ጠበቃ.com

ጠበቃ.com Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጠበቃ.com, Lawyer & Law Firm, Addis Ababa.

  ።የስር ፍርድ ቤትም አመልካች የቀረበባቸውን [የመጀመሪያ ደረጃ] የመቃወሚያ ክርክር ለመከላከል ወራሽነቴን በ1997 ዓ.ም አሳውጃለው በማለተ ያነሱትን ማስረጃና መከራከሪያ የማስረጃ አቀራረ...
15/11/2023





የስር ፍርድ ቤትም አመልካች የቀረበባቸውን [የመጀመሪያ ደረጃ] የመቃወሚያ ክርክር ለመከላከል ወራሽነቴን በ1997 ዓ.ም አሳውጃለው በማለተ ያነሱትን ማስረጃና መከራከሪያ የማስረጃ አቀራረብ ስርዓቱን የተከተለ አይደለም በማለት ሳይቀበለው ቀርቷል።

ይሁንና ከሳሽ የሆነ ወገን በክሱ ላይ ተከሳሽ የሚያቀርበውን የመጀመሪያ
ደረጃ መቃወሚያ አስቀድሞ ገምቶ ለዚህ የሚረዳውን [ክርክርና] ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ እንዲያቀርብ አይጠበቅም፡፡

ከላይ ከጠቀስነው የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 245 ድንጋጌ መገንዘብ እንደሚቻለው መቃወሚያ ሲቀርብ ፍርድ ቤቱ ሌላው ተከራካሪ ወገን በመቃወሚያው ላይ የሚያቀርበውን ክርክር ከሰማ በኋላ መቃወሚያውን ለመወሰን ተገቢ መስሎ የሚገምተው ማስረጃ እንዲቀርብለት ትዕዛዝ እንደሚሰጥና በመጨረሻም የቀረበው መቃወሚያ ከማስረጃው አንፃር መርምሮ ተገቢው ብይን መስጠት ይኖርበታል።

ስለሆነም አመልካች ላቀረቡት ክስ ከተጠሪዎች የቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ተመልክተው መቃወሚያውን ውድቅ ለማስደረግ የበኩላቸውን ክርክር በማቅረብ ክርክራቸውንም በማስረጃ ለማስደገፍ ያቀረቡት ጥያቄ የስር ፍርድ ቤት የማስረጃ አቀራረብ ስርዓቱን የተከተለ አይደለም በማለት
ማስረጃውን ተቀብል ከቀረበው መቃወሚያና ከክሱ ይዘት አንጻር ሳይመረምር ብይን መስጠቱ ህጉን የተከተለ ሆኖ አላገኘነውም፡፡ የበላይ ፍርድ ቤቶችም ይህን ሳያርሙ ማለፋቸው የሚነቀፍ ነው፡፡

      የፌዳራል ህገ መንግስት አንቀጽ  #37 ፤ ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.  #91፤  #137(1) ፣  #223፣  #256"ከሳሽ ወገን ክስ በሚሰማበት ወቅት ያላቀረበው ማስረጃ መኖሩን በበቂ ም...
15/05/2023





የፌዳራል ህገ መንግስት አንቀጽ #37 ፤ ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. #91፤ #137(1) ፣ #223፣ #256

"ከሳሽ ወገን ክስ በሚሰማበት ወቅት ያላቀረበው ማስረጃ መኖሩን በበቂ ምክንያት በማስደገፍ ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት ባገኘበት ሁኔታ ተከሳሽ የመከላከያ መልሱን እንዲያሻሽል የሚያቀርበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ በተሟላ መልስ ባልተከራከረበት ሁኔታ ተከሳሽ ከሳሽ ባቀረበው ሰነድ ላይ አስተያየቱን በጽሁፍ ብቻ ያቅርብ ብሎ የመደመጥ መብቱ ሊታለፍ አይገባም።"

የፌዳራል ህገ መንግስት አንቀጽ #37 ፤ ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. #91፤ #137(1) ፣ #223፣ #256 ".....

         #የወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 130 እና 131‘’በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 130 ንዑስ አንቀጽ 2 የተዘረዘሩት የወንጀል ክስ መቃወሚያዎች አመላካች (indicative ...
02/04/2023





#የወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 130 እና 131

‘’በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 130 ንዑስ አንቀጽ 2 የተዘረዘሩት የወንጀል ክስ መቃወሚያዎች አመላካች (indicative provision) እንጅ ሁሉንም በመቃወሚያነት ሊቀርቡ የሚችሉ ጉዳዮችን በሙሉ የሚዘረዝር (exhaustive provision) ድንጋጌ አይደለም፡፡’’

አንድ የወንጀል ክስ የቀረበበት ተከሳሽ ከሱ ደርሶት ከተነበበለት በዃላ መጀመሪያ የሚጠየቀው ክሱን ይቃወም እንደሆነ ነዉ። ክሱን እቃወማለዉ ለሚል ተከሳሽ ምክንያት የሚሆኑ ጉደሸዮች በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 130 ሰር ተዘርዝረዋል።

