የጥብቅናና ህግ ምክር አገልግሎት -TheLawyers' Office

የጥብቅናና ህግ ምክር አገልግሎት -TheLawyers' Office በማንኛውም የፌደራል ፍርድ ቤቶች የጥብቅና አ�

28/03/2024
27/12/2023
21/05/2023
18/05/2023
14/05/2023

የሥራ ውል ማቋረጥና ማራዘም /የመንግስት ሠራተኛ/
⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️
በባለፈው ጽሑፍ አንድ መንግስት ሠራተኛ እንዴት ከሥራ ልታገድ ይችላል በሚል ፖስት ካደረኩ በኋለ ብዙ ሰዎች ከሥራችሁ ጋር ብዙ ጥያቄ ያቀረባችሁ ሲሆን ለእያንዳንዱ መልስ መስጠት ወይም በስልክ ማስረዳት ጊዜ ስለሚወስድ በቂም ላይሆን ስለሚችል በሚከተለው መልኩ እንድትረዱና አስፈላጊውን መረዳት እንድታገኙ ቀርቦላችኋል፡- የፌደራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064 የህግ ድንጋጌዎች /የተወሰኑ ማብራሪያ ብቻ ተደርጎ/
አንቀጽ 83፡- በራስ ፈቃድ የሥራ ውል ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በማንኛውም ጊዜ የአንድ ወር ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሥራውን በፈቃዱ ሊለቅ ይችላል፤ ሆኖም መስሪያ ቤቱ ሠራተኛውን በቀላሉ ሊተካው የሚችል ከሆነ የአንድ ወሩን ጊዜ ሳይጠብቅ ስንብቱን ሊፈቅድለት ይችላል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተውን የአንድ ወር የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ አገልግሎቱን ያቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ ግዴታውን ባለመወጣቱ ለሚደርሰው ጉዳት እንደተገቢነቱ በፍትሐ ብሔር እና በወንጀል ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
3. የመንግሥት ሠራተኛው ለሥራው እጅግ አስፈላጊና በቀላሉ ለመተካት የማይቻል ሆኖ ሲገኝ ወደ ፊት ከሚቀጠርበት መስሪያ ቤት ጋር በመስማማት የመልቀቂያውን ጥያቄ ሠራተኛው ካመለከተበት ቀን ጀምሮ ከሦስት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ሊራዘም ይችላል፡፡
አንቀጽ 84፡- በሕመም ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 43(2) ወይም (4) በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ለመመለስ ካልቻለ በሕመም ምክንያት አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. የዚህ አዋጅ አንቀጽ 59(3) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ በሥራው ምክንያት ጉዳት የደረሰበት የመንግሥት ሠራተኛ ለዘለቄታው መሥራት አለመቻሉ በሕክምና ማስረጃ ሲረጋገጥ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
3. በዚህ አዋጅ አንቀጽ 26 ንዑስ አንቀጽ (3)(ለ) መሠረት በሚፈጸመው ዝውውር ተስማምቶ ለመስራት ፈቃደኛ ያልሆነ የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 85፡- በችሎታ ማነስ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
1. የሙከራው ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግስት ሠራተኛ በሥራ አፈጻጸም ውጤቱ የችሎታ ማነስ ከታየበት ተገቢው የአቅም ማጎልበት ሥልጠናዎች ተሰጥተውት ካልተሻሻለ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. የመንግሥት ሠራተኛ ያለውን ዕውቀትና ችሎታ እየተጠቀመ በተመደበበት ሥራ ላይ የሥራ አፈጻጸም ውጤቱ በተከታታይ ለሶስት ጊዜ ከሚጠበቀው ውጤት በታች ከሆነ በችሎታ ማነስ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ ቢኖርም ለተከታታይ አምስት ዓመታት ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤት ሲያገኝ የነበረ የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤቱ በተከታታይ ለአራት ጊዜ ከሚጠበቀው ውጤት በታች ካልሆነ በስተቀር ከሥራ አይሰናበትም፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) እና (3) መሠረት የመንግሥት ሠራተኛውን ከሥራ ማሰናበት የሚቻለው እንደአስፈላጊነቱ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 31 ላይ የተቀመጠውን የሥራ አፈጻጸም ምዘና ዓላማ በመከተል ይሆናል፡፡
አንቀጽ 86፡- ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
1. የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ምክንያቱን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለመሥሪያ ቤቱ ማሳወቅ አለበት፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ሪፖርት የተደረገለት የመንግሥት መሥሪያ ቤት የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሠራተኛው ከሥራ ገበታው ላይ የተለየበት ምክንያት ከአቅም በላይ መሆኑን ካረጋገጠ የመንግሥት ሠራተኛው ይዞት የነበረውን የሥራ መደብ ለስድስት ወር ክፍት አድርጎ መጠበቅ አለበት፡፡ ሆኖም የመንግሥት ሠራተኛው በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራው ካልተመለሰ ከሥራ ማሰናበት ይቻላል፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ ቢኖርም የመንግስት ሰራተኛው ከስድስት ወር በላይ በሥራ ላይ ያልተገኘው በእስር ምክንያት ከሆነና ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት በነፃ ስለመለቀቁ ማስረጃ ካቀረበ የመንግስት መስሪያ ቤቱ ባለው ክፍት የሥራ መደብ ቀደም ሲል ይከፈለው የነበረውን ደመወዝ እያገኘ ወደ ሥራ እንዲመለስ ማድረግ አለበት፡፡
4. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለተከታታይ አሥር ቀናት ከመደበኛ የሥራ ቦታው ላይ ከተለየ በየአስር ቀናት ልዩነት በተከታታይ ለሁለት ጊዜ በማስታወቂያ ተጠርቶ ለመንግስት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካላደረገ ከሥራ ይሰናበታል፡፡
5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (4) መሠረት በማስታወቂያ ጥሪ የተደረገለት የመንግሥት ሠራተኛ ከሥራ ከተለየበት ቀን ጀምሮ አንድ ወር ከመሙላቱ በፊት ወደ ሥራው ለመመለስ ለመንግስት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ሠራተኛው ከሥራ የቀረበትን ምክንያት በመመርመር የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ወደ ሥራው እንዲመለስ ይደረጋል፡፡
6. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (4) ቢኖርም ከስራ የተሰናበተ ሰራተኛ ከሥራ ከቀረበት ቀን ጀምሮ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ከሥራ የቀረበት ምክንያት ከአቅም በላይ ለመሆኑ ለመሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገና በቂ ማስረጃ ካቀረበ በመሥሪያ ቤቱ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሲፈቅድ ወደ ሥራ ሊመለስ ይችላል፡፡
7. የሙከራ ጊዜውን ያላጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለአንድ ወር ጊዜ በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ያለተጨማሪ ሥነ-ሥርዓት አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 87፡- የሠራተኛ ቅነሳ
1. ማንኛውንም የመንግሥት ሠራተኛ፣
ሀ) የሥራ መደቡ ሲሰረዝ፣
ለ) መሥሪያ ቤቱ ሲዘጋ፣
ሐ) ትርፍ የሰው ኃይል ሲኖር፣
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 30(1) መሠረት ለመደልደል ካልተቻለ ወይም የመንግሥት ሠራተኛው ዝቅ ባለ የሥራ ደረጃ ላይ ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ ከሥራ ይሰናበታል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1)(ሐ) መሠረት ቅነሳ የሚደረገው የመንግሥት ሠራተኛው በመሥሪያ ቤት ውስጥ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ካሉ ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ጋር ሲወዳደር በሥራ ውጤቱና ባለው ችሎታ ዝቅተኛ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡
አንቀጽ 88፡- በዲስፕሊን ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 69 ንዑስ አንቀጽ (1)(ሠ) መሠረት በዲስፕሊን ቅጣት የተወሰነበትና በአስተዳደራዊ ይግባኝ ውሳኔው ያልተሰረዘለት የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 89፡- በዕድሜ ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 73 መሠረት አገልግሎቱ ካልተራዘመ በስተቀር በሕግ ከተወሰነው የመጦሪያ ዕድሜ ከደረሰበት የመጨረሻ ወር የመጨረሻ ቀን ጀምሮ አገልግሎቱ እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት በጡረታ ለሚሰናበት የመንግሥት ሠራተኛ ጡረታ ከመውጣቱ ከሶስት ወር በፊት በጽሑፍ እንዲያውቀው ይደረጋል፡፡
