ስለ ህግ ምን ያህል ያውቃሉ?

ስለ ህግ ምን ያህል ያውቃሉ? YOU don't necessarily have to be a law master just to have knowledge of law but this page will let y

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል ባላቸው ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀመረ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠...
25/08/2024

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል ባላቸው ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀመረ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ):-የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል ባላቸው ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀመረ።

ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር በመጣስ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ፡-
- በዮሀንስ ዳንኤል በርሄ፣
- በአማኑኤል መውጫ አብርሃ፣
- በናትናኤል ወንድወሰን ሹሜ፣
- በኤልያስ ድሪባ በዳኔ፣
- በይዲድያ ነጻነት አበበ እና
- በእሌኒ ክንፈ ተክለአብ በተባሉ ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር መዋል የቻሉት በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም ያሉ የበረራ ባለሙያዎችን በማስገደድ በረራውን ለማስቀጠል በፈጠሩት አምባጓሮና ግርግር ወንጀል ተጠርጥረው እንደሆነ የወንጀል ምርመራ ቡድኑ ገልጿል።

የፖሊስ የምርመራ ቡድኑ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ከተመሠረተባቸው የወንጀል ክስ በተጨማሪ ከፀረ-ሰላም ኃይሎች ተልዕኮ ተቀብለው የተንቀሳቀሱ በመሆናቸው በሽብር ወንጀልም መጠርጠራቸውን ጨምሮ ገልጿል።

በወቅቱ የአየር መንገዱ የደህንነት ኃይሎችና የበረራ ባለሙያዎች በትዕግስት ሁኔታውን ለማርገብ ቢማጸኗቸውም፣ ድብቅ አጀንዳቸውን እያራመዱ አሻፈረን ማለታቸውንም በወንጀል ምርመራ መዝገቡ ተካቷል።

በቁጥጥር ሥር የዋሉት ተጠርጣሪዎች የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ የበረራ ሕግና አሰራርን በመጣሳቸው እንዲሁም በተጠረጠሩበት የሽብር ወንጀል በነገው ዕለት ነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ፍርድ ቤት ፖሊስ እንደሚያቀርባቸው ታወቋል።

ፍትሕበአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ የተገደለችው የ7 ዓመቷ ህጻን ሔቨን ታሪክ የበርካቶችን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሆኗል።ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዛሬ   በፊት በባህርዳር ከተማ እንደሆነ ዛሬም ድረስ መ...
18/08/2024

ፍትሕ

በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ የተገደለችው የ7 ዓመቷ ህጻን ሔቨን ታሪክ የበርካቶችን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሆኗል።

ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዛሬ በፊት በባህርዳር ከተማ እንደሆነ ዛሬም ድረስ መሪር ሀዘን ውስጥ የምትገኘው እናት " ኢዮሃ " በተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርባ ተናግራለች።

ሕጻን ሔቨን የተደፈረችው ተከራይተው ይኖሩበት በነበረ ግቢ አከራይ ነው።

የተደፈረችበት መንገድም ወደ ሽንት ቤት በምትሔድበት ጊዜ ጠብቆ ወደ ቤት በማስገባት ነው። እጅግ በጣም አሰቃቂም ነበር።

ህጻን ሔቨንን የደፈረው ወንጀለኛ በምትደፈርበት ወቅት አንገቷን አንቆ ፤ አፏን አፍኖ ድርጊቱን የፈጸመ ሲሆን ወድቃ የሞተች ለማስመሰል ደሟን አንጠባጥቦ በር ላይ ጥሏት መሄዱን እናት ታስረዳለች።

እናት ልጇን ብቻ አይደለም ያጣችው ፤ ፍትህ ስትጠይቅ ይህንን ግፍ ሰምተው እንዳልሰማ የሆኑ ጎረቤት እና ቤተሰቦች ፤ በጥቅም ወንጀለኛውን ነጻ ለማስወጣት የሰሩ ፤ እናትን ጭምር ተባብረው ለማጥፋት ረጅም ርቀት የተጓዙ ፤ ማስፈራሪያ ደርሷቸው ቃላቸውን ከመስጠት የጠፉ ሁሉ ለእናት ፈተና ሆነውባታል።

