Free-Legal/ነፃ-ሕግ

Free-Legal/ነፃ-ሕግ Stay Legally Aware make a better decisions, and avoid unnecessary mistakes.
(1)

10/05/2026

ሰ/መ/ቁ 245575 & 184757
👇👇👇
ባንኮች በዋስትና በያዟቸው ሀብቶች ላይ የቀደምትነት መብት ሊኖራቸዉ የሚችለዉ ዋስትና ከመቀበላቸዉ በፊት ከባለሃብቱ (ከታክስ ከፋዩ) የሚፈለግ የታክስ እዳ መኖር አለመኖሩን ከግብር ሰብሳቢዉ ባለስልጣን አጣርተው ባለስልጣኑም የታክስ ዕዳ የሌለበት መሆኑን በሰነድ የተደገፋ ማረጋገጫ የሰጠ እንደሆነ ብቻ መሆኑን እና ይህን ሂደት ሳይከተል በዋስትና የያዘ እንደሆነ በታክስ ሕግ መሰረት ታክስ ከፋዩ መክፈል የሚገባዉ የመክፈያ ጊዜዉ የደረሰ ታክስ በሙሉ ተከፍሎ እስከሚያልቅ ድረስ ባለስልጣኑ በታክስ ከፋዩ ሀብት ላይ የቀደምትነት መብት ይኖረዋል (አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 33 ትን መሰረት በማድረግ የተሰጠ ትርጉም)

09/05/2026
08/05/2026

Watch, follow, and discover more trending content.

08/05/2026

ስለ ኑዛዜ ከውርስ ሕግና ከሰበር ውሳኔዎች አንፃር!
***
የኢትዮጵያ የውርስ ሕግ ኑዛዜ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሰጠው ትርጉም ባይኖርም አንድ ኑዛዜ ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ምን ምን እንደሆኑ በዝርዝር የሚያስቀምጡ የሕግ ድንጋጌዎችን ከፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 857 እስከ 908 ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡

በዚህ ጽሁፍ ኑዛዜ በምን አግባብ ቢደረግ በሕግ ዘንድ ውጤት ይኖረዋል፤በውርስ ሕጋችን ላይ የተቀመጡት የኑዛዜ አደራረግ ስርዓቶች አስገዳጅነታቸው እስከምን ድርስ እንደሆነና ኑዛዜ በፍርድ ቤት ቢጸድቅ ሊያስገኝ የሚችለው ውጤትና ባለመጽደቁ የሚያመጣው ተጽእኖ ምን እንደሆነ ከውርስ ሕግ እና አስገጋጅ ከሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ውሳኔዎች አንጻር በአጭሩ ዳሰሳ ለማድርግ ተሞክሯል፡፡

ለኑዛዜ ዋጋ መኖር አስፈላጊ የሆኑ የስረ ነገር ሁኔታዎች

በፍትሐ ብሔር ህግ ከአንቀጽ 857 እስከ 879 የተደነገጉት ድንጋጌዎች ለኑዛዜ ዋጋ መኖር አስፈላጊ የሆኑ የሥረ ነገር ሁኔታዎች (essential condition of wills) አካትተው ተደንግገዋል፡፡ ከእነዚህ አጠቃላይ ደንጋጌዎች ለመረዳት እንደሚቻለው ለኑዛዜ ዋጋ መኖር አስፈላጊ የሆኑ የሥረ ነገር ሁኔታዎች በሁለት ከፍሎ ማየትና መተንተን ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው የኑዛዜ ሁለንተናዊ ወይም ተፈጥሯዊ አስፈላጊ ነገር( inherent or intrinsic elements of will) የሚባለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በኑዛዜው ይዘት ላይ የሚያተኩርና ለሕግና ሞራል ተቃራኒ መሆን ወይም አለመሆኑን የሚቆጣጠሩ ናቸው፡፡

የኑዛዜ ሁለንተናዊ ወይም ተፈጥሯዊ ነገር የሚባለው ተናዛዡ ኑዛዜውን በሚፈጽምብት ወቅት የነበረው የአእምሮ ሁኔታ ወይም ኑዛዜ የማድረግ ሀሳብ የነበረው መሆኑ( animus testandi ) የምንለው ነው፡፡ የኑዛዜ ክርክር የሚነሳው ኑዛዜ አድርጊው ከሞተ በኋላ ስለሆነ ኑዛዜ አድርጊው በሙሉ ፍላጎቱና ሀሳቡ ኑዛዜውን ያደረገ ስለመሆኑ እንዴት እርግጠኛ መሆን ይቻላል የሚለው ነጥብ ነው፡፡ ይህን ለመረዳት የሚከተሉት ነጥቦች ከግምት ውስጥ መግባት ይኖርባቸዋል፡፡

