Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ I am a Senior Attorney and legal advisor at all Federal and Oromia Courts, with over 15 years of experience.

I have an LLM Degree(Master of Laws) in Commercial and Investment Law and an LLB Degree from Mekelle University in 2007.

  በሆነ ኃላፉነት ለደረሰ ጉዳት እንዲከፈል የሚወሰን ካሳ በተቻለ መጠን ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል ሆኖ የሚመዛዘን መሆን ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2090/1 እና 2091ኢንሹራንስ...
13/08/2026

በሆነ ኃላፉነት ለደረሰ ጉዳት እንዲከፈል የሚወሰን ካሳ በተቻለ መጠን ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል ሆኖ የሚመዛዘን መሆን ያለበት ስለመሆኑ
የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2090/1 እና 2091

ኢንሹራንስ ሰጪዎች ቅሪት አካሉ እንዲሰጣቸው ወይም የቅሪት አካሉ ግምት ከካሳው ላይ እንዲቀነስ በሚል የሚያቀርቡት ክርክር ካሳው ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል መሆን አለበት በሚል መከራከሪያ ማእቀፍ ውስጥ ሊታይ የሚገባ እንጂ ዳኝነት ተከፍሎ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ መቅረብ አለበት የሚባል ክርክር ስላለመሆኑ
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 234 (1/ረ) ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 204256 በሆነው በቅፅ 27 ላይ የተሰጠ የሰበር ውሳኔ።

ፍርድ ቤቶች ግን አልሰማንም አላየንም እያሉ በዝምታ የሚያልፉት ነገር ይገርመኛል።

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

በ2003ዓም የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ሲጀመር ፕሮጀክቱ ተጠናቆ 5,150 ሜጋዋት ሀይል ማመንጨት ሲጀምር በአመት ከ1ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ያመጣል ተብሎ ነበር። አሁን ...
13/08/2026

በ2003ዓም የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ሲጀመር ፕሮጀክቱ ተጠናቆ 5,150 ሜጋዋት ሀይል ማመንጨት ሲጀምር በአመት ከ1ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ያመጣል ተብሎ ነበር። አሁን ደግሞ ይህ የባለውን 5,150 ሜጋ ዋት እያመረተ ቢገኝም ሌሎቹም በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ግድቦች ተጨምረው 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አላመጡም። ምክንያቱም አጠቃላይ የተገኘው ገቢ ብር 121 ቢሊየን ብር ገደማ ሲሆን ይህ ወደ ዶላር ሲቀየር ወደ 781 ሚሊዮን ዶላር ነው የሚሆነው። እንዲሁ ነው ሆዳችንን ያጮሁት!!

ነሐሴ 7 2018

በኢትዮጵያ እየተመረተ ካለው የኤሌክትሪክ ኃይል ግማሽ ያህሉ ከህዳሴ ግድብ መሆኑ ተነገረ።

በአሁኑ ወቅት የታላቁ ህዳሴ ግድብ በሙሉ አቅሙ ማለትም 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመረተ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነግሮናል፡፡

እየተጠናቀቀ ባለው የ2018 ዓመት እንደ ሀገር 38 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ውጥን ተይዞ 35 ሺህ 671 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል መመረቱንና፤ከተመረተው ግማሽ ያህሉ ማለትም 18 ሺህ 360 ጊጋ ዋት ሰዓት የተመረተው ከህዳሴ ግድብ መሆኑን የተቋሙ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል፡፡

ከአፍሪካ ግዙፉ የሀይል ማመንጫ የሆነው ግድቡ ኢትዮጵያ የምታመርተውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን የመጨመሩን ያክል ሃገሪቱ ለሽያጭ የምታቀርበውን የኃይል መጠንም ጨምሮታል የሚሉት አቶ ሞገስ፤
የኃይል ምርቱ ከአምናው በ23 በመቶ መጨመሩን ተከትሎ ከሃይል ሽያጭ የተገኘው ገቢም ከ75 ቢሊዮን ብር በ2018 ዓመት ወደ 121 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱንም አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የማምረት አቅሟ ከዓመት ዓመት እያደገ መምጣቱን የሚናገሩት አቶ ሞገስ፤ ለዚህ ትልቁን ድርሻ የሚይዘው የህዳሴ ግድብ ነው፤ስራው ተጠናቆ ሁሉም ዩኒቶች እየሰሩ መሆኑና ባለፈው ዓመት ግድቡ በቂ ውሃ በመያዙ በሙሉ አቅሙ ማምረት ችሏል ብለዋል።

