Yonas Misganaw Law Office

Yonas Misganaw Law Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Yonas Misganaw Law Office, Lawyer & Law Firm, Addis Ababa.

08/02/2026

የአለም ጤና ድርጅትን 20 በመቶ በጀት የምትሸፍነዋ አሜሪካ ከድርጅቱ ነቅላ ወጥታለች። ሰንደቋም ከጀኔቫ ወርዷል።
አንድ አሜሪካዊ ሰው ሲናገር የሰማውት ነገር ያስገርማል። እንደሱ አባባል ከሆነ በአለም ጤና ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራ ከፍተኛ የጤና ባለሙያ እና አሜሪካን አገር ውስጥ በጤናው ዘርፍ ተቀጥሮ የሚሰራ ተመሳሳይ ባለሙያ (ሲቪል ሰርቫንት) መካከል ከፍተኛ ልዩነት አለ።
ለምሳሌ
1. በአለም ጤና ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራ ከፍተኛ ባለሙያ በአመት በአማካኝ የተጣራ 100 ሺ ዶላር ይከፈለዋል። አሜሪካን አገር ውስጥ ከፍተኛ የጤና ባለሙያ (ሲቪል ሰርቫንት) አመታዊ አማካኝ የተጣራ ደሞዙ 85 ሺ ዶላር ነው።
2. የአለም ጤና ድርጅት ሰራተኞች አብዛኞቹ ከደሞዛቸው ላይ ታክስ አይከፍሉም። 🤔
3. የአለም ጤና ድርጅት ሰራተኞች የልጆቻቸው የትምህርት ቤት ከፍያ በድርጅቱ ይሸፈናል። (በአመት በአማካኝ 20,000 ዶላር ይከፈላቸዋል)
4. የአለም ጤና ድርጅት ሰራተኞች ሌሎች ጥቅማጥቅሞችም አሏቸው።
የአለም ጤና ድርጅት እና መሰል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተቋማት ከትራምፕ ወደ ስልጣን መምጣት በሗላ ከፍተኛ የበጀት እጥረት እየገጠማቸው ነው። ተቋማቱ ከአባል አገራት በሚሰበሰብ መዋጮ በዋናነት ሰራተኞቻቸውን የተቀናጣ ኑሮ እያኖሩ ነው እንጅ ጠብ የሚል ስራ አይሰሩም የሚል ቅሬታ ይቀርብባቸዋል።
በእርግጥ በእኛ አገር ሳይቀር UN ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች የኑሮ ሁኔታቸው ከልክ ያለፈ ቅንጦት የተሞላበት ነው። በዚህ ምክንያት እኛ አገር NGO ሲባል ሰው አእምሮው ውስጥ የሚመጣው ከፍተኛ ደሞዝ ወይም የቅንጦት ህይወት ነው።
ይህ ግን ስህተት ነው። ሲጀመር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት NGO አይደለም።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሁን ደግሞ በትራምፕ የሰላም ቦርድ የመሰልቀጥ እድሉ እየሰፋ ይመስላል። የትራምፕ የሰላም ቦርድ ይህንን ድርጅት ጠቅልሎ ጡረታ ቢያስወጣው ጥሩ ነው።
Yonas MG

25/01/2026
11/01/2026

የጠበቆች ሒሳብ መዝገብ የመያዝ ጉዳይ የማይቀር እየሆነ ነው።

የፌዴራል ጠበቆች ማህበር የጠበቆችን ተቀናሽ የሚደረጉ ወጭዎች ዝርዝር በተመለከተ ጥናት እያደረገ መሆኑንና ለሚመለከተው አካል ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆኑን ጠበቃ Yonas Woldeyes ነገሮናል።
ነገርየው በጣም ጠቃሚ ነው በመሆኑም ሁሉም ጠበቃ የተዘጋጀውን መጠይቅ በደንብ ሞልቶ ለማህበሩ መላክ አለበት። መጠይቁን ለመሙላት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ።
https://forms.office.com/pages/responsepage.aspx?id=k2E77e7UKkuF-nNdwUfdFl1C72EucyRKi74IK3Lxoo1UMlZZR0E5SzhaOVM3Nk8zNUJXS0k4OUZFMC4u&fbclid=IwZXh0bgNhZW0CMTEAc3J0YwZhcHBfaWQPMjc1MjU0NjkyNTk4Mjc5AAEe9bhLyJTxx0dNCMViuAoFDV_OcflgWWNC0WmXU1yaM6D0IrQO2E8eG1QOLM4_aem_IEbvvytO3zmerGfIZxx-Bw&route=shorturl