ይህም ሆኖ ጥቂት የሚባሉ አንዳንዶቹ ማስፈራሪያ ጭምር እየደረሳቸው አግዘዋት ከብዙ መከራ በኋላ ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ይፈረድበታል።

ሥራ እየሰራች መኖር አልቻለችም።

ነገ ከእስር ሲለቀቅ እሷንም ጭምር ለመግደል እንደሚፈልግ ፤ ለዚህም ደግሞ ዳግም ሥራ ከጀመረችበት ቦታ ቤተሰቦቹ ተከታትለዋት ጥላ መውጣቷን እናት አስረድታለች።

በመሰረቱ በዚህች ምስኪን አንድ ፍሬ ፤ ክፉ ደግ በማታውቅ ህጻን ላይ አሰቃቂ የመድፈር እና ኃሏም ህይወቷን ያሳጣ የወንጀል ድርጊት የፈጸመ ሰው እንዴት 25 ዓመት ይፈረድበታል ? እውነት ይህ ማስተማሪያ ነው ?

የሔቨን ታሪክ የብዙ ህጻናት ታሪክ ጭምር ነው።

27/06/2024

፨ የመንደር ውሎች በሕግ ፊት ተቀባይነታቸው ምን ያህል ነው? ውል የሚጸናው ምን ሲሟላ ነው ?

አራት ነገር ካልተሟላ ውል አይጸናም ።

1ኛ• ፈቃድ (Consent) ነው። ተዋዋዩ ፈቃዱን የሰጠው ወዶና ፈቅዶ በማያሻማ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል። ምን ማለት ነው ይሄ፣ በመታለል/በማታለል የተፈጸመ ውል ዋጋ አይሰጠውም።

2ኛ• ተዋዋዮቹ በሕግ 'ችሎታ ያላቸው' መሆን አለባቸው። 'ችሎታ' የሕግ ትርጉሙ ሁለት ነው። የተዋዋዮች ዕድሜ ከ18 ዓመት በላይ መሆን እና የአእምሮ ጤና ነው።

3ኛ• የውሉ ዋና ጉዳይ በሕግ የሚፈጸም መሆን አለበት። ለምሳሌ ባዶ መሬት መሸጥ አይቻልም። ስለዚህ የባዶ መሬት ሽያጭ ውል ቢደረግም በፍርድ ቤት ውድቅ ነው።

4ኛ• የውል አቀራረጽ ወይም ፎርም ነው። ይህም ማለት ለምሳሌ ለማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሸጥ 2 ምስክሮች መኖራቸው፣ በውል አዋዋይ ፊት መረጋገጥ፣ ሕጉ ያስቀመጣቸው ዝርዝሮች ሟሟላት።

፨ የመንደር ውል ሕጋዊ ነው ?

የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች፣ ማለትም ቤትና መሬት በርካታ ሰዎች በመንደር ውል የሚሻሻጡ ቢሆንም በርካታ ሰዎች ተግባሩን ስላደረጉት ግን ሕጋዊ አያሰኘውም። ይህ የመንደር ውል በሕግ ተቀባይነት የማይኖረው የሰነድ ማረጋገጥ ዋና ዓላማን የሚጥስ መሆኑ ነው ።

፨ ሰነድ ለምን ይረጋገጣል? ባይረጋገጥስ ምን ችግር አለው ?

አንደኛ በተዋዋዮቹ መካከል ያለውን ግንኙነት ለመግዛት ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሦስተኛ ወገን ለሚያነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ነው። ሦስተኛ ወገን የሚባሉት እነማን ናቸው ያልን እንደሁ፣ ከገዥና ሻጭ ውጪ ያሉ የትኛውንም ወገኖችን ያካትታል። ለምሳሌ የመንግሥት አካል፣ የክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር፣ ባንክ፣ ለምሳሌ ሽያጩ ይፍረስልኝ የምትል/የሚል ሚስት/ባል . . . ወዘተ እነዚህ ሁሉ 3ኛ ወገን ይባላሉ።

ከእነዚህ አካላት አንዱ፣ እንበልና በመንደር ውል በተፈጸመ ንብረት ላይ ጥያቄ ቢያነሱ ሙግቱን ያለምንም እሰጥ አገባ አሸነፉ ማለት ነው። በመንደር ውል ቤት የገዛ ሰው ቀለጠ ማለት ነው። በአጭሩ ውል የሚረጋገጥበት ዋንኛ ዓላማ ሦስተኛ ወገኖች ለሚያነሱት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ነው። "የመንደር ውል ችግሩም ይሄ ነው።

