ሙሉዘር የህግ አማካሪና ጠበቃ/ lawyer muluzer

ሙሉዘር የህግ አማካሪና ጠበቃ/ lawyer muluzer Any legal issues will be discussed

የአክሲዮን ማህበራትን  በተመለከተ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ  ነጥቦች         ነሀሴ 14/2018ከሃምሳ በላይ አባላት ያላቸው የአክስዮን ማህበራት በተቋሙ ቀርበው ድንገተኛ እና መደበኛ የ...
20/08/2026

የአክሲዮን ማህበራትን በተመለከተ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ነጥቦች
ነሀሴ 14/2018
ከሃምሳ በላይ አባላት ያላቸው የአክስዮን ማህበራት በተቋሙ ቀርበው ድንገተኛ እና መደበኛ የባለ አክሲዮኖች ጉባኤ የሚያስተላልፏቸው ውሳኔዎችን በተመለከተ፣
1. በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የቃለ ጉባኤ ሰነድ፣
2. ስብሰባው በመመስረቻ ጽሁፍ ወይም በህጉ መሠረት መጠራቱን የሚገልጽ ማስረጃ መቅረብ አለበት፡፡
3. ቃለጉባኤው የማህበሩ ሙሉ ስም፣ ስብሰባው የተደረገበት ቦታ፣ ስብሰባው የተደረገበት ቀን፣ በስባሰባው ላይ የተገኙ አባላት ዝርዝር፣ በስብሰባው ላይ ያልተገኙ አባላት ዝርዝር፣ የሁሉም አባላት የአክስዮን ድርሻ መጠን፣ የስብሰባው አጀንዳዎች፣ የውሳኔው ይዘት መግለጽ ይኖርበታል፡፡
4. በድንገተኛም ሆነ በመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተገኙ አባላትን የሚገልጽ የአቴንዳስ ሽት ከቃለ ጉባኤው ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
5. የድንገተኛም ሆነ የመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ቃለጉባኤዎች በተለያዩ ሰነዶች ተዘጋጅተው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. የአባላቱ ቀጥር ከ50 በላይ የሆነ አክሲዮን ማህበር ተቋሙ ሰነድ አረጋጋጭ ባለሞያ እንዲላክለት ሲጠየቅ ከደብዳቤ ጋር ስብሰባውን ማን እንደጠራ፤ የስብሰባውን አይነት ድንገተኛ ወይም ጠቅላላ ጉባኤ በሚል መለየት፤ ስንተኛ ጥሪ እንደሆነ፤ ጥሪ ያደረገበትን መንገድ እንዲሁም አጀንዳዎቹን አስቀድሞ ከደብዳቤው ጋር ሊገለፅ ይገባል፡፡
7. የአክሲዮን ማህበራት መመስረቻና መተዳደሪያ ደንባቸው ድንገተኛ ወይም መደበኛ ጠቅላላ ጉበኤዎችን የሚጠሩበትን የጥሪ መንገዶች ወስነው ስለመግለጻቸው ማረጋገጥ ይገባል፡፡
8. በአክሲዮን ማህበር ስብሰባዎች ላይ የሚቀርቡ አጀንዳዎች ከጉባኤው ስልጣን ውጪ መሆን አለመሆናቸውን በአግባቡ ማጣራት ያስፈልጋል፡፡
9. አክሲዮን በሽያጭ ከማህበሩ አባል ውጭ ለሆነ ሰው ሲዘዋወር በቅድሚያ ከማህበሩ አባላት በቀዳሚነት የመግዛት መብት የነበረባቸው ባለአክሲዮኖች በሰነዱ ላይ በመፈረም የተስማሙ ስለመሆናቸው ማረጋገጥ . ይገባል፡፡
10. በጥሬ ገንዘብ ካፒታልን ካሳደጉ በኋላ ይህንን ለማህበሩ የገባውን ገንዘብ በዓይነት መዋጮ ለመለወጥ የሚቀርብ ቃለጉባኤ የህግ መሰረት ስለሌለው ሊመዘገብ አይገባም፡፡ በዓይነት የገባውንም መዋጮ በተመሳሳይ ሁኔታ በጥሬ ገንዘብ መለወጥ አይቻልም፡፡
11. የንግድ ማህበራት በቃለ ጉባኤ የሚያደርጓቸው ማሻሻያዎች ሰነዱ ከፀደቀበት ቀን አንስቶ እስከ ሁለት ወር ድረስ ካላስመዘገቡ ተቋሙ አገልግሎት አይሰጥበትም፡፡
12. የንግድ ማህበራት የማፍረስ ውሳኔ ከወሰኑ በኋላ ማህበሩን በነበረበት ለማስቀጠል ከፈለጉ
ዋና ምዝገባና የንግድ ፈቃድ፣
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ማህበሩ ያልተሰረዘ ለመሆኑ፣
ከገቢዎች የድጋፍ ደብዳቤ ሊቀርቡ ይገባል፡፡