አንቀጽ 90፡- በሞት ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ከሞተበት ቀን ጀምሮ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. አገልግሎቱ በሞት ምክንያት የተቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ የሞተበት ወር ሙሉ ደመወዙ እንዲሁም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 41(1) መሠረት ላልተወሰደ የዓመት ዕረፍት ፈቃድ የሚፈጸም ክፍያ ለትዳር ጓደኛው፣ የትዳር ጓደኛ ከሌለው ለሕጋዊ ወራሾች ይከፈላል፡፡
3. አግባብ ባለው የጡረታ ህግ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በሞት ምክንያት አገልግሎቱ ሲቋረጥ ለሚሠራበት መሥሪያ ቤት በጽሑፍ ላሳወቃቸው የትዳር ጓደኛው ወይም በስሩ ይተዳደሩ ለነበሩ ቤተሰቦች የሦስት ወር ደመወዝ በአንድ ጊዜ ይከፈላል፤ ሆኖም የትዳር ጓደኛውን ወይም በሥሩ የሚተዳደሩ ቤተሰቦቹን ሳያስመዘግብ የሞተ እንደሆነ ሥልጣን ካለው አካል ወይም ፍርድ ቤት በሚሰጥ ማስረጃ መሠረት ክፍያው ይፈጸማል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት የሚሰጠው ክፍያ ከግብርና ከጡረታ መዋጮ ነጻ ይሆናል፤ እንዲሁም በዕዳ ሊከበር ወይም በማቻቻያነት ሊያዝ አይችልም፡፡
አንቀጽ 91፡- የአገልግሎት ምስክር ወረቀት አሠጣጥ/Certificate of Service/ ክሊራንስ/
1. ለማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የሚሰጥ የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት ሠራተኛው ሲያከናውን የነበረውን የሥራ ዓይነት፣ የአገልግሎት ዘመኑና ሲከፈለው የነበረውን ደመወዝ የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
2. የሥልጠና ውል ግዴታ ወይም በመንግሥት መሥሪያ ቤቱ የሚፈለግበት ማናቸውም ዕዳ ያለበት የመንግስት ሠራተኛ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎቱን ሲያቋርጥ የውል ግዴታውን ስለመፈጸሙ ወይም ከዕዳ ነጻ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ከማግኘቱ በፊት የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት አይሰጠውም፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) በሥራ ላይ እያለ የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት ለሚጠይቅ የመንግስት ሠራተኛ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
አንቀጽ 92፡-አገልግሎት ሲቋረጥ የሚፈጸም ክፍያ
1. የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 87 መሠረት በቅነሳ ምክንያት ከሥራ ከተሰናበተና የሥራ ውሉ በተቋረጠበት ዕለት የጡረታ አበል የማይከፈለው ከሆነ፣
1.1. ለመጀመሪያ አንድ ዓመት የሦስት ወር ደመወዝ፣
1.2. በተጨማሪ ለአገለገለበት ለእያንዳንዱ ዓመት የወር ደመወዙ አንድ ሦስተኛ እየታከለ፣ ይከፈለዋል፤ ሆኖም የሚሰጠው ክፍያ ከሠራተኛው የአሥራ ሁለት ወር ደመወዙ መብለጥ የለበትም፡፡
2. የሙከራ ጊዜውን ለጨረሰና ከአንድ ዓመት በታች ላገለገለ የመንግስት ሠራተኛ የሚፈጸመው ክፍያ ከአገልግሎቱ ጋር ተመጣጣኝ ይሆናል፡፡
አንቀጽ 93፡- አገልግሎትን ማራዘም
1. የመንግሥት ሠራተኛ የመጦሪያ ዕድሜው ከደረሰ በኋላ በአንድ ጊዜ እስከ አምስት ዓመት በጠቅላላው ከአሥር ዓመት ለማይበልጥ ጊዜ አገልግሎቱን ማራዘም ይቻላል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የአንድን የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎት ማራዘም የሚቻለው፣
2.1. የሠራተኛው ትምህርት፣ ልዩ ዕውቀትና ችሎታ ለመሥሪያ ቤቱ ሥራ ጠቃሚ ሆኖ ሲገኝ፣
2.2. በደረጃ ዕድገት፣ በዝውውር ወይም በቅጥር ተተኪ ሠራተኛ ለማግኘት አለመቻሉ ሲረጋገጥ፣
2.3. ሠራተኛው ለሥራው ብቁ መሆኑ በሕክምና ማስረጃ ሲረጋገጥ፣
2.4. ሠራተኛው አገልግሎቱን ለመቀጠል ሲስማማ፣ እና
2.5. የአገልግሎቱ መራዘም ጥያቄው የመጦሪያ ዕድሜው ከመድረሱ ከሦስት ወር በፊት ለሚኒስቴሩ ቀርቦ ሲፈቀድ፣ ነው፡፡
የመንግስት ሰራተኛ አዋጅን በቴሌግራም ያግኙ
👇👇👇👇👇👇
telegram
https://t.me/ethiolawtips
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️