ለምሳሌ የሚከተሉት ወጭዎች የግድ ተቀናሽ መደረግ ይገባቸዋል ብየ አስባለሁ።

1. የራይድ ትራንስፓርት፣ መኪና ያላቸው የነዳጅ እና ጥገና ወይም አዲስ መኪና (ኮድ 2 የሆኑትን ጨምር) ግዥ፣ኢንሹራንስ እና ተያያዥ ወጭዎች

2. የቢሮ ኪራይ፣ የቢሮ ፈርኒቸር፣ ስቴሽነሪ መሳሪያዎች፣ የቢሮ ፅዳት፣ ጥገና፣ ቢሮ ውስጥ የሚዘጋጁ ሻይ፣ቡና፣ ውሀ እና የመሳሰሉ ወጭዎች

3. ደረጃውን የጠበቀ ሙሉ ሱፉ ከነጫማው ቢያንስ በአመት ሁለት ጊዜ እና ከዚህ ጋር የተያያዙ የንፅህና መጠበቂያ ወጭዎች

4. ሙያውን ለማሳደግ የሚወስዳቸው የአገር ውስጥ ወይም የውጭ አገር ስልጠና፣ የቢዝነስ ስብሰባና መሰል ወጭዎች

5. ጠበቃው ከያዘው ጉዳይ ጋር በተያያዘ ማስረጃ ለማግኘት የሚያወጣቸው ወጭዎች። ለምሳሌ የልዩ ባለሙያዎች አስተያየት ወይም ምክር፣ የፓሊስ ሪፓርት፣ የህክምና ሪፓርት፣ የአስተዳደር ተቋማት ሪፓርት፣ የምስክሮች ትራንስፓርትና መሰል ወጭዎች፣ የሰነድ ማረጋገጥ ወጭዎች

6. ኮፒ፣ ፕሪንት፣ ትርጉም፣ ፀሀፊ ወዘተ

7. ኢንተርኔት፣ ስልክ እና ተያያዥ ወጭዎች

8. ሰራተኛ ወይም ጉዳይ አስፈፃሚ ካለው የእነሱ ደሞዝና ሌሎች ወጭዎች

9. ደረጃውን የጠበቀ ካባ ቢያንስ በአመት አንድ ጊዜ

10. ላፕቶፕ እና የስራ ስልክ ግዥ እና ጥገና

11. የሙያ ፈቃድ እድሳት፣ የሙያ ማህበራት የአባልነት ክፍያ ወጭዎች

12. የነፃ ጥብቅና አገልግሎት ወጭዎች ግምት

13. የሕግ ሶፍትዌሮች ግዥ ወይም ክፍያ ለምሳሌ የሌጋል ቴክ እና የመሳሰሉ ሰብስክሪብሽን ክፋያዎች። ለስራው የሚጠቅሙ የሚከፈልባቸው ዙም፣ቲም፣ወርድ እና የመሳሰሉ ወጭዎች

14. የቢዝነስ ካርድ ህትመት፣ ዌብሳይት ማበልፀግና ማስተዳደር ወጭዎች

15. ከደንበኛው ጋር በሚኖረው ቀጠሮ የሚያወጣቸው ከአልኮል ውጭ የሆኑ ሻይቡና፣ምሳ ወይም እራት እና ተያያዥ ወጭዎች (የራሱን የጠበቃውን ወጭ ላይጨምር ይችላል)

16. የባንክ አገልግሎት ክፍያዎች፣ ከስራው ጋር በተያያዘ ለተበደረው ብድር የሚከፈሉ የብድር ክፍያዎች ከነወለዳቸው።

17. ደረሰኝ ሊቀርብባቸው የማይችሉ ግን ማስረጃ ያላቸው ሌሎች ጥቃቅን ወጭዎች

18. ......

11/01/2026
23/04/2024

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከለጋሾች የሚያገኙት ገንዘብ የታክስ ሥርዓቱን ካልተከተለ ምርመራ እንደሚደረግበት፣ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን መመርያ ተዘጋጀ፡፡

23/02/2024

ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔር ከህወሓት አባልነታቸው ተሰናበቱ

| ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግራይ ጦርነት ወቅት በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት ከፍተኛ አመራሮቹ ውስጥ፤ ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔርን ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከፓርቲ አባልነታቸው ማሰናበቱን አስታወቀ።

በእስር ላይ ከነበሩ አመራሮች መካከል ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ እና ዶ/ር አብርሃ ተከስተ በፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ ውሳኔ አሳልፏል።