አንድ ሰው በፖሊስ ጣቢያ የሰጠው ቃል ፍርድ ቤት ቀርቦ ከሚሰጠው የምስክርነት ቃል ቢቃረን በሐሰተኛ ምስክርነት የማይቀጣ ስለመሆኑየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ...
16/07/2026

አንድ ሰው በፖሊስ ጣቢያ የሰጠው ቃል ፍርድ ቤት ቀርቦ ከሚሰጠው የምስክርነት ቃል ቢቃረን በሐሰተኛ ምስክርነት የማይቀጣ ስለመሆኑ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 153228 አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል።
*
በተጠቀሰው መዝገብ ላይ ሰበር ሰሚ ችሎቱ የደረሰበት ድምዳሜ ዓቃቤ ህግ ግለሰቦቹ በፖሊስ ፊት የሰጡትን ቃል ፍርድ ቤት ቀይረው ሀሰተኛ ምስክርነት ሰጥተዋል በማለት በወንጀል ህግ አንቀጽ 453(2) መሰረት ጥፋተኛ ሊባሉ አይገባም የሚል ነው።ሰበር ሰሚ ችሎቱ ምክንያት ያደረገውም ሁለት ምክንያቶችን ነው:-

1ኛ. ፖሊስ የዳኝነት አካል አይደለም! በወንጀል ህግ አንቀጽ 453 ስር "ሀሰተኛ ምስክርነት" የሚያስቀጣው በዳኝነት ወይም በዳኝነት መሰል (Quasi-Judicial) ሥርዓት ላይ ቀርቦ ሲዋሽ ብቻ ነው። ፖሊስ ደግሞ ወንጀል የሚከላከልና አካል እንጂ የዳኝነት ስልጣን የለውም።
2ኛ . ቃላት መቃረናቸው ብቻውን ጥፋተኛ አያደርግም።
አንድ ምስክር በፖሊስ ፊት የሰጠው ቃል እና ፍርድ ቤት የሰጠው ቃል ስለተቃረነ ብቻ በፍርድ ቤት የዋሸው ውሸት ነው ተብሎ በቀጥታ ሊደመደም አይገባም።
በሚል ነው።
የውሳኔውን ዝርዝር ይዘት ለመመልከት
https://t.me/futehir
https://t.me/futehir
https://t.me/futehir

የመኪና ሽያጭ ውል፣ስልጣን ባልው ኣካል ቀርቦ ካልተመዝገበ/ካልተረጋገጠ ሕጋዊ ውጤት የለውም።(source Khermed law firm)
12/07/2026

የመኪና ሽያጭ ውል፣
ስልጣን ባልው ኣካል ቀርቦ ካልተመዝገበ/ካልተረጋገጠ ሕጋዊ ውጤት የለውም።
(source Khermed law firm)

 ==========================በኢትዮጵያ የፍትሐ ብሔር ሕግ መሠረት፣ አንድ ወራሽ ከውርስ ሊነቀል (ሊገለል) የሚችልባቸው ግልጽ የሆኑ ሕጋዊ ምክንያቶች አሉ። ይህ በሁለት ዋና ዋ...
10/07/2026


==========================
በኢትዮጵያ የፍትሐ ብሔር ሕግ መሠረት፣ አንድ ወራሽ ከውርስ ሊነቀል (ሊገለል) የሚችልባቸው ግልጽ የሆኑ ሕጋዊ ምክንያቶች አሉ። ይህ በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከፈላል፦ በሕግ ምክንያት የሚመጣ መገለል (Unworthiness) እና በኑዛዜ የሚደረግ ስረዛ (Disinheriting)።