ሀ) ተናዛዡ ራሱ በሙሉ ሀሳቡ ኑዛዜ የፈጸመ መሆኑ

በፍ/ብ/ሕ/ቁ 857 በተገለጸው መሰረት ሟች ኑዛዜ የማድረግ ሀሰብና ፍላጎት ኖሮት እንደዚሁም የኑዛዜው ይዘት በመረዳት ኑዛዜ ማድረግ ያለበት እሱ ራሱ ብቻ መሆን እንዳለበት በግልጽ ደንግጓል፡፡ ህጉ የሟች ሀሳብ በሌሎች ሰዎች ማለትም በወኪሎች በኩል በኑዛዜ ላይ መግለጽ እንደማይገባው በመከልከል ኑዛዜውን የሟች የግል ስራና የራሱ የሀሰብ መግለጫ መሆን እንዳለበት በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ አንድ ሰው በሌላ ሰው በስሙ ኑዛዜ እንዲያደረግ ፤እንዲለውጥ ወይም እንዲሽር ስልጣን ሊሰጠው እንደማይችል አንድ ሰው ሌላ ሶስተኛ ወገን ወራሹን እንዴት እንደሚወስንና ውርሱ ለማን መተላለፍ እንዳለበት እንዲፈጽም ሊያደርግ እንደማይችል የውርስ ህግ ደነግጋል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር መ/ቁጥር 134836 በቅጽ 22 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጓሜ ላይ እንደተመላከተው “ ኑዛዜ ጥብቅ የሆነ የግል ጠባይ ያለው እና በሟች ብቻ የሚፈጸም በመሆኑ ብዙ ሰዎች አንድ በሆነ ጽሁፋ በጋራ ማናዘዝ የማይቻልና ኑዛዜው ፈራሽ የሚያደርገው ነው፡፡ በመሆኑም በተደረገው ኑዛዜ በሟች የግል ንብረት ላይ ሌላ ሰው ጭምር በአንድ የኑዛዜ ሰነድ ላይ ተናዘው ከተገኙ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 858፤857 እና 880 ተከታዩ ድንጋጌዎች አንጻር ፍርድ ቤቶች ኑዛዜውን ፈራሽ ነው በማለት የሚሰጡት ውሳኔ የሚነቀፍበት ሕጋዊ መክንያት የለም” ሲል የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡

07/05/2026

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በይ/መ/ቁ/804/16 ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ.23021 (በቅጽ 5) ላይ ባልና ሚስት ጋብቻቸውን ካፈረሱ በኋላ አብረው መኖራቸው ጋብቻው እንደቀጠለ ይቆጠራል የሚለው ሐሳብ በሕግ አውጪው የማይታወቅ አዲስ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓትን የሚደነግግ እና በሕገመንግሥቱ ለሕግ አውጪ በተሰጠው ሥልጣን ውስጥ ጣልቃ መግባት ነው በማለት ወስኗል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣን እና ተግባርን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1261/2013 አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 80 መሠረት ምክር ቤቱ የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ እና አስገዳጅ ነው፡፡

05/05/2026

አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተከሰሰበት የዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ እንዲሰናበት ካልተወሰነበት በስተቀር ከስራ በታገደበት ወቅት ሳይከፈለው የቀረው ደመወዝ የሚከፈለው ስለመሆኑ ። ቅፅ 24 መዝገብ ቁጥር 161880

በአዲሱ የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2024 (2025) መሰረት፡

የመንግስት ሰራተኛ በዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ ሲታገድ፣ በእግዱ ጊዜ ደመወዙ ሊቆም ይችላል።

በመጨረሻ ከስራ እንዲሰናበት ውሳኔ ካልተወሰነበት (ወይም ውሳኔው ካልተረጋገጠ)፣ በእግዱ ወቅት ያልተከፈለው ሙሉ ደመወዝ ያለ ወለድ መከፈል አለበት።

 #ዉጭ  #ሀገር  #የሚሰሩ  #ኢትዮጵያዊያን  #ጉዳት  #በሚደርስባቸው  #ጊዜ ሰዎችን ወደ  ውጪ ሀገር  #የላከ  #ሰው ( #ድርጅት) በተላኩት ሰዎች ላይ ለሚደርስ  #ጉዳት  #ካሣ የመክ...
05/05/2026

