ጠበቃ ይልቃል/Attorney Yelkal Yizengaw

ጠበቃ ይልቃል/Attorney Yelkal  Yizengaw Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጠበቃ ይልቃል/Attorney Yelkal Yizengaw, Lawyer & Law Firm, Belay Zeleke Street, Addis Ababa.

ወቅታዊ የተሻሻሉ፣አዲስ የወጡ ህጎች፣የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔወች፣ጠቃሚ የህግመረጃወች በዚህ ገጽ ለተከታዮቻችን እናደርሳለን።
በማናቸውም ጉዳይ ጥብቅና ለማቆም
ለህግ ምክር አገልግሎት።
(+251) 0975121866
or(+251)0941696748
https://t.me/yilkalyizengaw

03/06/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Solomon Getachew, Teklewyni Geb Micael, ማቴዎስ አለማየሁ, Haataatu Ni Danda'ama

የፌድሬሽን ምክር ቤት በመ/ቁጥር 108/15 ከፌድራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር ተጠሪ በነበረው የቤት ይዞታ ክርክር የተሰጠ ውሳኔ1. የክርክሩ አመጣጥ በአጭሩተጠሪ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ...
27/05/2026

የፌድሬሽን ምክር ቤት በመ/ቁጥር 108/15 ከፌድራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር ተጠሪ በነበረው የቤት ይዞታ ክርክር የተሰጠ ውሳኔ
1. የክርክሩ አመጣጥ በአጭሩ
ተጠሪ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረቡት አቤቱታ በካርታ ቁጥር 29252 የይዞታ ማረጋገጫ የእኔ የሆነውን ይዞታ በአደራ ለጥበቃና ለቤት ሰራተኛ ሰጥቼ ወደ ውጭ ሀገር ስሄድ መንግስት ይህንን ይዞታ ወስዶብኛል። ይህንን ለማስመለስ ፕራይቬይታይዜሽን ኤጄንሲ ባመለክትም ጉዳዩን ለማየት ስልጣን የለኝም በማለቱ ጉዳዩን ለፌደራል መጀመሪያ ደረጀ ፍርድ ቤት አመልክቶ ይህ ይዞታና ቤት ለተጠሪ እንዲመለስለት የወሰነ ሲሆን ይህንን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲሁም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም አጽንቶታል። ይሁን እንጂ የፌደረሽን ምክር ቤት በፍርድ ቤቶች የተሰጠውን ውሳኔዎች በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን የህግ ትርጉም ውሳኔዎች ጨምሮ ሽሮታል።
2. የፌደሬሽን ምክር ቤት የሻረበት ህጋዊ እና የፍሬ ነገር ምክንያቶች
2.1. አንዱና ዋናው ምክንያት ይህ ምክር ቤት የሻረበት ምክንያት
የፌደራል ፍርድ ቤት ይህን ጉዳይ ለመመልከት ስልጣን የለውም የሚል ሲሆን ለዚህም ይህንን ከአዋጅ ቁጥር 47/67 ውጭ በመንግስት እጅ የገቡ ቤቶችን በተመለከተ እንዲሁም ቤቱ በህግ አግባብ የተወረሰ ነው ወይንስ ያልተወረሰ ነው ? የሚለውን የዳኝነት ጥያቄ ለማየት እና ለመወሰን ስልጣን ያለው በአዋጅ ቁጥር 110/89 መሠረት የፕራይቬታይዜሽን ኤጄንሲ እንጂ መደበኛ ፍርድ ቤት አይደለም የሚል ነው።
2.2. ሌላው የማስረጃ ምዘና በተመለከተ ሲሆን ፍርድ ቤቶች አመልካች ቅጽ 003 መረጃ ስለ ቤቱ በተመለከተ አላቀረበም በሚል የመጨረሻ መደምደሚያ በማድረግ ለአመልካች መወሰናቸው ቤቱ ከመንግስት እጅ ከቆየ 40 አመት የሆነው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አሳማኝነቱ አግባብ እንዳልሆነ በፍርድ ያብራራ ሲሆን ይህ ቤት የተወረሰ ሳይሆን በህገወጥ መንገድ በመንግስት የተያዘ ስለመሆኑ ተጠሪ በማስረጃ አላስረዳም። በተጨማሪም የማስረዳት ሸክሙን በተመለከተ በስር ፍርድ ቤት በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 358 መሠረት እንዴት በስር ፍርድ ቤት ከከሳሽ ወደ ተከሳሽ የሄደበት መንገድ ግልጽና ምክንያታዊ አለመሆኑን አትቷል
2.3 . ሌላው በምክንያትነት በሀተታው ያስቀመጠው ጉዳዩ አስቀድሞ በፕራይቬታይዜሽን ኤጄንሲ ቤቱ መመለስ የሌለበት መሆኑ ወስኖ እያለ በድጋሚ እንደ አዲስ በመደበኛ ፍርድ ቤት መታየቱ አግባብነት የሌለው መሆኑን በፍርዱ ያተተ ሲሆን ይህም በፍ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 5 እና 244/2/ለ/ ላይ ከተቀመጠው ጋር የሚያያዝ ነው።
2.4. የተጠሪ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በተመለከተ የመከነ መሆኑን ገልጾ ከአዋጁ 47/67 ውጭ በህገወጥ መንገድ ከተያዘ በአቀጽ 12/2/ መሠረት አዲስ ካርታ ሊይዙ የሚገባ ሲሆን በዚህ መንገድ ተጠሪ የራሳቸው የይዞታ ካርታ የላቸውም። በፊት የነበራቸው ካርታ ከፍ/ህግ ቁጥር 1195 አንጻር ተገቢነት የለውም ሲል በምክንያትነት አስፍሯል
3. በአጠቃላይ ከማስረጃ ምዘና እና ጉዳዩ ተቀብሎ ለማየት ካለው ስልጣን አንጻር በስር ፍርድ ቤቶች እስከ ፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ የተሰጠው ውሳኔ የህገመንግስቱን አንቀጽ 37/1/ ላይ የተቀመጠውን ሚዛናዊ አያደርግም በማለት ውሳኔ
https://t.me/yilkalyizengaw