ህወሓት በከፍተኛ አመራሮቹ ላይ ይህን ውሳኔ ያሳለፈው፤ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ትላንት ሐሙስ የካቲት 15፤ 2016 ካደረገው ስብሰባ በኋላ መሆኑን ገልጿል። ህወሓት በጦርነቱ ወቅት “በጠላት እጅ ወድቀው ነበር” ያላቸውን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን በተመለከተ “ለረጅም ጊዜ ሲንጓተት” የቆየውን ያስተላለፈው ውሳኔ፤ የነበሩትን ሁኔታዎች በመገምገም እና የፓርቲውን ህገ ደንብ በመከተል መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።

በዚህም መሰረት “እጃቸውን ለጠላት በመስጠት” እና “ምስጢር አሳልፈው በመስጠት” የተገመገሙት የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም እና የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉ ገብረ እግዚብሔር፤ ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከፓርቲ አባልነታቸው “መባረራቸውን” ህወሓት አስታውቋል።

በትላንቱ ሰብሰባ “ከባድ ጸጸት” እንደተሰማቸው መግለጻቸው የተነገረላቸው ሁለቱ ተሰናባቾች፤ ወደፊት “በተሰማሩበት የስራ መስክ ህዝቡን ለመካስ እንደሚሰሩ” ቃል መግባታቸውን የፓርቲው መግለጫ ጠቅሷል።

ኬሪያ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር የዋሉት በትግራይ ክልል ጦርነት ከተቀሰቀሰ ከአንድ ወር በኋላ ነበር። የእርሳቸውን መያዝ በተመለከተ በወቅቱ መረጃውን ይፋ ያደረጉ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን፤ ኬሪያ በገዛ ፍቃዳቸው “ለመንግስት እጃቸውን መስጠታቸውን” መዘገባቸው ይታወሳል። በወቅቱ የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት ኬሪያ፤ “በመከላከያ ሰራዊ ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም” እና “በሀገር ክህደት ወንጀል” ተጠርጥረው የእስር መያዣ ትዕዛዝ ከወጣባቸው 96 ሰዎች መካከል አንዷ ነበሩ።

ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች አንዷ የነበሩት የፓርላማ አባሏ ሙሉ ገብረ እግዚያብሔር በቁጥጥር ስር የዋሉት ከኬሪያ መያዝ ከአንድ ወር በኋላ ነበር። ሁለቱ ተጠርጣሪዎች፤ 62 ግለሰቦች እና ድርጅቶች በተካተቱበት መዝገብ ክስ የተመሰረተባቸው በሐምሌ 2013 ዓ.ም. ነው። የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ተጠርጣሪዎቹን የከሰሰው፤ “በሕገ መንግስትና በሕገ መንግስት ስርዓት ላይ የሚደረግ ወንጀልን እንዲሁም የሽብርተኝነት ድርጊቶች” ፈጽመዋል በሚል ወንጀል ነበር።

በህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በተከፈተው በዚህ መዝገብ ከተካተቱ 52 ግለሰቦች ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋሉት 21 ተከሳሾች ብቻ ነበሩ። ከሃያ አንዱ ተከሳሾች መካከል ስድስቱ በታህሳስ 2014 ዓ.ም. ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር ተለቅቀዋል። የፍትሕ ሚኒስቴር “የጤና እና የዕድሜ ሁኔታቸውን ከግምት በማስገባት” ክሳቸው እንዲቋረጥ ማድረጉን በወቅቱ ካስታወቀላቸው ተከሳሾች መካከል ሙሉ ገብረ እግዚያብሔር ይገኙበታል።

የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት የሆኑት ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማን ጨምሮ ቀሪዎቹ የድርጅቱ አባላት፤ ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር የተለቀቁት በመጋቢት 2015 ዓ.ም. ነበር። የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በትላንትናው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ፤ ዶ/ር አብርሃም እና ዶ/ር አዲስ አለም በፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ መወሰኑን አስታውቋል።

እንደ እነርሱ ሁሉ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት፤ ዶ/ር ሰሎሞን ኪዳኔ፣ ዶ/ር ረዳኢ በርሄ፣ ወ/ሮ ኪሮስ ሃጎስ እና አቶ አጽብሃ አረጋዊም በተመሳሳይ ሁኔታ በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ ውሳኔ ማስተላለፉን ህወሓት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።

የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በትላንቱ ስብሰባው፤ ህወሓት በቀጣይነት ለሚያካሄደውን 14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ የሚሆኑ ሶስት አባላትን መርጧል።

በኮሚቴው አባልነት የተመረጡት ፈትለወርቅ ገብረእግዚያብሔር (ሞንጆሪኖ)፣ ወ/ሮ አልማዝ ገብረጻድቅ እና አቶ ኢሳያስ ታደሰን ነው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

Vacancy for fresh graduates (2014 & 2015 EC).
30/09/2023

Vacancy for fresh graduates (2014 & 2015 EC).