#ዉጭ #ሀገር #የሚሰሩ #ኢትዮጵያዊያን #ጉዳት #በሚደርስባቸው #ጊዜ ሰዎችን ወደ ውጪ ሀገር #የላከ #ሰው ( #ድርጅት) በተላኩት ሰዎች ላይ ለሚደርስ #ጉዳት #ካሣ የመክፈል #ግዴታ #ያለበት #ስለመሆኑ
🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩🍩

➤ዉጭ ሀገር የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ጉዳት በሚደርስባቸው ጊዜ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አዋጅ ቁ.(632/2001) በአዋጅ ቁጥር 923/2008 የተሻረ (በአዋጅ ቁጥር 1246/2013 የተሻሻለ) ጥበቃ ይሰጣል።

➤ #ከአሰሪና #ሠራተኛ #አገናኝ #አገልግሎት ጋር በተገናኘ ሰዎችን ወደ ውጪ ሀገር የላከ ሰው (ድርጅት) በተላኩት ሰዎች ላይ ለሚደርስ ጉዳት ካሣ የመክፈል ግዴታ የሚኖርበት ስለመሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 74111 ሀምሌ 04 ቀን 2004 ዓ/ም በዋለው ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል።

05/05/2026

የቼክ ክፍያን ማገድ
**********
የንግድ ሕጉ ድንጋጌ (አንቀጽ 857) ፦ አንድ የቼክ አውጪ ቼኩ ለባንክ ቀርቦ ከመከፈሉ በፊት ለባንኩ "ክፍያ አትፈጽም" የሚል ትዕዛዝ መስጠት እንደሚችል ይገልጻል። ሆኖም ግን፣ ሕጉ ትዕዛዙ የሚሰጥባቸውን "በቂ ምክንያቶች" በዝርዝር ባለማስቀመጡ፣ በተግባር ላይ ግልጽነት የጎደለው አሠራር እንዲሰፍንና የቼክ ተአማኒነት ላይ ጥያቄ እንዲነሳ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (SBB/64/2016)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በንግድ ሕጉ ላይ የታየውን ይህንን ክፍተት ለመሙላት እና የቼክን የክፍያ ዋስትና (ተአማኒነት) ለመጠበቅ ግልጽ መመሪያ አውጥቷል። በዚህ መመሪያ አንቀጽ 6.2.2 መሠረት፣ ባንኮች "ክፍያ ይቁም" (Stop Payment) የሚል ትዕዛዝን ተቀብለው ሊያስተናግዱ የሚችሉት በሚከተሉት ሁለት ምክንያቶች ብቻ እንደሆነ ተደንግጓል፦

* ቼኩ የጠፋ ከሆነ (Loss of Check)፦ ቼኩ በአካል ከባለቤቱ እጅ ጠፍቶ ለሌላ ወገን አደጋ ሊያጋልጥ የሚችል መሆኑ ሲረጋገጥ።
* ቼኩ የተሰረቀ ከሆነ (Theft of Check)፦ ቼኩ በሌባ ወይም ባልተፈቀደ አካል ተወስዶ ወዳልተገባ ክፍያ ሊያመራ የሚችል ከሆነ።
ስለሆነም የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በግልጽ እንደሚደነግገው በአካውንት ውስጥ በቂ ስንቅ (ገንዘብ) ሳይኖር ቼክ ጽፎ በመስጠት በኋላ ላይ ከሕግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ሲባል "ክፍያ ይቁም" የሚል ትዕዛዝ መስጠት በፍጹም የማይቻል ሲሆን፣ ባንኮችም ከመጥፋትና ከመሰረቅ ውጭ የሚቀርቡ ማናቸውንም የክፍያ ማገጃ ትዕዛዞች የመቀበል ግዴታ የለባቸውም። ያለበቂ ምክንያት እንዲህ ዓይነቱን ትዕዛዝ መስጠት በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 693 መሠረት "በቼክ ማጭበርበር ወንጀል" የሚያስጠይቅ ሲሆን፣ ይህም ተጠያቂነት የሚከሰተው ባንኩ በትዕዛዙ መሠረት ክፍያ ሲከለክል፣ ተጎጂው የክስ ማመልከቻ ሲያቀርብ እና ቼክ አውጪው ሆን ብሎ የባለገንዘቡን መብት ለመጋፋት ወይም ክፍያውን ለማሰናከል አስቦ ትዕዛዙን ማስተላለፉ በሕግ ፊት ሲረጋገጥ ነው።

