Habtamu Tilahun Legal Office

Habtamu Tilahun Legal Office Law, Ethiopian law, Ethiopian tax law, Ethiopian customs law, Business law, family law, succession, etc

05/02/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Marke Mathewos, Lij Beki

23/01/2026

የፍርደኞች ልውውጥ (Transfer of Sentenced Persons) እና አሳልፎ መስጠት (Extradition): ልዩነታቸውና አንድነታቸው በአጭሩ
====================
By Jura Legal Update
ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፥ ኢትዮጵያ
====================
የፍርደኞች ልውውጥ እና አሳልፎ መስጠት ተመሳሳይ ቢመስሉም፣ ዓላማቸውና የሚከናወኑበት መንገድ ግን መሠረታዊ ልዩነት አላቸው።

የፍርደኞች ልውውጥ በዋናነት ሰብዓዊነትን መሠረት ያደረገ ነው። ሂደቱም ጥፋተኛ ተብሎ ተፈርዶበት ቅጣት ላይ ባለ ግለሰብ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን ነው። ገና በክስ ሂደት ላይ ያለ ወይም ያልተፈረደበት ሰው በዚህ የሕግ ማዕቀፍ አይካተትም።

​ዓላማው እስረኞች ከባዕድ ሀገር ቋንቋ፣ ባህልና ማኅበራዊ ሁኔታ ወጥተው፣ ቀሪ ቅጣታቸውን በሀገራቸውና በቤተሰቦቻቸው አቅራቢያ እንዲጨርሱ ማድረግ ነው። ይህም ታራሚው ከእስር ሲወጣ ወደ ማኅበረሰቡ በቀላሉ እንዲቀላቀል ይረዳል።

የፍርደኞች ልውውጥ ሂደት ​በአብዛኛው ፈቃደኝነት ላይ መሰረት ያደረገ ነው። እስረኛው ወደ ሀገሩ ለመመለስ ፈቃደኛ መሆን አለበት። እንዲሁም ሁለቱም ሀገራት (ፍርድ የሰጠውና እስረኛውን የሚቀበለው ሀገር) መስማማት ይኖርባቸዋል።

​የቅጣት አፈጻጸምን በተመለከተ ግለሰቡ ወደ ሀገሩ ከተመለሰ በኋላ በባዕድ ሀገር የተፈረደበትን ቅጣት በሀገሩ ይፈጽማል።

በአንጻሩ፣ አሳልፎ መስጠት (Extradition) ደግሞ የሕግ የበላይነትን ለማስከበርና ወንጀለኞች እንዳያመልጡ ለማድረግ የሚከናወን ነው። ​የግለሰቡ ሁኔታ ወንጀል ፈጽሞ የተከሰሰ (የሚፈለግ) ወይም ተፈርዶበት ከሀገር የሸሸ ሊሆን ይችላል።

​ዓላማው አንድ ግለሰብ ወንጀል ፈጽሞ ወደ ሌላ ሀገር በመሸሽ ከሕግ እንዳያመልጥ ማድረግ ነው። ግለሰቡ ተላልፎ የሚሰጠው ወንጀሉ ወደተፈጸመበት ወይም ክስ ወደተመሠረተበት ሀገር እንዲቀርብ ነው።

በዚህ ሂደት የግለሰቡ ፈቃድ አይጠየቅም። ሂደቱ የሚከናወነው በሁለቱ ሀገራት የሕግ አስከባሪ አካላት (በፖሊስና በፍትሕ አካላት) አማካኝነት በግዳጅ ነው።

ግለሰቡ ተላልፎ የሚሰጠው ገና ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ወይም በዚያው ሀገር ቅጣቱን እንዲፈጽም ነው።

በቀላል አገላለጽ፣ የፍርደኞች ልውውጥ የተፈረደበት ሰው ቅጣቱን በሀገሩ እንዲጨርስ የማድረግ ዓላማ ያለው ሲሆን አሳልፎ መስጠት ደግሞ የሸሸ ወንጀለኛ ተይዞ ለፍርድ እንዲቀርብ የማድረግ የሕግ ማስከበር ሂደት ነው።

የፍርደኞች ልውውጥ በዋናነት ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ እና እስረኛው ወደ ማኅበረሰቡ በቀላሉ እንዲቀላቀል የሚደረግ ሲሆን፤ አሳልፎ መስጠት ደግሞ ወንጀለኞች ከአንድ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር በመሸሽ ከሕግ እንዳያመልጡ (Impunity) ለማድረግ የሚከናወን የሕግ ማስከበሪያ መንገድ ነው።