ይህም የሃገሪቱን ኃይል የማመረት አቅም 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት አድርሶታል ብለውናል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.....
https://tinyurl.com/4337rxau

ምንታምር ፀጋው

12/08/2026
  ሳይሰጥ የሚወስደው እርምጃ ህገ ወጥ እና ካሳ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ በማለት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔ።   አካል ሳይፈቅድ የተያዘ ይዞታ ወደ ሕጋዊ ሥርዓትእንዲገባና ...
12/08/2026

ሳይሰጥ የሚወስደው እርምጃ ህገ ወጥ እና ካሳ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ በማለት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔ።

አካል ሳይፈቅድ የተያዘ ይዞታ ወደ ሕጋዊ ሥርዓትእንዲገባና በሊዝ ሥርዓት እንዲተዳደር ካልተደረገ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 26/4 በተደነገገዉ መሰረት አግባብ ያለዉ አካል የማስለቀቂያ ትእዛዝ መስጠትና ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ የ7 የሥራ ቀናት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ብቻ ይዞታዉን ለያዘዉ ሰዉ በአካል በመስጠት ወይም በቦታዉ በሠፈረዉ ንብረት ሊይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ሥልጣን ያለው ሲሆን በሕግ
የተጣለበትን ማስጠንቀቂያ የመስጠት ግዴታ ሳይወጣ መሬቱ በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዟል በሚል ብቻ በመሬቱ ላይ የሰፈረ ንብረት የሚያወድም ወይም በንብረቱ ላይ ጉዳት እንዲደርስበት የሚያደርግ ከሆነ በደረሰዉ ጉዳት ልክ ካሣ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 238091 በሆነው በቅፅ 27 ላይ የተሰጠ የሰበር ውሳኔ።



እና ኦሮሚያ ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ

የጥብቅና አገልግሎት ለምትፈልጉ በ #0910266507 ወይም በ #0906515217 ልታገኙኝ ትችላላችሁ፣ በአገልግሎታችን ትረካላችሁ።



Interesting scientific news
12/08/2026

Interesting scientific news

አንዲት እናት የመንታ ልጆቿን አባት ለማወቅ በዩኒቨርስቲ ኦፍ ኮሎምቢያ ወደሚገኘው የዲኤንኤ ምርመራ ማዕከል አመራች።

ማዕከሉ የተለመደውን ናሙና ወስዶ ከመረመረ በኋላ ባገኘው ውጤት ስለተገረመ በድጋሚ ምርመራ አደረገ። ውጤቱ ስላስገረማቸው እርግጠኛ መሆን ፈልገው ነበር።

መንትዮቹ ከአንድ እናት ቢወለዱም አባታቸው ግን የተለያየ ነበር።
https://bbc.in/3S8fLZV

  ንብረት ክፍፍል ጥያቄ ድርሻን  መሰረት በማድረግ የቀረበ ሲሆን አመልካቹ በድርሻው ተመስርቶ ዳኝነት እስከጠየቀ ድረስ ከድርሻው ውጪ ያለውን ግምት መሰረት አድርጎ ዳኝነት እንዲከፍል የሚደረ...
11/08/2026

ንብረት ክፍፍል ጥያቄ ድርሻን መሰረት በማድረግ የቀረበ
ሲሆን አመልካቹ በድርሻው ተመስርቶ ዳኝነት እስከጠየቀ ድረስ ከድርሻው
ውጪ ያለውን ግምት መሰረት አድርጎ ዳኝነት እንዲከፍል የሚደረግበት
የህግ አግባብ ስላለመኖሩ እና የውርስ ንብረቱ ጠቅላላ ግምት የፍርድ ቤቱን
የስረ ነገር ስልጣን ለመወሰን የግድ የሚባልበት የሕግ መሰረት የሌለ
ስለመሆኑና
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 17 እና 225 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 167589 በቅጽ 24 ላይ የተሰጠ የሰበር ውሳኔ።

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

  በቅርቡ በኢትዮ ቴሌኮም የቴሌኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በአስተዳደር እና ጸጥታ ጥበቃ ጽ/ቤት የውትድርና ስልጠና ያላቸውን አካለት መልምሎ መመደቡና ማስጠበቅ በአዋጅ ቁጥር 464...
10/08/2026