ቼክ የገንዘብ ተኪ ሆኖ የሚያገለግል የክፍያ ሰነድ በመሆኑ፣ አንዴ ጽፈው ለሰው ካስረከቡ በኋላ መልሶ ለማገድ የሚቻለው ቼኩ ከእጅዎ ወጥቶ በሌባ ወይም በድንገት ከጠፋብዎት ብቻ ነው፡፡ ከግለሰቡ ጋር ያለዎት ሌላ አለመግባባት (ለምሳሌ የውል አለመከበር) "ክፍያ ይቁም" ለማለት በቂ ምክንያት አይሆንም፡፡ እንደነዚህ ያሉ አለመግባባቶችን በሌላ የሕግ መንገድ (በፍትሐ ብሔር ክስ) መፍታት እንጂ ቼክን በማገድ ወንጀል ውስጥ እንዳይገቡ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡

የተዘጋ መዝገብ ለማንቀሳቀስ አመልካች በራሱ ጉድለት ወይም ቸልተኝነት ቀጠሮውን ሳይከታተል ቀርቶ ካልሆነ በቀር ፍትህ የማግኘትና የመከራከር መብት ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል ...
03/05/2026

የተዘጋ መዝገብ ለማንቀሳቀስ አመልካች በራሱ ጉድለት ወይም ቸልተኝነት ቀጠሮውን ሳይከታተል ቀርቶ ካልሆነ በቀር ፍትህ የማግኘትና የመከራከር መብት ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል እንደ በቂ ምክንያት በመዉሰድ ለተጠሪ በቂ ወጪና ኪሳራ አስከፍሎ መዝገቡን ማንቀሳቀስ የሚገባ ስለመሆኑ።
በፌ/ብ/ሥ/ሥ/ሔ/ቁ.74 (2) ዴንጋጌ መሰረት ‛በቂ ሆኖ የሚገመት እክል“ ምን እንደሆነ የተመከከተ ባይሆንም በቀጠሮ ለመቅረት ምን ምክንያት እንደሆነ አጠቃላይ ሁኔታዉን መመርመር የሚያስፈልግ ሆኖ፣ አመልካች በራሱ ጉድለት ወይም ቸልተኛነት ቀጠሮዉን ሳይከታተል ቀርቶ ካልሆነ በቀር፣ ፍትህ የማግኘትና የመከራከር መብት ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል እንደ በቂ ምክንያት በመዉሰድ ለተጠሪ ተገቢ ኪሳራና ወጪ በማስከፈል፣ የተዘጋዉ መዝገብ ተከፌቶ ክርክሩ እንዲሰማ መደረጉ አግባብ ስለመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ 182136 በቅፅ 24 ላይ የተሰጠ አስገዳጅ ውሳኔ።
የፌ/ብ/ሥ/ሥ/ሔ/ቁ.32 (2) እና 74 (1)

03/05/2026

ከጋብቻ በፊት የነበረ የግል ቤት በትዳር ዉስጥ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ቢደረግለትም የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም፡፡ (የፌደሬሽን ምክር ቤት መስከረም 28-2017 ዓ.ም)

ቀደም ሲል ከጋብቻ በፊት የግል የነበረ ቤት በትዳር ዉስጥ መሰረታዊ በሚባል ደረጃ እድሳት ከተደረገለት ወይም ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ ከተደረገለት ቤቱ የባልና ሚስት የጋራ ይሆናል በማለት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትበሰ/መ/ቁ 215860 ዉሳኔ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ይህ የሰበር ሰሚ ችሎቱ ዉሳኔ ሕገ-መንግስቱን ይቃረናል በሚል የሕገ-መንግስት ትርጉም ለፌደሬሽን ምክር ቤት ቀርቦት የነበር ሲሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤቱ መስከረም 28-2017 ዓ.ም በሰጠዉ ዉሳኔ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉን ዉሳኔ በመሻር ተፈጻሚነት የለዉም ብሏል፡፡ፌደሬሽን ምክር ቤት ዉሳኔ ከጋብቻ በፊት የግል የነበር ቤት በጋብቻ ዉስጥ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ መደረጉ ቤቱን የጋራ ንብረት አያደርገዉም፡፡ ቤቱን ለማሻሻል እና ለማስፋፋት የወጣ ወጪ ተጣርቶ ወጪዉ በድርሻ እንዲወስዱ ከሚደረግ በስተቀር ቤቱ የጋራ አይሆንም፡፡
ከጋብቻ በፊት የነበረ የግል ቤት በትዳር ዉስጥ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ቢደረግለትም የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም፡፡ነገር ግን ቤቱን ለማሻሻል እና ለማስፋፋት የወጣ ወጪ ተጣርቶ ወጪዉ በድርሻ እንዲወስዱ ይሆናል ::