by tsgaye demke
Source legal consulting limited

19/03/2023

በወንጀል ክርክር ፍርድ ቤት ቀርበው የእምነት ክሕደት ቃል ስለመስጠት /Plea of the accused)
========================
ክሱን እየሰማ ያለ ፍርድ ቤት ተከሳሹ የእምነት ክህደት ቃሉን እንዲሰጥ ማዘዝ የሚችለው የመጀመሪያ መቃወሚያ ያልቀረበ እንደሆነ ወይም መቃወሚያው ቀርቦ የሕግ መሰረት የለውም ተብሎ ውድቅ ከተደረገ ወይም ሕጉ በሚያዘው መሰረት መዝገቡ ለጊዜው ካልተዘጋ ብቻ ነው። የእምነት ክሕደት ቃል (plea) ስንል ተከሳሹ ጉዳዩን በያዘው (ክሱን እየሰማ ባለው) ፍርድ ቤት ፊት ቀርቦ ስለቀረበበት ክስ ፍሬ ነገር መፈፀሙን ኣለመፈፀሙን እና ጥፋተኛ መሆኑን ኣለመሆኑን ለመግለፅ የሚናገረው ቃል ማለት ነው።

#ስለ እምነት ቃል (Plea of guilty)

በአጠቃላይ ስለ እምነት ቃል ሲወሳ ሁለት ነገሮች ወደ ኣእምሮኣችን ይመጣሉ፡፡ እነሱም ዓ/ሕግ እና ተከሳሽ በሚያደርጉት ስምምነት (Plea bargaining) በተከሳሹ የሚሰጥ እምነት ቃል ኣንዱ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ተከሳሹ ጉዳዩን በያዘ አሟጓች /የስር/ ፍርድ ቤት ፊት ቀርቦ ክሱን ከተነበበለት በyላ የሚሰጠው የእምነት ቃል (Plea of guilty) ነው።