​ዋና ዋናዎቹ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፦
​1. በሕግ ምክንያት ከውርስ መገለል:- ​አንድ ወራሽ የሚከተሉትን ጥፋቶች ፈጽሞ ሲገኝ፣ በኑዛዜ ባይጠቀስም እንኳ በሕግ ፊት የመውረስ መብቱን ያጣል።

ሀ። ​ግድያ ወይም የግድያ ሙከራ፦ ወራሹ የሟቹን ሕይወት ሆን ብሎ ካጠፋ ወይም ለመግደል ሙከራ ካደረገ።

ለ/ ​የሐሰት ምስክርነት፦ በሟች ላይ የሞት ቅጣት ወይም ከአምስት ዓመት በላይ የሚያስቀጣ የሐሰት ምስክርነት ሰጥቶ ከሆነ።

ሐ/ ​ኑዛዜን ማጭበርበር፦ ሟቹ ኑዛዜ እንዳይጽፍ መከልከል፣ የተጻፈውን መደበቅ ወይም የሐሰት ኑዛዜ ማዘጋጀት።

​2. በኑዛዜ አማካኝነት ከውርስ መንቀል

ሀ/ ​አውራሹ (ንብረት ባለቤቱ) በሕይወት እያለ በሚያደርገው ኑዛዜ አንድን ወራሽ ለይቶ "አይወርሰኝም" ብሎ ሊሰርዝ ይችላል። ይህ የሚሆነው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦

ለ/ ​በቂ ምክንያት ሲኖር፦ ወራሹ በአውራሹ ላይ ከባድ በደል (ለምሳሌ፡ ስድብ፣ ድብደባ ወይም ስም ማጥፋት) ካደረሰ።

ሐ/ ​የቤተሰብ ግዴታን አለመወጣት፦ ወራሹ ለሟቹ እርዳታ በሚያስፈልገው ጊዜ ድጋፍ ካላደረገ ወይም የግዴታውን ካልተወጣ።

መ/ ​ያለ በቂ ምክንያት መገለል፦ አውራሹ ያለምንም ምክንያት ወራሹን ከውርስ ሊነቅለው ይችላል፤ ነገር ግን በዚህ ጊዜ ወራሹ "የግዴታ ክፍል" (Legitimation) የሚባለውን የውርስ መብት ለመጠየቅ ሊከራከር ይችላል።

​3. ውርሱን በፈቃደኝነት መተው:- ​አንድ ወራሽ በራሱ ፍላጎት "ውርሱን አልፈልግም" ብሎ የመተው መብት አለው። ይህ የሚደረገው ውርሱ ከተከፈተ በኋላ ባሉት ወራት ውስጥ ለፍርድ ቤት ወይም ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ ነው።

​ማወቅ ያለበዎት ነገር፦
​ይቅርታ፦ አውራሹ ወራሹ የፈጸመውን ጥፋት ይቅር ማለቱን በግልጽ ካሳየ ወይም በጽሑፍ ካሰፈረ፣ የመገለል ሂደቱ ሊቀለበስ ይችላል።

​ዕዳ፦ አንድ ወራሽ ከውርስ ሲነቀል፣ ከውርሱ ጋር የሚመጣውን ዕዳ የመክፈል ግዴታም አብሮ ይነሳለታል።

እንኳን ለብርሐነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ።መልካም በአል!!
19/01/2026

እንኳን ለብርሐነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ።መልካም በአል!!

✨"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል"✨(ሉቃስ 2÷11)እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድ...
07/01/2026

✨"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል"✨
(ሉቃስ 2÷11)

እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነትና የበረከት እንዲሆንላችሁ እመኛለው ::
✨🎄መልካም በዓል🎄✨
ጠበቃ ሙሉዘር ገ/ህይወት

Address

Nifas Silk Lafto Lebu
Addis Ababa

Telephone

+251911588933

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሙሉዘር የህግ አማካሪና ጠበቃ/ lawyer muluzer posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share