03/05/2026

ኢትዮጵያ በቅርቡ ያወጣችው የህንጻ አዋጅ ቁጥር 1356/2016 (Ethiopian Building Proclamation No. 1356/2024) ቀደም ሲል የነበረውን አዋጅ ቁጥር 624/2001 በመተካት በዘርፉ ላይ መሰረታዊ ለውጦችን ይዞ መጥቷል።
ከአዋጁ የወጡ ዋና ዋና 5 ነጥቦች እነሆ፦

1. የተጠያቂነት ወሰን መስፋት (Extended Liability)
በአዲሱ አዋጅ መሰረት ማንኛውም በህንጻ ግንባታ ሂደት ላይ የሚሳተፍ አካል (ባለቤት፣ ዲዛይነር፣ ተቋራጭ እና አማካሪ) በግንባታ ወቅት ለሚከሰት ማንኛውም የጥራት መጓደል ወይም አደጋ በወንጀል እና በፍትሐብሔር ይጠየቃል። በተለይ ዲዛይነሮች እና ተቋራጮች ለህንጻው ደህንነት ያላቸው የኃላፊነት ጊዜ ተለይቶ ተቀምጧል።

2. የህንጻዎች ምደባ እና የቁጥጥር ስርአት (Building Categorization)
ህንጻዎች እንደ አገልግሎታቸው፣ እንደ ቁመታቸው እና እንደሚያስተናግዱት ሰው ብዛት በሦስት መደቦች (Category A, B, and C) ተከፍለዋል።
ለእያንዳንዱ መደብ የሚሰጠው የፍቃድ አሰጣጥ እና የቁጥጥር ጥብቅነት ይለያያል።
ከፍተኛ የህዝብ ብዛት የሚያስተናግዱ (እንደ ሞል፣ ሆስፒታል) ለደህንነት ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣቸዋል።

3. የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት (Sustainability & Environment)
አዲሱ አዋጅ ግንባታዎች አካባቢን እንዳይበክሉ እና የሀይል አጠቃቀማቸው ቀልጣፋ እንዲሆን (Energy Efficiency) ትኩረት ይሰጣል።
የዝናብ ውሃ አሰባሰብ (Rainwater Harvesting) ስርአት።
ቆሻሻ አወጋገድ እና የተፈጥሮ ብርሃን አጠቃቀምን በዲዛይን ደረጃ እንዲካተቱ ያዝዛል።

4. አካል ጉዳተኞችን እና አረጋውያንን ያገናዘበ ግንባታ (Accessibility)
ማንኛውም ህዝባዊ አገልግሎት የሚሰጥ ህንጻ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን እና ህጻናት ያለምንም እንቅፋት እንዲንቀሳቀሱበት የሚያስችል ስርአት (Ramps, Lifts, Signage) ሊኖረው እንደሚገባ በግልጽ አስቀምጧል። ይህንን ያላሟላ ህንጻ የይለፍ ፍቃድ (Occupancy Permit) አይሰጠውም።

5. የህንጻ አስተዳደር እና የይለፍ ፍቃድ (Occupancy Permit & Maintenance)
ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት የሚሰጠው "የመገልገያ ፍቃድ" ጥብቅ ሆኗል።
ህንጻው ከተመረቀ በኋላ በየጊዜው እድሳት (Maintenance) እንዲደረግለት እና የደህንነት ፍተሻ እንዲከናወን ህግ አስገድዷል።
ህንጻው ለታለመለት አላማ ብቻ መዋሉን የመቆጣጠር ስልጣን ለማዘጋጃ ቤቶች ሰጥቷል።

ይህ አዋጅ በዋናነት የግንባታን ጥራት ማረጋገጥ፣ የአደጋ ተጋላጭነትን መቀነስ እና በዘርፉ ላይ የሚታየውን የሙስና እና የብልሹ አሰራር ክፍተቶችን ለመድፈን ያለመ ነው።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251992731165

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Free-Legal/ነፃ-ሕግ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Free-Legal/ነፃ-ሕግ:

Share

Category