Like tube

Like tube this page is useful

11/09/2025

እግዚአብሔር ይመስገን!

30/04/2025

መብራት ኃይል የቤት እቃውን ሁሉ አቃጠለው ምን ይሻላል እንደው?

29/09/2022

የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የሕይዎት ታሪክ
ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ከእናቱ ከወይዘሮ ሀገርነሽ ዋሴ ከአባቱ አቶ አፈወርቅ መንግሥቱ በ1970 ዓ.ም በጎንደር አዘዞ ተወለደ፡፡ በተወለደ በ3 ወሩም ወላጆቹ ኑሯቸውን በደብረታቦር ከተማ አደረጉ፡፡ በዚያም እድሜው ሲደርስ በደብረታቦር ከተማ ከዘመናዊ ትምህርት ጋር ተዋውቋል፡፡ ማዲንጎ የሙዚቃ ፈርጥነቱን ለመጀመር ማይክ የጨበጠው ገና በ9 ዓመቱ በቀበሌ ኪነት ነበር፡፡ በኋላም ድምፀ መረዋነቱን የተመለከቱት የ603ኛ ክፍለ ጦር አባላት ወደ ባሕርዳር ይዘውት ተጉዘው ዛሬ የተጎናጸፈውን ክብሩን አሀዱ እንዲል አደረጉት፡፡
ማዲንጎ በባሕር ዳር የጀመረውን የጥበብ ሥራ ለማሳደግ ወደ አዲስ አበባ አቅንቶ መጀመሪያ እርጎየዎች ጋር ከዚያም ላፎንቴኖች ጋር ሠርቷል፡፡
ድምጻዊ ማዲንጎ በ1989 ዓ.ም ከሁለት ጓደኞቹ ጋር የቲሸር ባንድ አልበሙን አሳትሞ ለሕዝብ ጀሮ አድርሷል፡፡በ1991 ዓ.ም ያወጣው “ስያሜ አጣሁላት” አማን ነወይ ጎራው የሚለው የሙዚቃ ክሩ ይበልጥ በሰዎች ዘንድ ተወዳጅነትን እንዲያገኝ አደረገው፡፡ በ1997 ዓ.ም በኤልያስ መልካ ተቀናብሮ ለሕዝብ ጀሮ የደረሰው “አይደረግም” አልበም “እልፍ ሲሉ እልፍ እየተገኘ ደሀ ነው በልቡ ሞትን የተመኘ “የሚል ስንኝ የቋጠረባትን ዘፈኑን ለሕዝብ አደረሰ፡፡
በ2007 ዓ.ም ስወድላት የሚለውን አልበም በድምፀ መረዋ ድምጹ ሥራውን በማቅረብ አድናቆትን አትርፏል፡፡
ማዲንጎ ከአልበሞቹ በተጨማሪ ነጠላ ዜማወችን ሠርቷል የኢትዮጵያ ሚሊኒየም ሲከበር የበዓሉ ድምቀት ነበር፡፡ የፊልም ማጀቢያ ሙዚቃዎችንም ሠርቷል፡፡
ሀገር አጣብቂኝ ውስጥ በገባችበት ወቅት ግንባር ድረስ ወርዶ ጀግኖችን በማበርታቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡
ማዲንጎ ለወንድም እና እሕቶቹ እንዲሁም ጓደኞቹ የሥራ ፈር ቀዳጅ በመኾን መንገዱን አሳይቷል፡፡ ማዲንጎ ደግ ሩህሩህ እና ለሰው አዛኝ በመኾኑ የተቸገሩትን በመርዳት የድርሻውን ተወጥቷል፡፡
ማዲንጎ አፈወርቅ ባለትዳር እና የአንዲት ሴት ልጅ አባት ሲኾን በማኅበራዊ ሕይወቱም ለበርካቶች መጠጊያ ነበር፡፡ ማዲንጎ በጡረታ የተገለሉ የሙያ አባቶች እና እናቶችን በመጠየቅ ቅድሚያውን ይወስዳል፡፡
አራራይ የሙዚቃ የመረዳጃ ማኅበር መስራች እና አባል ነበር፡፡ ማዲንጎ አዲስ አልበም ለማሳተም ዜማ እና ግጥም አጠናቆ ነበር፡፡ ተወዳጁ ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ በተወለደ በ44 ዓመቱ መስከረም 17/2015 ዓ.ም በድንገት አርፏል፡፡
የሙያ አጋሮቹ የጥበብ አድናቂዎቹ እና ቤተሠቦቹ በተገኙበት መስከረም 19/2015 ዓ.ም በቅድስት ስላሴ ካቴዴራል ቤተክርስቲያን የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ይፈጸማል፡፡