የእምነት ቃል ለመስጠት መስማማትን /plea bargaing/ በዋነኝነት በኮመን ሎው የሕግ ስርዓት ተከታይ ኣገሮች የሚታወቅ ሆኖ ሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች (ዓ/ሕግና ተከሳሽ) የሚስማሙት፤ ተከሳሽ የእምነት ቃል እንዲሰጥና በአንፃሩ ደግሞ ዓቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ የሚያቀርበው ክስ እንዲቀንስ ወይም ተመስርቶ የነበረ ክስ ቀንሶ እንዲያነሳ ወይም ቅጣት እንዲቀልለት ለፍርድ ቤት ሓሳብ ማቅረብ ነው (ኣንዳንዱ ጊዜ እስከ 30% ቅጣት ይቀነሳል)። በእነዚህ አገሮች አብዛኛዎቹ የወንጀል ጉዳዮች ውሳኔ የሚያገኙት በእምነት ቃል መሰረት ነው። ለዚህ ኣስራር መምጣት ምክንያት የሆኑት ደግሞ በየጊዜው እየጨመረ የመጣው የፍ/ቤት ጉዳዮች ለማቃለልና የክርክር ስርዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ በመምጣቱ ነው ይባላል።

ክሱን ለሚሰማ ፍርድ ቤት የሚሰጥ የእምነት ቃል ተቀባይነት በሚመለከት የተለያዩ የሕግ ስርዓቶች የተለያየ ኣም ኣላቸው$ የኮመን ሎው የሕግ ስርዓት የሚከተሉ አገሮች ያየን እንደሆነ በተከሳሾች የሚሰጥ የእምነት ቃል በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት ሊያገኝ ይገባል ይላሉ። ስለሆነም ኣብዛኛው የወንጀል ጉዳዮች ውሳኔ የሚያገኙት ተከሳሾች በሚሰጡት የእምነት ቃል ነው። የእምነት ቃል ተቀባይነት እንዲኖረው የሚያደርጉ ሁኔታዎች/ ምክንያቶች :: ለምሳሌ:- የአሜሪካን ኣገር ብንወስድ

ሀ) የእምነት ቃል ከመሰጠቱ በፊት የሕግ ኣማካሪ (ጠበቃ) እና ከጠበቃው ለመነጋገር የሚያስችል በቂ ጊዜ ሊያገኝ ይገባል።
ለ) ፍ/ቤቱ ሌላ ኣስፈላጊ ምክር መስጠት ኣለበት። ከሚሰጠው ምክር ኣነዳንዶቹ ለመጥቀስ ያህል የቀረበበት ክስ በሚገባ የተረዳው መሆኑን ማረጋገጥ፤ በጁሪ ኣልዳኝም የማለት መብት እንዳለው ሊወሰንበት የሚችል ኣነስተኛ እና ከፍተኛ ቅጣት ምን እንደሆነ እና ሌሎች ተጨማሪ ቅጣቶችም ሊወሰንበት እንደሚችል መንገር
ሐ) የሚሰጠው የእምነት ቃል በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ማረጋገጥ አና
መ) ክሱ የፍሬ ነገር መሰረት ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ናቸው።

የኮንቲኔንታል የሕግ ስርዓት የሚከተሉ ኣገሮች ግን ተከሳሹ በሰጠው እምነት ቃል መሰረት ብቻ እነዲፈረድበት ፍ/ቤቱን በአፅንኦት ያሳሰበ ካልሆነ በስተቀር ከጣልያን በስተቀር በሌሎች ኣገሮች ተቀባይነት የለውም። ስለዚህ ተከሳሽ የእምነት ቃል ቢሰጥም ማስረጃ የግድ መስማት ኣስፈላጊ ተደርጎ ይወሰዳል።

