሉ ዳኞችና የክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ዳኞች ያነሱትን ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ ይደረግልን የመብት ጥያቄ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ትልቅ ሃላፊነት በመውሰድና ከክልሎች ጋር በተባበር መንገድ በመስራት የዳኞች የደመወዝ ጭማሬ ጥያቄ መፍታት ችለዋል። በጋራ የተደረገው ስራ ውጤት እንዳመጣ በግልጽ አሳይቷል።
ሆኖም፣ የዐቃቤያነ ህጎች ተመሳሳይ ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ በህግ ቢፈቀድላቸውም፣ እስካሁን ድረስ ተግባራዊ አልሆነም። ይህም ባለሙያዎቹን በተደጋጋሚ ቅሬታ እንዲያነሱ አድርጓቸዋል።
ይህን ጉዳይ መፍታት የሚገባው የፍትህ ሚኒስትር ነው። እንደ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሃላፊነት በመውሰድ፣ ከክልል ፍትህ ቢሮዎች ጋር በቅርብ በመተባበር የዐቃቤያነ ህጎችን የመብት ጥያቄ በፍጥነት መፍታት ይገባዋል።
ይህ ጉዳይ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይፈታ ሲቀር፣ በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ የሰራተኞች ተነሳሽነት እየቀነሰ፣ የስራ ጫናውም እየጨመረ ነው። በቀጣይ በጀት ዓመት ይህ በፍትህ ስርዓቱ ችግር እና ትልቅ ጫና ሊፈጥር ይችላል።
ስለዚህ፣ የፍትህ ሚኒስትር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አፋጣኝ መፍትሄ እንዲያመጡ እንጠይቃለን። እንደ ዳኞች ጉዳይ በጋራ በመስራት፣ የዐቃቤያነ ህጎችንም ተመሳሳይ የደመወዝ ጭማሬ በፍጥነት ማስተግባር ይገባል።
በጋራ እንስራ! በጋራ ውጤት እናምጣ(Ethio Law Daily)

የአብክመ ፍትህ ቢሮ ሀላፊዎች የሙያተኞችን መብትና ጥቅማ ጥቅም ለማስከበር እየሄዳችሁበት ያለዉንና ስታደርጉት ለነበረዉ ጥረት እጅግ እናመሰግናለን፡፡ እስካሁን የነበረዉ ችግርም በክልሉ ፍትህ ...
22/06/2026

የአብክመ ፍትህ ቢሮ ሀላፊዎች የሙያተኞችን መብትና ጥቅማ ጥቅም ለማስከበር እየሄዳችሁበት ያለዉንና ስታደርጉት ለነበረዉ ጥረት እጅግ እናመሰግናለን፡፡ እስካሁን የነበረዉ ችግርም በክልሉ ፍትህ ቢሮ በኩል እንዳልሆነ ሁሉም ሙያተኛ ይረዳችኋል ብለን እናምናለን፡፡ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ቢሮዉ በወቅቱ የሙያተኞቹን ጭማሪ ደሞዝ መክፈል አልቻለም፡፡ “የክልሉ ዐቃቤያነ ህጎች ሀገራዊ የደመወዝ ጭማሬ እንደማይቀር በቅርቡ በጀቱ እንደሚለቀቅ እና ከነ ውዝፉ እንደሚከፈል የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሀላፊ የተከበሩ አቶ ብርሃኑ ጎሽም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል”
እናመሰግናለን!

22/06/2026

ስለ ዐቃቤያነ ህግ የደመወዝ ጭማሬ (ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
=======///=======
በአማራ ክልል የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገልንም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል።
" በአንድ የፍትህ ሥርአት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው " - የክልሉ ፍትሕ ቢሮ
በአማራ ክልል ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ፣ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ እንዳልተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
ዓቃቢያነ ህጉ፥ የ2018 በጀት ዓመት የደመወዝ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 1110/2018 እነሱንም የሚያካትት ቢሆንም፣ የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ እስኪቀሩት ድረስ ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳልተደረገላቸው ገልጸዋል።
የፌደራል ዓቃቢያነ ህግ የማሻሻያው ተጠቃሚ በሆኑበት ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሙያዎች ተነጥለው መቅረታቸው አግባብ እንዳልሆነና አሳሳቢ የህልውና ጥያቄ በመሆኑ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽምን በስልክ አነጋግሯል።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ በዝርዝር ምን አሉ ?
የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሀገራዊ የደሞዝ ጭማሪው ከመታወጁ በፊት በክልሉ የዓቃቢያነ ህግ የደረጃ ማሻሻያ ተደርጎ እንደነበር አንስተዋል።
" ከፌደራል የደሞዝ ጭማሪ መጥቷል ሲባል የክልሉ መንግስት ያደረገውን የደረጃ እድገት ማስተካከያን መነሻ ያደረገ ሪፖርት ለፌደራል መንግስት ልከናህ። ይሁን እንጂ ሀገራዊው የደሞዝ ስኬል ማሻሻያ ግን ለክልሉ ዓቃቢያነ ህግ እስካሁን አልተላከም።
ለምንድነው እስካሁን ያልመጣው? የሚለው የኛም ጥያቄ ነው።
የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴሯን ሰብሳቢ ያደረገ ኮሚቴ ተቋቁሟል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጡም ጥረት እየተደረገ ነው።
የዳኞች የደሞዝ ማሻሻያ በቅርቡ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ተግባራዊ ተደርጓል። በአንድ የፍትህ ስርዓት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው።
የእኛም አቋም ሀገራዊ ጭማሪው ለዓቃቤ ህግም መምጣት አለበት የሚል ነው " ሲሉ ነግረውናል።
የዐቃቢያነ ህግ ጥያቄ የደሞዝ ጭማሪው እስከ ውዝፍ ክፍያው ይከፈለን የሚል መሆኑን ለኃላፊው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሀገራዊ የደሞዝ ማሸሻያው መመሪያ መስከረም ላይ እንደወጣ አስታውሰው እንደ አማራ ክልል ከመስከረም ጀምሮ ውዝፉም አብሮ ይሰጠን የሚል ጥያቄ ለፌደራል መቅረቡን አሳውቀዋል።
በመጨረሻም የፌደራል መንግስት ውሳኔውን አሳልፎ በጀቱን ሲለቅ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ የዚህን በጀት ዓመት ውዝፍ ክፍያ በቀጥታ ለባለሙያዎቹ ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ጠቁመዋል።
የጊዜ ጉዳይ እንጂ መፍትሄ ማግኘቱ የማይቀር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማኔጅመንትም በትናንትናው እለት በጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጉንና በቀጣይም ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር የሚደረገውን ንግግር ኮሚቴው አጥብቆ እንደሚከታተለው ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም
See less

Address

196
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በኢትዮጵያ የዳኞችና የዓቃቢያነ-ህጎች ድምፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category