05/09/2022

*(ጃማ ደጎሎ)*
************
ጃማ ወረዳ በአማራ ቢሄራዊ ክልላዊ መንግስተ በደ/ወሎ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንዷ ናት፡፡የወረዳዋ የቆዳ ስፋት 529.621እስኮየር ካሬ ወይንም 129.251.2ሄ/ር ነው፡የህዝቧ ብዛት ወ-72580 ሴ-71831 አጠቃላይ=144411 ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡የጃማ ወረዳ እርሰ ከተማ ደጎሎ ስትሆን ስያሜዋን ያገኘችው ከሸዋ የመጡ እንግዶ የህዝብን ርህሩህነትና ደግነት በማየት ደግ ወሎ ማለትም ወሎ ደጉ ብለው ሰየሞት፡፡
ደጎሎ ከተማ ከአዲስ አበባ 260 ኪ.ሜ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ደሴ 120 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
በደቡብ ፡ሚዳ ወረሞ ወረዳ
ከሰሜን፡ወራኢሉ ወረዳ
ከምስራቅ ፡መንዝ ጌራ ወረዳ
ከምዕራብ ፡ከላላ ወረዳ ያዋስኖታል፡፡
ጃማ ወረዳ 22 የገጠር ቀበሌ እና 2 የከተማ ቀበሌ በአጠቃላይ 24 ቀበሌዎችን በውስጧ አቅፋለች፡፡
የወረዳዋ ህዝብ መተዳደሪያ በአብዛኛው ግብረናና ንግድ ሲሆን የወረዳዋ አቀማመጥ 58.5 ሜዳ 29.3 ወጣ ገባ 12.2 ቆላማ ነው አመታዊ አማካኝ የዝናብ መጠን 1130ሚ.ሜ ነው፡፡
በወረዳዋ የሚገኙ የአፈር አይነቶች ቀይ አፈር 10% ጥቁር 63% ግራጫ አፈር 17% ነው፡፡
ወረዳዋ ከመሠረተ ልማትና ከማህበራዊ አገለግሎት አንፃር የተሻለ ተጠቃሚ እየሆነች ትገኛለች ፡፡
በጤናው ዘርፍም 6 ጤና ጣቢያ 22 ጤና ኬላ 1ጠቅላላ ሆስቢታል ይገኙባታል፡፡
በትምህርቱም ዘርፍ 1-4ኛ 36ት/ቤት 1-8ኛ 26ት/ቤት 9-10ኛ 3ት/ቤት 9-12ኛ 1ት/ቤት በድምሩ 66ት/ቤቶች ይገኛሉ፡፡
ከተማዋ ከአ/አ ደጎሎ ከደጎሎ ከላላ እንዲሁም ከደጎሎ ወራኢሉ ከወራኢሉ ደሴ አቆርጦ የሚያልፍ ምቹ መስመር አላት ሆኖም ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነች አቀማመጥ አላት፡፡የመንገዱም ደረጃ ወደ አስቫልት ለማሳደግ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደ ተግባር በመግባት ላይ ነው፡፡
በከተማዋ 33ሚሊየን ብር የፈጀ ትልቅ የዱቄት ፍብሪካ አግልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የፖስታና ማካሮኒ ስራ ለመጀመር ትልቅ ፋብሪካ ለመክፈት የመሬት ርክክቡ ተጠናቆ ግንባታ በመጀመር ላይ ይገኛል ፡፡ከዚህም ሌላው ትልቅ የገበያ ማዕከል ለመክፈት የመሠረት ድንጋይ በከተማዋ ተቀምጧል፡፡
በወረዳዋ ዘመናዊ ሆቴሎች፣ፔንሲዎኖች፣እንዲሁም ሱፐር ማርኬቶች የመሣሠሉ የንግድ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ደረጃውን የጠበቀ ህንፃወች በመገንባት ላይ ይገኛሉ፡፡በከተማዋ የኢትዮጰያ ንግድ ባንክ፣አቢሲንያ ባንክ፣በቅርቡ ይከፈታል ተብሎ የሚጠበቀው አባይ ባንክን ጨምሮ አግልግሎት ይሰጣሉ፡፡
በወረዳዋ ለቱሪስት መስህብ የሚሆኑ የተፈጥሮ ቅርሶችም አሏት በምችግ የሚገኘው ተነባብሮ የተሚገኘው የተፈጥሮ ቀይ ድንጋይ ቀልብን የሚስብ ድንቅ ተፈጥሮ አንዱ የቱሪስት መስህብ ነው፡፡ እንዲሁም ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ገዳማት በአፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግስት 4ኛ ክ/ዘመን የአህያ ፈጅ ብስቋም ማርያም ጥንታዊ ገዳም ትገኛለች፡፡ አቀማመጧ ተራራ ላይ ሲሆን በሶስት ተራሮች የተከበበች ናት ፡፡በእስልምናውም ጥንታዊ የእምነት ቦታዎችን እናገኛለን በአመት አንድ ግዜ የመውሊድ ስነ ስርአት የሚከበርበት ታላቁ የጃማኦ ሸህ በውስጡ ይገኛል፡፡
ጃማ ወረዳ የሀይማኖት መቻቻል በሰፊው ያለባት የወሎ ተምሳሌት በመባል ትታወቃለች፡፡
የሁለቱም ዕምነት ተከታዮች በሰላም በፍቅሩ ተቻችለው የሚኖሩባት ሀገር ነች ፡፡የሀይማኖት ብዛቷም ክርስትና =55% እስልምና=45% የእምነት ተከታዮች ይኖራሉ ተብሎ ይገመታል ፡፡
ጃማ ወረዳ በግብርናው ዘርፍ በሰፊው ትታወቃለች፡፡
ጃማ ወረዳ ከዚህም ባሻገር በይበልጥ ስሟን የሚያስጠራት እጅ የሚያስቆረጥመው በችስቻሶዋ ትታወቃለች :-ጃማ ምድረ ገነት
ችስቻሶሽ

ህፃናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደረገችው የቤት ሠራተኛ ፍርድ ቤት ቀረበች(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)ፍርድ ቤቱ የህጻን ግዮናዊት መላኩ እና ህጻን ክርስቲና መላኩን በአሰ...
05/09/2022

ህፃናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደረገችው የቤት ሠራተኛ ፍርድ ቤት ቀረበች
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
ፍርድ ቤቱ የህጻን ግዮናዊት መላኩ እና ህጻን ክርስቲና መላኩን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች የተባለችው ተጠርጣሪ ላይ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ እንዲያደርግ የ14 ቀን ጊዜ ሰጠ።
ተጨማሪ ምርመራ እንዲደረግ የ14 ቀን ጊዜ የፈቀደው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው።
ተጠርጣሪ ህይወት መኮንን ሀይሉ በነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠኋቱ 3:30 ላይ በለሚኩራ ክ/ከ አራብሳ ኮንዶሚኒዬም ተቀጥራ በምትሰራበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የህጻን ግዮናዊት መላኩ አፏን በማፈን በቢላ በማረድ ህይወቷ እንዲያልፍ ማድረጓን እና ህጻን ክርስቲና መላኩን ደግሞ አፍፏን በማፈን በማነቅ በአጠቃላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረጎን ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል።
በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዋን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ የሰው ማስረጃ ለማሰባሰብና የግድያ ወንጀል የተፈጸመበትን ትክክለኛ ምክንያት በማስረጃ ለማረጋገጥ እንዲሁም በተጠርጣሪዋ ዙሪያ ያሉ ግለሰቦች ላይ ማስረጃ ለማሰባሰብና በወንጀሉ ስፍራ የተገኘ ስለታማ ቢላን በፎረንሲክ ለማስመርመር በተጨማሪም የአስከሬን ምርመራ ውጤት ለማምጣት በወ/መ/ስ/ህ /ቁ. 59/1 መሰረት የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጠርጣሪዋ በኩል ምንም አስተያየት ያልቀረበም።

የምርመራ መነሻ መዝገብን የተመለከተው የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪዋ ላይ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ እንዲያደርግ የ14 ቀን ጊዜ ፈቅዷል።
ምንጭ፦ ታሪኩ አዱኛ

አዝናኝና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ ሃሳቦችን በሰፊውA wide range of fun and engaging ideas

02/09/2022

“ካሳንቺስ ባዛር ” ከዛሬ ጀምሮ ይከፈታል።

ቡሽሜን አርትና ኤቨንት ኦርጋናይዘር ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽህፈት ቤት ጋር በመቀናጀት ካሳንቺስ ባዛር በሚል ስያሜ ካሳንቺስ ስድስት ኪሎ ታክሲ መያዣ ፊት ለፊት የ2015 ዓ.ም አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የንግድ አውደርእይ ከዛሬ ነሐሴ 27 ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2014 ዓ.ም ይካሄዳል።