የአገራችን የሕግ ስርዓት ስንመለከት ደግሞ መጀመሪያ የተከሳሹ እምነት ክህደት ቃል ከመጠየቁ በፊት ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ በሚገባ እንዲረዳው ፍ/ቤቱ የክሱን ዝርዝር ለተከሳሹ ማስረዳት አለበት (የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.132 (1) እና ሕገ መንግስት ዓንቀፅ 20 (2)። በመሆኑም ፍ/ቤቱ ለተከሳሹ መግለፅ ያለበት ነገር ፤ የወንጀሉ ዝርዝር ፣ የወንጀሉ ኣፈፃፀም የሚያቁሙ የሕግ ፣ የሞራል እና የግዙፍ ተግባር ጠባዮች ሁሉ (Legal, material and moral elements of the offence) (የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.111 (1) (ለ) እና የወ/ሕግ ዓነቀፅ 23 ፣ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ሊወሰንበት የሚችለውን የቅጣት ዓይነትና የቅጣቱ መነሻና ጣሪያ ፣ የተከሳሹን ሕገ መንግስታዊ መብቶች ማለትም ፣ ያለመናገር መብቱን ፣ ክሱን ለማመን ወይም ለመካድ ሙሉ መብት እንዳለው እና ጥፋተኛነቱን ማረጋገጥ የዓ/ሕግ ግዴታ መሆኑንና ጥፋተኛነቱ በማስረጃ እስኪረጋገጥ ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት ያለው መሆኑን ነው። ኣስፈላጊው ገለፃ ከተደረገለት በኋላ ተከሳሹ የቀረበለትን ክስ መፈፀሙንና ጥፋተኛ መሆኑን የሚያምን ወይም የሚክድ መሆኑን ፍ/ቤቱ ይጠይቃል።

ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ላይ የተዘረዘረውን ወንጀል መፈፀሙን ያመነ እንደሆነ ፍ/ቤቱ የእምነት ቃሉን ወድያው መቀበል የለበትም። ቃሉን ከመቀበሉ በፊት ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት። ኣንድ ተከሳሽ ለቀረበበት ክስ ሙሉ በሙሉ ኣምኗል የሚባለዉ መቼ ነው? የሚል ጥያቄ በዚህ አጋጣሚ ማንሳት ተገቢነት አለው። ተከሳሹ ወንጀሉን ፈፅሜኣሎህ ብሎ ማመኑ ብቻ ሙሉ በሙሉ ማመኑን ኣያረጋግጥም። ሙሉ በሙሉ ኣምኗል የሚባለው የእምነት ቃሉን የሰጠው በነፃ ፈቃዱ (voluntarily) መሆኑ ሲረጋገጥና ወንጀሉን ለመፈፀሙ የሚያመለክቱ መሰረታዊ እውነታዎች (Factual basis) መኖራቸው ሲረጋገጥ ነው።

ፍ/ቤቱ እነዚህን ሁኔታዎች ለማጣራት የሚከተሉትን ማጣሪያዎችና ገለፃዎች ማከናውን አለበት፣

ሀ) ተከሳሹ የወንጀሉን ዝርዝር በትክክል መረዳቱን ጠይቆ ማረጋገጥ ፣
ለ) የተከሳሹን የእምነት ቃል ፍ/ቤቱ ከተቀበለው ወድያው የጥፋተኛነት ውሳኔ እንደሚሰጥና ተከሳሹ የመከላከል መብት እንደማይኖረው ማስረዳት ፣
ሐ) ወንጀሉን መፈፀሙን እንዲያምን ተፅእኖ ወይም ማስፈራራት ደርሶበተ እንደሆነ ይህንኑ ከተከሳሹ ጠይቆ ማረጋገጥ ፣
መ) ተፅዕኖ ደርሶበት እንደሆነ ያለ ፈቃዱ እንዲያምን መገደድ እንደሌለበት ማስረዳት፣
ሠ) በክስ ማመልከቻው ላይ የተዘረዘረውን የወንጀሉን ኣፈፃፀም ዝርዝር ተከሳሹ ፈፀምኩ ከሚለው አገላለፅ (አነጋገር) ጋር በማስተያየት እንዲሁም ተከሳሹ ቢክድ ኖሮ ዓ/ሕግ ሊያቀርብ ያዘጋጀውን ማስረጃ በአጭሩ በመጠየቅ ተከሳሹ ወንጀሉን ለመፈፀሙ የሚያሳዩ መሰረታዊ እውነታዎች (Factual basis) መኖራቸውን ማረጋገጥ አለበት።