​ለምሳሌ፦ ​በቻይና ፍርድ ተፈርዶባት በእስር ላይ የሚገኝ ግለሰብ፣ የሚመጣው በፍርደኞች ልውውጥ ስምምነት ነው።​ነገር ግን አንድ ግለሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ ወደ ቻይና ቢሸሽ፣ ኢትዮጵያ ግለሰቡን የምትጠይቀው በአሳልፎ የመስጠት (Extradition) ሕግ ይሆናል።

አንድነታቸውን በተመለከተ ሁለቱም ሂደቶች እንዲከናወኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል የጸደቀ የሕግ ስምምነት ወይም አዋጅ መኖር አለበት። ሁለቱም ሂደቶች የሀገራቱን ሉዓላዊነት እና የሕግ ሥርዓት ማክበርን ይጠይቃሉ። በሁለቱም ሁኔታዎች፣ ግለሰቡ የፈጸመው ድርጊት በሁለቱም ሀገራት ሕግ ዘንድ "ወንጀል" ተብሎ የተደነገገ መሆን አለበት።

መልካም ቀን!

23/01/2026
23/01/2026
23/01/2026

📝 የጋብቻ ውል አልተመዘገበም ማለት ፈረሰ ማለት አይደለም!
ብዙዎቻችን የጋብቻ ውል (Pre-nuptial Agreement) በሰነዶች ማረጋገጫ ካልተመዘገበ በስተቀር ህጋዊ ውጤት የለውም ብለን እናስባለን። ነገር ግን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 225731 ላይ አስገራሚና ግልጽ የሆነ ትርጉም ሰጥቶበታል።

ቁልፍ ነጥቦች፡

✅ ዋናው መስፈርት ምንድን ነው? በህጉ መሰረት የጋብቻ ውል "አስገዳጅ" የሚሆነው በፅሁፍ ሆኖ በአራት ምስክሮች ሲረጋገጥ ብቻ ነው። ውሉ በመንግስት ተቋም ዘንድ (ለምሳሌ ውልና ማስረጃ) አለመመዝገቡ ብቻውን ውሉን ዋጋ ቢስ አያደርገውም።

✅ የመመዝገቡ ጥቅም ለማን ነው? የውሉ ቅጂ በመንግስት መሥሪያ ቤት እንዲቀመጥ የተፈለገው ለ3ኛ ወገኖች (ለምሳሌ ለተጋቢዎቹ አበዳሪዎች) ጥበቃ ለመስጠት ነው። ውሉ ካልተመዘገበ በ3ኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሊሆን አይችልም፤ በተጋቢዎቹ መካከል ግን የፀና ነው።

✅ መቼ ነው ውጤት የሚኖረው? ተጋቢዎቹ "ውል አልፈረምንም" ብለው ካልካዱ ወይም ውሉ መኖሩን ካልካዱ ድረስ፣ ውሉ በመንግስት ዘንድ ባይመዘገብም በመካከላቸው እንደ ህግ ሆኖ ያገለግላል።

✅ የቤተሰብ ህጉ አላማ፡ የጋብቻ ውል በተለይ ከጋብቻ በፊት የነበሩ የግል ንብረቶችን ለመለየት የሰዎችን እውነተኛ ፍላጎት የሚያሳይ በመሆኑ፣ ፍርድ ቤቶች ውሉን ከቤተሰብ ህጉ መሰረታዊ አላማ አንጻር በጥንቃቄ ሊመረምሩት ይገባል።

ባጭሩ፦ የጋብቻ ውል የፈረማችሁ ጥንዶች፣ ውሉ በሰነዶች ማረጋገጫ ስላልተመዘገበ ብቻ "እንደሌለ" አይቆጠርም። በመካከላችሁ መኖሩ እስካልተካደ ድረስ መብታችሁን ያስከብራላችኋል።

⚖️ ህግን ማወቅ ከብዙ ውዝግብ ያድናል!