17/05/2026

With Sam Man Brovn Mulugeta – I just got recognized as one of their top fans!

07/05/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mwg L Wgl, Ye Wusane Sew, Alex Tamene, Sam Man Brovn Mulugeta, Tme Lij

01/05/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Belayneh Assefa, Md Rq

ሰበር በቅፅ 28 በሰ/መ/ቁ 150290 በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም በባንክ የገንዘብ ሐዋላ መላኪያ ወረቀት ሰነድ ገንዘብ መላኩን ከማስረዳት ውጪ በምን ምክንያት ገንዘቡ መላኩን ወይም ገን...
25/03/2026

ሰበር በቅፅ 28 በሰ/መ/ቁ 150290 በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም

በባንክ የገንዘብ ሐዋላ መላኪያ ወረቀት ሰነድ ገንዘብ መላኩን ከማስረዳት ውጪ በምን ምክንያት ገንዘቡ መላኩን ወይም ገንዘቡ በብድር፣በአደራ የተሰጠ መሆኑን ሊያስረዳ የማይቻል ስለመሆኑ። የፍ/ሕ/ቁጥር 2472፣ 2782/1/2/2802/2 ጠቅሶ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
https://t.me/yilkalyizengaw

13/03/2026

Federal Supreme Court is the highest court in Ethiopia. It is constitutionaly established court. It is also one of the three pillars of the federal state that assures the check and balance in & among.

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ: መዝገብ ቁጥር 244308******ከዚህ ቀደም በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 የተሰጠው ውሳኔ መሰረት በማድረግ በከተማ ...
13/03/2026

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ: መዝገብ ቁጥር 244308
******
ከዚህ ቀደም በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 የተሰጠው ውሳኔ መሰረት በማድረግ በከተማ ክልል ያለን ይዞታ ለማስመለስ የቀረበ የመፋለም ክስ በይርጋ አይታገድም በሚል በሰበር መዝገብ ቁጥር 210477 የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ተቀይሯል፡፡

ከከተማ መሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ አለአግባብ ከያዘ ሰው ላይ ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በአስር ዓመት ይርጋ ይታገዳል ተብሎ ተተርጉሟል፡፡ሙሉ ውሳኔውን በቴሌግራም ይከታተሉ


https://t.me/yilkalyizengaw

Federal Supreme Court is the highest court in Ethiopia. It is constitutionaly established court. It is also one of the three pillars of the federal state that assures the check and balance in & among.