ይህን ሁሉ ማጣሪያ ካደረገ በyላ ፍ/ቤቱ ሁለት ኣማራጮች ይኖሩታል፡፡ ይኸውም በተከሳሹ እምነት ቃል ላይ ጥርጣሬ ካደረበት ዓ/ሕግ ማስረጃውን እንዲያሰማና ተከሳሹም የመከላከያ ማስረጃውን እንዲያቀርብ ለመፍቀድ ይችላል (ቁ.134 (2))። ባደረገው ማጣሪያ የተከሳሹን የእምነት ቃል ከተቀበለው ግን ተከሳሹ ጥፋተኛ ነኝ ብሏል በማለት ከመዘገበ በኃላ ከዚህ ጋር ተያይዞ ሲነሳ የሚገባው ነጥብ የስነ ስርዓት ሕጉ በተከሳሹ እምነት ቃል ብቻ ውሳኔ ሊሰጥባቸው የሚችሉና የወንጀል ክሶች ቢኖሩም ከወንጀሉ ከባድነት ኣንፃር ታይቶ ማስረጃ ሲሰማባቸው የሚገባ የወንጀል ዓይነቶች ለይቶ ኣለማስቀመጡ ነው። በልምድ እንደሚሰራበት ግን በዕድሜ ልክ ወይም በሞት ሊያስቀጣ በሚችል ወንጀል የተከሰሰ ሰው ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ቢያምንም ፍ/ቤቱ ማስረጃ እንዲቀርብ የሚያዝበት ሁኔታ ነው ያለው።

የፍትሕና ሕግ ስርዓት ምርምር ኢንስቲቱት ባዘጋጀው የወ/ሕ/ስ/ስ/ ረቂቕ በዓንቀፅ 128 ላይ እንደተመለከተው ከሆነ ግን በተከላሹ እምነት ቃል ብቻ ሊወሰኑ የማይችሉና የሚችሉ ለይቶ ኣስቀምጧል። የዓንቀፁ ይዘት እንደሚከተለው ይላል።

ተከሳሹ ጥፋተኛ ነኝ በማለት የእምነት ቃሉን ቢሰጥም ፍ/ቤቱ ማስረጃ ሰምቶ መወሰን ኣለበት። ሆኖም የክስ ኣቤቱታ በማቅረብ በሚያስቀጣ በማንኛውም ወንጀል ወይም በደንብ መተላለፍ ፍርድ ቤቱ ማስረጃ ሳይሰማ በተከሳሹ የእምነት ቃል ብቻ የጥፋተኛነት ውሳኔ ለመስጠት ይችላል።

ይህ ረቂቅ እንዳለ ወይም በተወሰነ መልኩ በማሻሻል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀው እንደሆነ ካለማወቃቸውና የባለሙያ ድጋፍ ሳያገኙ ወይም በሌላ ምክንያት ያልፈፀሙትን ወንጀል ፈፅመናል ብለው ለሚያምኑ ተከሳሾች ጠቃሚና በሚያስተማምን ማስረጃ ተንተርሶ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል።

ሆኖም በተግባር በተደጋጋሚ እንደሚታየው ተከሳሹ የተከሰስኩበት ወንጀል ፈፅሜዋሎህ፣ ጥፋተኛ ነኝ በማለት የእምነት ቃሉን ሲሰጥ ወንጀሉን ለምንና እንዴት እንደፈፀመው የሚያመለክት ዝርዝር ሁኔታ ሲገልፅ አይታይም ፣ ፍ/ቤቱም ይህን ዝርዝር ነገር እንዲገልፅ የማያደርግ መሆኑን ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ ተከሳሽ የሰጠው የክህደት ቃል መሆኑ በግልፅ የሚያሳይ እያለ የእምነት ቃል ሰጥቷል እየተባለ የጥፋተኛነት ፍርድ ሲሰጥ ይታያል።

17/03/2023

ደመወዝ 35,803
መደብ -የህግ ምክር አገልግሎት ሀላፊ

ለዳኝነት ይወዳደሩ!
06/02/2023

ለዳኝነት ይወዳደሩ!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጥብቅናና ህግ ምክር አገልግሎት -TheLawyers' Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የጥብቅናና ህግ ምክር አገልግሎት -TheLawyers' Office:

Share