23/01/2026

የፖሊስ የወንጀል ምርመራ እንደትና መቼ
(ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል)
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
 የወንጀል ምርመራ ማለት አንድ ወንጀል እንዴት እንደተፈጸመ እና ተጠያቂው ማን እንደሆነ ለመለየት መረጃዎችን የማፈላለግ፣ የመተንተን እና የማደራጀት ሂደት ነው። በልብ ወለድ ድርሰቶች ላይ የሚታዩ መርማሪዎች በጥቂት ብልህ ፍንጮች ብቻ ወንጀሎችን ሲፈቱ ቢታዩም፣ በተጨባጭ ዓለም ያለው ምርመራ ግን ውስብስብ፣ አድካሚ እና ሙሉ በሙሉ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ ነው።

➨የወንጀል ምርመራ ዋና ዓላማ ወንጀል ፈጻሚዎችን በመለየት፣ በቂ ህጋዊ ማስረጃዎችን በመሰብሰብ እና ለፍትህ በማቅረብ ስለተፈጸመው ወንጀል እውነታውን ማውጣት ነው። ይህም የግለሰቦችን መብት በማክበር እና በህግ አስከባሪ አካላት ላይ የህዝብ አመኔታን በመገንባት የሚከናወን ነው። ሂደቱ ወንጀል መፈጸሙን ማረጋገጥን፣ ማስረጃዎችን መሰብሰብና መተንተን፣ ተጠርጣሪዎችን መለየትና ያሉበትን ማወቅ፣ እንዲሁም ለክስ የሚሆን ጠንካራ መረጃ ማቅረብን ያካትታል። ይህም በመጨረሻ የወደፊት ወንጀሎችን ለመከላከልና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።
🔺የወንጀል ምርመራ መሠረታዊ መርሆዎች
የወንጀል ምርመራ ዋና መርሆዎች የወንጀል ቦታን የመጠበቅ፣ ማስረጃዎችን የመለየት፣ የመሰብሰብ፣ የመጠበቅ እና የማቅረብ ስልታዊ ሂደቶችን ያካትታሉ። ይህ ሂደት በግልጽ እውነታዎች ላይ የተመሠረተ (objectivity)፣ የተሟላ ሰነድ (በ 5ቱ "W" እና በ 1ዱ "H" ጥያቄዎች የታገዘ) እና ጥብቅ የማስረጃ ቅብብሎሽ ሰንሰለትን (chain of custody) የተከተለ መሆን አለበት። እንዲሁም ተጠርጣሪው ጥፋተኛ መሆኑ በፍርድ ቤት እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹህ የመቆጠር መብቱን እና ህጋዊ ሂደቶችን በማክበር፣ ወንጀለኛውን ለመለየት፣ ያሉበትን ለማወቅ እና ክስ ለመመስረት የሚከናወን ተግባር ነው።
መሠረታዊ መርሆዎች
1. ገለልተኝነት እና ተጨባጭነት (Objectivity & Neutrality): ምርመራው ያለ ምንም አድልዎ፣ በግምት ላይ ሳይሆን በእውነታዎች ላይ ብቻ የተመሠረተ መሆን አለበት።
2. ንጽህ ሆኖ የመገመት (Presumption of Innocence): ተጠርጣሪዎች ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹህ ይቆጠራሉ።
3. ጥንቃቄ እና ጥልቀት (Thoroughness): እያንዳንዱ ጥቃቅን ዝርዝር ነገር ዋጋ አለው፤ የወንጀል ቦታዎች እና ማስረጃዎች በጥንቃቄ መመዝገብ እና መመርመር አለባቸው።
ዋና ዋና የምርመራ ደረጃዎች (5ቱ ክፍሎች)
1. መለየት (Recognition): በወንጀል ቦታ ላይ ሊሆኑ የሚችሉ ማስረጃዎችን መለየት።
2. መሰብሰብ (Collection): ቁሳዊ እና የቃል ምስክርነት ማስረጃዎችን ማሰባሰብ።
3. ጥበቃ (Preservation): ማስረጃዎች እንዳይበከሉ ወይም እንዳይጠፉ መጠበቅ (ለምሳሌ የወንጀል ቦታውን በማጠር መጠበቅ)።
4. መገምገም (Evaluation): የተሰበሰቡ ማስረጃዎች ከጉዳዩ ጋር ያላቸውን ተያያዥነት መተንተን።
5. ማቅረብ (Presentation): ጉዳዩን ለዐቃቤ ሕግ ውጤታማ በሆነ መንገድ ማቅረብ።
ዋና ዋና ጽንሰ-ሀሳቦች እና መሣሪያዎች
 የሎካርድ ልውውጥ መርህ (Locard's Exchange Principle): ማንኛውም ንክኪ አሻራ ይተዋል (ለምሳሌ፦ ወንጀለኛው በቦታው ላይ የሆነ ነገር ይተዋል፣ ወይም የሆነ ነገር ይዞ ይሄዳል)።
አምስቱ "W" እና አንዱ "H":
1. ምን (What)፣
2. መቼ (When)፣
3. የት (Where)፣
4. ማን (Who)፣
5. ለምን (Why) እና
6. እንዴት (How) — እነዚህ ምርመራን ለመምራት የሚያገለግሉ ጥያቄዎች።
ሦስቱ 'I'ዎች:
1. መረጃ (Information): ከተለያዩ ምንጮች መረጃዎችን መሰብሰብ።
2. ምርመራ/ጥያቄ (Interrogation): ተጠርጣሪዎችን መጠየቅ።
3. የሳይንስ መሣሪያዎች/ፎረንሲክ (Instrumentation): ለትንተና ሳይንሳዊ መሣሪያዎችን መጠቀም (DNA፣ የጣት አሻራ)።
ጊዜ ጀምሮ ፍርድ ቤት እስኪቀርብ ድረስ ያለውን ጥንቃቄ የተሞላበት አያያዝ በሰነድ መመዝገብ።
የአንድ መርማሪ ብቃቶች
 ታማኝነት፣
 ቅንነት፣
 ጠንካራ የክትትል ክህሎት፣
 የሕግ እውቀት፣
 ሳይኮሎጂ እና የኮሙኒኬሽን ችሎታ።