የቤተሰብ ህግ በሰበር ችሎት 📢 አዲስ የህግ መጽሐፍ የቅድመ-ትዕዛዝ ጥሪ! "የቤተሰብ ህግ በሰበር ውሳኔዎች" — በአቀራረቡ ለየት ያለና በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች...
22/02/2026

የቤተሰብ ህግ በሰበር ችሎት

📢 አዲስ የህግ መጽሐፍ የቅድመ-ትዕዛዝ ጥሪ!

"የቤተሰብ ህግ በሰበር ውሳኔዎች" — በአቀራረቡ ለየት ያለና በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ላይ ያተኮረ አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለህትመት ይበቃል።

በአሁኑ ወቅት የህትመት ዋጋ መናር ስራዎችን ለህዝብ ለማድረስ ፈታኝ ቢሆንም፣ ይህ እውቀት ለባለሙያውና ለአንባቢው እንዲደርስ ለማድረግ በጣም ውስን ኮፒዎችን (ከ300-500 ብቻ) ለተመዝጋቢዎች ለማቅረብ ተዘጋጅተናል።

🎯 የምዝገባ አማራጮች እና ልዩ ጥቅሞች
መጽሐፉን በሁለት መንገድ መመዝገብ ይችላሉ፦

1. ቅድሚያ ገዢ (Early Bird):
ቅድሚያ ክፍያ በመፈጸም መጽሐፉ እስኪወጣ ለሚጠብቁ ደንበኞች የሚከተሉት ልዩ የቴክኖሎጂ ጥቅሞች ለተወሰነ ጊዜ በነጻ ይሰጣሉ፦

* Desktop Application: ከቅፅ 1-28 ያሉ፣ የ7 ዳኞች ትርጉም፣ የህፃናትና ሴቶች ጉዳይን ጨምሮ ከ 10,000 በላይ የሰበር ውሳኔዎች ማጠቃለያ የያዘ። እያንዳንዱ ማጠቃለያ የክርክሩን አመጣጥ፣ ቁልፍ የህግ ትርጉም እና የፍርዱን አመክንዮ በዝርዝር የያዘ ሲሆን፤ ፈጣንና ዘመናዊ መፈለጊያ (Search) ተገጥሞለታል።

* Mobile Application: ከ10 ሺህ በላይ ውሳኔዎችን "የአንድ መስመር" ማውጫ የያዘ መተግበሪያ።
2. ኋላ ገዢ (Standard):
መጽሐፉ ሲታተም ክፍያ ፈጽመው መጽሐፉን ብቻ በአድራሻቸው የሚረከቡ።

📘 የመጽሐፉ መረጃ
* ርዕስ፦ የቤተሰብ ህግ
* የገጽ ብዛት፦ 350
* ዋጋ፦ 1,000 ብር (Delivery/ማድረሻን ጨምሮ)

📝 እንዴት ይመዘገባሉ?
ኮፒው በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ስምዎትንና አድራሻዎትን በሚከተለው ስልክ ቁጥር ይላኩ፦

📞 ስልክ፦ 0915735560 (በText, Telegram ወይም WhatsApp)
ሲመዘገቡ የሚከተለውን መረጃ ያካትቱ፦
* ሙሉ ስም
* ስልክ ቁጥር
* አድራሻ (መጽሐፉ እንዲደርሶ የሚፈልጉበት)

* የምዝገባ አይነት፦ "ቅድሚያ ገዢ" ወይም "ኋላ ገዢ" በማለት ይጥቀሱ።

> ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉ ለተመዝጋቢዎች ብቻ የሚሸጥ ሲሆን፣ ርክክቡም ባለዎት አድራሻ ላይ በመመስረት በቤትዎ ወይም በቢሮዎ ድረስ በነጻ ይከናወናል።
>
ይህንን መልዕክት ለሌሎች የህግ ባለሙያዎች በማጋራት ይተባበሩ!

(ከታች ምስል mobile app screenshots)

Address

Belay Zeleke Street
Addis Ababa
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠበቃ ይልቃል/Attorney Yelkal Yizengaw posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ጠበቃ ይልቃል/Attorney Yelkal Yizengaw:

Share