ይህም ሆኖ ግን አንድ ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ወይም የክስ ማመልከቻውን ለመቃወም የሚችለው በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 130 ሰር በተመለከቱት ጉዳዮች ብቻ ነው ተበሎ ሊገደብ አይገባም ሲል ይህ የሰበር ችሎት ወሳኔ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል።

የሰበር ችሎቱ ሙሉ ወሳኔ ኮፒን ከሊንኩ ላይ ማዉረድ ይቻላል።

       #244   #33(1 እና 2)  #231(1/ሀ)ተከሳሽ የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 33(2) እና 231(1) መሰረት ያደረገ የመ/ያ ደረጃ መቃወሚያ ሲያቀርብ ብዙ ግዜ ከሳሽ የሆነዉ ወገን “...
02/04/2023




#244 #33(1 እና 2) #231(1/ሀ)

ተከሳሽ የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 33(2) እና 231(1) መሰረት ያደረገ የመ/ያ ደረጃ መቃወሚያ ሲያቀርብ ብዙ ግዜ ከሳሽ የሆነዉ ወገን “መቃወሚያዉ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 244 መሰረት የሚቀርብና በቁ. 245 መሰረት ተመርምሮ ወሳኔ የሚሰጥበት አይደለም::” የሚል ክርክር ሲያቀርብ ይስተዋላል።

ለመሆኑ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 244 ስር ከተዘረዘሩት ወጪ ያሉ የሕግና የፍሬ ነገር ክርክሮች ላይ በመመስረት የሚቀርብ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እንዴት ሊስተናገድ ይገባል?

ለዚህ ጥያቄ በከፊል መልስ የሚሰጠን #በሰ/መ/ቁ_204199 (የታተመ ቅፅ 25)ነዉ። በዚህ መዝገብ የሰበር ችሎቱ በሰጠው ወሳኔ ላይ

“አንድ ሰዉ በሌላ ሰዉ ሊይ ክስ በማቅረብ በዳኝነት አካል ማስወሰን የሚችለው ክሱ በቀረበበት ሰዉ የተጣሰበት/ የተነካበት በሕግ ወይም በዉል እዉቅና እና/ወይም ጥበቃ ያገኘ መብት ወይም ጥቅም ሊኖረዉ ይገበሸል።(የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 33(2 እና 3) ይመለከቷል፡፡) ይሕንንም ከሳሽ በፍሬ ነገር ደረጃ በክስ አቤቱታዉ ሊይ ማሳየት(ማረጋገጥ) ይጠበቅበታል።

በፍሬ ነገር ደረጃ በክሱ ላይ የተገለፀውን በተመለከተ ሌላኛዉ ወገን ክስ በተመሰረተበት ነገር ሊይ ከሳሹ በሕግ እና/ወይም በዉል እዉቅና እና ጥበቃ ያገኘ መብት ወይም ጥቅም የለዉም እንዱሁም የሚያስከስሰኝን ተግባር አልፈጸምኩም ወይም በክሱ የተገለፀው ድርጊት የሚያስከስስ አይደለም በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በማቅረብ መቃወሚያ አቅርቦ እንዲቃወም ሳይጠብቅ ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤት በእራሱ ጊዜ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 33(2 እና 3) እና 231(1/ሀ) መሰረት የክስ አቤቱታዉን መርምሮ ተገቢዉን የመወሰን ኃላፊነት አለበት።

እንዱሁም ተከሳሹ ይህንን መከራከሪያ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 244/2 መሰረት በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ሥረ ነገሩን የሚመለከት ጭብጥ ከመመስረቱና በጭብጡ ላይ ማስረጃ ከመስማቱ እና ከመመርመሩ በፊት እነደነገሩ ሁኔታ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 245/1 መሰረት እንደ አስፈሊጊነቱ ዉሳኔ ለመስጠት ተገቢ ነዉ ያለዉን ማስረጃ አስቀርቦና መርመሮ ዉሳኔ መስጠት ይኖርበታል።”

ብሏል።

ሙሉ ወሳኔው በሚከተለዉ ሊንክ ላይ ይገኛል።

 #የቅጣት ገደብን የሚከለክሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በተመለከተ የሰበር ችሎት ውሳኔ #ሰ/መ/ቁ 185700 #የተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ማመን፣  #ከግል ተበዳይ ጋር ታርቆ መካስ፣ እና  #የፍርድ ...
20/01/2023

#የቅጣት ገደብን የሚከለክሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በተመለከተ የሰበር ችሎት ውሳኔ

#ሰ/መ/ቁ 185700

#የተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ማመን፣ #ከግል ተበዳይ ጋር ታርቆ መካስ፣ እና #የፍርድ ቤትን ወጪ ለመሸፈን ማረጋገጫ መስጠት የቅጣት ውሳኔን ለመገደብ የግድ መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታ አይደሉም።

01/12/2022

Justice must not only be done, but must be seen to be done.

19/11/2022

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠበቃ.com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ጠበቃ.com:

Share