ወንጀል ምርመራ ግቦች
ወንጀል መፈጸሙን ማረጋገጥ፣ ወንጀለኛውን መለየት፣ ማስረጃ ማሰባሰብ፣ የተዘረፉ ንብረቶችን ማስመለስ እና ለክስ የሚሆን ጠንካራ ፋይል ማደራጀት።

የፖሊስ የወንጀል ምርመራ ዓይነቶች
1. የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ማለት መርማሪው የስሜት ህዋሳቶችን ተጠቅም የወንጀሉን ድርጊት ለማጣራት የሚያደርገው ሂደት ማለት ነው ይኸውም መርማሪው አዕምሮውን በመጠቀም ተመርማሪው ወደ እውነቱ የሚመጣበትን መንገዶች በመከተል ይፈጽማል፡፡
2. የቴክኒክ ምርመራ በሌላ በኩል መርማሪው ከወንጀል ስፍራ ማስረጃዎችን በመሰብሰብ ሳይንስን በመጠቀም ማስረጃዎችን በላብራቶሪ ጭምር የመመርመር ስርዓት ነው፡፡
 ወንጀል ጉዳይ ሥራውን የሚጀምረው መርማሪው ምርመራውን ለመጀመር የሚያስችለው መረጃ ሲደርሰው ነው፡፡
 መረጃ ሰጪዎች ስለወንጀል መፈጸም የሚሰጡት፡-
1. በክስ (በወንጀል ህግ ስነ- ስርዓት አንቀፅ ቁጥር11)
2. በአቤቱታ (ወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት አንቀፅ13) ወይም
3. በእጅ ከፍንጅ ወንጀል ድርጊት (ስነ- ስርዓት ህግ ቁ.19-21) መልክ ነው፡፡

 በክስ አቀባበል ወቅት ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
1. ክስ አቅራቢው ሲመጣ ማረጋጋት
2. ጉዳዩ ወንጀልና ፍታብሄር መሆኑን መለየት
3. ከክሱ ጋር የቀረበ ማስረጃ መኖር አለመኖሩን ማወቅ
4. በክሱ ላይ የተጠርጣሪው ማንነት መታወቅ አለመታወቁን መረዳት
5. የተከሳሽ ያለበትን አድራሻና ሁኔታ ማወቅ /በህይወት መኖሩን፣ መሞቱን ፣ሀገር ውስጥ መኖሩን/
6. ክሱ በሌላ ፖሊስ ጣቢያ የቀረበ አለመሆኑን
7. የይርጋ ዘመን ያላለፈበት መሆኑን የወንጀሉ የተፈጸመበትን ጊዜና ቦታ መለየት
8. ተከሳሽ ወይም እግዚቢት መያዝ አለመያዙን
9. የተፈጸመው ድርጊት በማን መጣራት እንዳለበት