እርግጥ ውል በሰነዶች ሲረጋገጥ መንግሥት ቴምብር ያሳርፍበታል። ገቢ ያገኛል። ገዥና ሻጭ ሰነዱን ይዘው ክፍለ ከተማ ሲሄዱ የመንግሥት አካል ቀረጥ ይጥላል። ከዚያም ገቢ ይገኛል። ተዋዋዮች ሕጋዊ ሰነድ ይዘው ስለቀረቡ፣ ሕጋዊ አገልግሎት አግኝተው የስም ማዞርያ አሹራ ይከፍላሉ። ይህም ሌላ ገቢ ነው። ለዚህም ነው ውሉ በሕጉ ላይ የተቀመጠውን ፎርም ስላሟላ እንደ ሕጋዊ ውል ተቆጥሮ ተፈጻሚነት የሚኖረው።

፨ ተፈጻሚነት ይኖረዋል ማለት ግን ምን ማለት ነው ?

በአጭሩ ለምሳሌ ሻጭ ለገዢ ስም አላዞርልህም ቢል ፍርድ ቤት ከሶ በግዴታ ስም እንዲያዞር፣ ገዥ ላይ ለደረሰው ኪሳራም ካሳ እንዲያገኝ ይሆናል ማለት ነው። ይህን ዕድል ግን በመንደር ውሎች ላይ ለማሳካት አስቸጋሪ ይሆናል።

፨ በመንደር ውል የተሸጠ ንብረት እጣ ፈንታው ምንድነው ?

በፍርድ ቤት ቀርቦ ያልተመዘገበ ውል፣ ወይም በውል አዋዋዮች ፊት ያልተረጋገጠ የመንደር ውል እንደ ሕጋዊ ተቆጥሮ አፈጻጸም ሊቀርብበት አይችልም። በዚህ ላይ ምንም ብዥታ መኖር የለበትም። የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል በጽሑፍ መሆን አለበት፣ በሁለት ምስክሮች ፊት መሆን አለበት። በአዋዋይ ፊት መሆን አለበት።

ዋንስቶፕ የአንድ ማዕከል ኢንቨስትመንት አገልግሎቶቻችን በኢንቨስትመንት አማካሪነት፣ በጉምሩክ ማስተላለፍ፣ በግንባታ ንድፍ እንዲሁም ከባለብዙ ዲሲፕሊን ቡድኖቻችን ጋር በመተባበር የኢቨንት አደ...
07/09/2023

ዋንስቶፕ የአንድ ማዕከል ኢንቨስትመንት አገልግሎቶቻችን በኢንቨስትመንት አማካሪነት፣ በጉምሩክ ማስተላለፍ፣ በግንባታ ንድፍ እንዲሁም ከባለብዙ ዲሲፕሊን ቡድኖቻችን ጋር በመተባበር የኢቨንት አደረጃጀትና ሂሳብ (ኦዲቲንግ) አገልግሎት በመስጠት በሚገባ የተደራጀ አገልግሎት ሰጪ ኢትዮጵያዊ ድርጅት ነው።
ኩባንያችን ላለፉት ዓመታት በአብዛኛው ለቻይና ባለሀብቶች አገልግሎቱን ሲሰጥ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በማስፋት እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሮጀክት (ኢንቨስት) ለማድረግና እቅድ ላላቸውና ለሁሉም ባለሀብቶችና የንግድ ሰዎች ማስተናገድ ችሏል።
You can directly contact me on inbox

ስለ ኮንስትራክሽን ህግ በጥቂቱ....
05/05/2023

ስለ ኮንስትራክሽን ህግ በጥቂቱ....

ስለ ኮንስትራክሽን በጥቂቱ....
05/05/2023

ስለ ኮንስትራክሽን በጥቂቱ....

04/05/2023

በዚህ ገፅ ላይ ህግን በሚመለከት ማንኛውም ጥያቄ ቢኖርዎት በውስጥ መስመር መልዕክት በማስቀመጥ ፡ የህግ ምክር እንዲሁም የፅህፈት አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
አመሰግናለሁ !

25/05/2021

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ስለ ህግ ምን ያህል ያውቃሉ? posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share