04/09/2023

የሰራተኞች ጥያቄ ምንድነው ? ከሰሞኑን ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር በነበረው ውይይት ምን ጥያቃ ተነሳ ምንስ ምላሽ ተሰጠ ?

(የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን - ፕሬዜዳንት ካሳሁን ፎሎ)

ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ ደሞዝ ተከፋዩ ሰራተኛ ችግር ላይ ነው ያለው። በተለይ ዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ የሆነው ሰራተኛ እጅግ የከፋ ችግር ውስጥ ይገኛል።

ለኑሮ ውድነቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከኮቪድ19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተፈጠረው የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ከሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ የታየው የዋጋ ንረት፣ የነዳጅ ዋጋ መጨመር ምክንያቶች ሲሆኑ #ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ በተለያዩ ቦታዎች የሚደረጉ ጦርነቶች እና ግጭቶች ለኑሮ ውድነት አስተዋፅኦ አድርገዋል።

የኑሮ ውድነቱን ለማቅለል እየተጠየቀ ያለው ጥያቄ ፦

- ሰራተኛው በጣም ችግር ላይ ስለሆነ የስራ ግብር ይቀነስ።

- ዝቅተኛ ደመወዝ የሚከፈላቸው ጭራሽ መኖር ወደማይችሉበት ደረጃ ላይ ስለደረሱ የገበያው ሁኔታ ታይቶ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ይወሰን።

- ለሁለት ዓመት የተቋረጠው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አማካሪ ቦርድ ተመልሶ እንደገና ስራ እንዲጀምር። ይህ ቦርድ ከመንግሥት 5 ከሠራተኛ 5 ፣ ከአሰሪ 5 የሚሳተፉበት የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ አፈፃፀምን እየተከታተለ አቅጣጫ የሚሰጥ ችግር ሲኖርም የሚፈታ ነው። ይህ ቦርድ ስራው በመቋረጡ የሠራተኞችን ጉዳይ ተጠያቂ የሚደረግበት ቦታ አልነበረም።

- 20/80 ተግባራዊ አልሆነም ተግባራዊ ይደረግ። ይህ ስራ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ለሚቀጥሩት ሰራተኛ ይከፍላሉ ተብሎ የወጣ መመሪያ ነው። መመሪያው የሚለው ለሰራተኛው 80% ለአስተዳደራዊ ወጪ 20% ይውሰድ የሚልነው።

- በነፃ የመደራጀት እና የመደራደር መብት ይከበር። ሰራተኞች ለመደራጀት ሲሞክሩ / ሲደራጁ በአሰሪዎቻቸው እርምጃ ይወሰድባቸዋል ፣ እርምጃዎቹ ከቦታ ቦታ ማዘዋወር፣ ከድራ ዝቅ የማደረግ፣ ከስራ ማባረር ይጨምራሉ። ስለዚህ ህግ በሚፈቅደው የመደራጀት እና የመደራደር መብታቸው ይጠበቅ ይህጉ ይፈፀመ።

- በሀገሪቱ ባለው የፀጥታ ሁኔታ ሰራተኞች ላይም ጉዳት እያመጣ አንዳንድ ቦታዎች ሰራተኞች እንደሚታገቱ፣ እንደሚገደሉ፣ ስለሚታወቅ ያ ጉዳይ ተነስቶ መፍትሄ እንዲሰጥ ተጠይቋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምንድነው ?

በውይይቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዝቅተኛ ደመወዝ ወለል፣ ስራ ግብር ቅነሳ፣ ከአማካሪ ቦርድ ጋር በተያያዘ ሌሎችም ለተነሱ ጥያቄዎች ለሚመለከታቸው አካላት አቅጣጫ ሰጥተዋል።

" ጥያቄዎቹ ትክክል አይደሉም " ፤ ወይም " አይፈፀሙም " የሚል ምላሽ አልተሰጠም። በጊዜ ሂደት ምላሽ እንደሚያገኙ ተገልጿል።

ምላሽ የሚሰጡት በጥናት ላይ ተመርኩዞ በመሆኑ ይታያል የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፤ አቅጣጫም አስቀምጠዋል።

ወዲያው መፈፀም ያለበት የአማካሪ ቦርድ መቀጠል ላይ ቅድመ ሁኔታ የማያስፈልገው ስለሆነ እሱ እንዲቀጥል ለሚመለከታቸው አካላት አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ሌሎችም ጥያቄዎች እንዲታዩ በሚል አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

(የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን - ፕሬዜዳንት ካሳሁን ፎሎ)

🙄😭🤔
03/09/2023

🙄😭🤔

01/09/2023

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 13:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yonas Misganaw Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yonas Misganaw Law Office:

Share