ለመርማሪ የሚያስፈልጉት ዕውቀትና ክህሎት
1. ጠቅላላ ዕውቀት
2. የህግ ዕውቀት
3. የመግባባት ክህሎት
4. የመጻፍ ክህሎት
5. የዕቅድ አወጣጥ
6. የማስታወስና
7. ውሳኔ አሰጣጥ
የወንጀል ስፍራ/crime scene/
 የወንጀል ስፍራ ማለት ወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመበትና ውጤት ያገኘበትን የጠቃልላል፡፡
 የወንጀል ስፍራ መታወቅ ያለው ጠቀሜታ፡-
1. ከወንጀሉ ድርጊት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ማስረጃዎች በቀላሉ ለማግኘት፣
2. የወንጀል ስፍራ ማወቅ የምስክሮችን ትክክለኝነት ለማወቅ
3. ምርመራው የሚጣራበትና ለፍርድ የሚቀርብበትን ቦታ ለማወቅ
4. ድርጊት ፈጻሚው ላይ ለመድረስ አቅጣጫ ያሳያል
የወንጀል ስፍራ ማስረጃዎች
 አንድ ሰው የትኛው የረገጣቸው ወይም የተንቀሳቀሰባቸው መንገዶች ፣ ማናቸውም የነካቸው ነገሮች ሳያስተውላቸው የሚተዋቸው ማናቸውም ነገሮች በእርሱ ላይ ዝምተኛ ምስክር ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው
 የጣት አሻራው ወይም የእግር/ጫማ ዱካው፣ ፀጉሩ፣ ከልብሱ የቀሩት ክሮች የሰበራቸው መስተዋቶች፣ የተዋቸው የቁሳቁስ ምልክቶች፤ የፋቃቸው ቀለማት፣ የፈሰሳቸው ወይም ይዞ የሄዳቸው ደም ወይም የአባላዘር ፈሳሾች ናቸው

የግል ተበዳይ ቃለ መጠይቅ
1. ሚስጥራዊነት መጠበቅ አለበት (Privacy )፡- ተጎጂን ወይም ምስክርን የሚናገሩትን ነገር ማንኛውም ሰው ሊሰማው በሚችል ቦታ ላይ ቃለ መጠይቅ ማድረግ ተገቢ አይደለም ፡፡
2. ደህንነት (Security ) ቃለ መጠይቅ በምናደርግበት ወቅት ማንኛውም የማይፈለግ ሰው በቦታው አለመኖሩን ወይም ገባ ወጣ የሚል ሰው አለመኖሩን ፣ ቃል ሰጭዎች ከማንኛም እይታ ውጭ መሆኑን እና ቃለመጠይቁ የሚደረግበት ቦታ ምቾት እንዲሰማው የሚያደርግ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ፡፡
3. አቀማመጥ ስርዓት ፡- በጣም ሳይርቅ ወይም በጣም ሳይቀርብ በተገቢዉ ርቀት ምቾት በማይነሳ መልኩ የግል ተበዳይ መቀመጥ አለበት፡፡እንድሁም በእኩል የአቀማመጥ ሁኔታ መቀመጥ የተሻለ ነዉ፡፡
4. የዓይን ግንኙነት ( Eye contact ) በአብዛኛው ባህል ቀጥታ የአንድ ሰው ዓይን ማየት እንደነውር ይቆጠራል ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ቀጥታ ዓይን ማየት ተቃውሞን ወይም መጋፈጥን ወይም ቁጣን ሊያመለክት ይችላል ፡፡ ስለዚህ ቀጥታ ዓይን ማየት የሚፈራን የሚያፍርን ቃል ሰጭን የተለያየ አቅጣጫ ማየት ጠቀሜታ አለው ፡፡
5. የምልክት ቋንቋ ( Body language ) እንደየማህበረሰቡ ባህልና አስተዳደር የተለያየ በመሆኑ ለግንዛቤ የሚያስቸግር ቢሆንም በቃለ መጠይቅ ወቅት የአንድን ሰው እንቅስቃሴ ፣ የሰውነት ቋንቋ ወይም የምልክት ቋንቋ የምንላቸውን በተገቢው መንገድ መረዳት ይጠቅማል
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251911973891

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Habtamu Tilahun Legal Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Habtamu Tilahun Legal Office:

Share

Category