አምራች እና አከፋፋይ ድርጅቶች የሚሳተፋበት በዚህ የንግድ አውደ ርዕይ ላይ አልባሳት ፣ መዋቢያ እቃዎች ፣የትምህርት ግብዓት ቁሳቁሶች፣ የቤት እቃዎች ፣ ለበዓሉ ደግሞ የበግ ፣ የዶሮ ፣እንቁላል መሠል ምርቶች በቅናሽ ዋጋ የሚቀርብበት ነው።

የቄርቆስ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጥላሁን ፈይሳ አውደርዕዮን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጡት መግለጫ ላይ አምራች እና ሸማችን የሚያገናኘው ይህ አውደ ርዕይ የተሳካ እንዲሆን ትብብር ላደረጉ የካሳንችስ አካባቢ ወጣቶች ቦታውን ለፈቀዱ ባለሀብት እና በዚህ ኘሮግራም ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ቡሽሜን አርትና ኤቨንት ኦርጋናይዘር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንገሻ ተሰማ የንግድ አወደ ርዕዮን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ላይ ከ “ካሳንቺስ ባዛር ” የንግድ አውደርእይ ከሚገኝ ገቢ ላይ ለ 500 አረጋውያን የበዓል መዋያ የሚሰጥ ሲሆን በተጨማሪም ለኵላሊት ህመምተኞች ማእከል የገንዘብ ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

02/09/2022

በጎንደር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ውሳኔ

ለመላው የጎንደር ህዝብ ለሶስተኛ ዙር አገራችን ለማፈራረስ ወራሪዉ ሃይል ጦርነት ለኩሷል ፡፡

ስለሆነም አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡

ጥምር ጦራችን በሁሉም ግንባር በሙሉ ብቃትና ወኔ ጠላትን እየመከተ እየደመሰሰ ይገኛል፡፡ ስለሆነም የጎንደር ከተማ አስተዳደርና የፀጥታ ምክር ቤት ማህበረሰባችን ራሱን ማዘጋጀትና የከተማችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል
የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡

1. ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማችን በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡

2. ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ የተከለከለ ነው፡፡

3. ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ ማሰጨነቅ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

4. በከተማችን የሚገኙ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡

5. በተለያዩ አሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት የተከለከለ ነው፡፡

6. ማንኛውም የግል ሆነ የመንግስት ተሸከርካሪ ለፀጥታ ስራ ሆነ ለዘመቻ የሠው ሃይል ለማንቀሳቀስ በሚመለከታቸው የዘመቻ ማምሪያ ኮማንድ ፖስት ትብብር ሲጠየቅ የመተባበር ግዴታ አለበት ላለመተባበር ተሸከርካሪን የሚሸሽግ፣ የሚያሸሽ ሆን ብሎ ተበላሸ በሚል ላለመተባበር ጥረት የሚያደርግ ተጠያቂና የጥፋት ኃይሎች ተባባሪ ተደርጎ ስለሚቆጠር ከዚህ አይነት ጥፋት በመቆጠብ ኃላፊነትን መወጣት ይገባል፡፡

7. ማንኛውም የቤት አከራይ ወይም አልጋ የሚያከራይ፣ ሆቴሎች፣ ፔንሲዮኖች ተከራዮቻቸውን እና ተጠቃሚዎቻቸውን የመለየትና ማንነታቸውን የመለየት፣ የታደሰ ህጋዊ መታወቂያ ስለመኖራቸው የማረጋገጥ ግዴታ እና አስፈላጊውን መረጃ ይዞ ለጸጥታ አካል ሪፖርት የማድረግ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት

8. ማንኛውም ሰው ፀጉረ ልውጥ ሰው ሲያጋጥመው በቅርብ ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆም ኃላፊነት አለበት

9. ከነሀሴ 27/2014 ዓ.ም ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት የተከለከለ ሲሆን አስቸኳይ የሆነ ጉዳይ የገጠመው ለምሳሌ ለህክምና መታወቂያ ቢያስፈልግ፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ ቢያስፈልግ፣ ወደ ውጭ አገር የሚያስፈልግ ጉዞ የመሳሰሉት አስቸኳይ ጉዳዮች ከገጠሙና መታወቂያ መስጠት ካስፈለገ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ የመስጠት ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ

10. ማንኛውም የመንግስት የግል ታጣቂ አካባቢውን በብሎክ አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነት ግዴታ አለበት

11. አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

12. ከከተማ ውጭ ወደ ከተማው ለጸጥታ ስራ፣ ሆነ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Like tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share