በቅርቡ በኢትዮ ቴሌኮም የቴሌኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በአስተዳደር እና ጸጥታ ጥበቃ ጽ/ቤት የውትድርና ስልጠና ያላቸውን አካለት መልምሎ መመደቡና ማስጠበቅ በአዋጅ ቁጥር 464/97 መሠረት ግዴታ ያለበት በመሆኑ፣ እነዚህ የጥበቃ ሰራተኞች የሚቆጣጠር እና የሚያስተዳድራቸው በየወረዳው ያለው የጸጥታ መዋቅር በመሆኑ በዚህ አግባብ የተመደቡ የጥበቃ ሰራተኞች የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኞች ሊባሉ አይችሉም በማለት የህገ መንግስት ትርጉም ሰቷል።

የኔ ጥያቄ በአዋጁ ላይ የፌደራል እና የክልል አስተዳደር ጽ/ቤቶች የቴሌኮሙኒኬሽን እና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት አውታሮችን የመጠበቅ ግዴታ አለባቸው ከማለት ውጭ ለኢትዮ ቴሌኮም ይሁን ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋም መሰረተ ልማቶች ለሚመድባቸው የጥበቃ ሰራተኞች ደሞዝ የሚከፍለው፣ የሚቆጣጠረው፣ የማባረር እርምጃ የሚወስደው ይህ ተቋም ሰለመሆኑ አዋጁ የሚለው ነገር በሌለበት የጥበቃ ሰራተኞቹን የወረዳ ፀጥታ ጽ/ቤት የውትድርና ስልጠና ያላቸውን ሚሊሻም ይሁን ተሰናባች የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩትን መልምሎ ለኢትዮ ቴሌኮም መሰረተ ልማት ጥበቃ ላይ የተመደቡትን ሰራተኞች ደሞዝ በየወሩ የሚከፍላቸው ኢትዮ ቴሌኮም በሆነበት ሁኔታ፣ የጥበቃ ሰራተኞችም የሚተዳደሩበት አንድ የሥራ ሂደት ቡድን በማደራጀት በቡድኑ በኩል ሰራተኞቹን የሚቆጣጠር፣ የሚያስተዳድር ሆኖ ሳለ የፀጥታ ጽ/ቤት እነዚህን የጥበቃ ሰራተኞች የውትድርና ስልጠና ያላቸውን እና ስነምግባር ያላቸውን መልምሎ በመመደቡ ብቻ ደሞዝ የሚከፍላቸው፣ የመዋቅሩ የሚቆጣጠራቸው፣ የሚያስተዳድራቸው ኢትዮ ቴሌኮም ሆኖ ሳለ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የሥራ ውል ቅጥር ግንኙነት የላቸውም ማለት ታድያ የማን ሰራተኞች ናቸው ሊባሉ ነው? የሚጠብቁት የኢትዮ ቴሌኮም መሰረተ ልማቶችን ነው፣ ደሞዝ የሚከፍላቸው ኢትዮ ቴሌኮም ነው፣ የሚተዳደሩት፣የሚመሩት በኢትዮ ቴሌኮም መዋቅር ስር በተደራጀ የሥራ ሂደት ቡድን ነው። ምልመላና ምደባ ብቻ ነው በወረዳ ፀጥታ ጽ/ቤት በኩል የሚከናወነው። በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሠረት የሥራ ቅጥር ግንኙነት አለ የሚያስብሉ መስፈርቶች ደሞዝ እየከፈ ለተቋሙ አገልግሎት የሚሰጡ ከሆነ የሥራ ቅጥር ውል እንዳለ በተደነገገበት ሁኔታ የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኞች አይደሉም መባሉ እንዴት ይታያል? እስቲ የፌደሬሽን ምክርቤት ውሳኔ እና አዋጅ ቁጥር 464/97 አይታችሁ የሆነ ነገር በሉ? ከዚህ በኃላ ወዴት ይኬዳል?

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

 #በ30/11/2017 ዓም በዋለው ችሎት ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት በመዝገብ ቁጥር 242314 በሆነው በከተማ ህጋዊ ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም የተሰራ ህንፃ ወይም ቤት የህ...
09/08/2026

#በ30/11/2017 ዓም በዋለው ችሎት ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት በመዝገብ ቁጥር 242314 በሆነው በከተማ ህጋዊ ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም የተሰራ ህንፃ ወይም ቤት የህንፃው/የቤቱ ባለቤት ይሆናል የሚለውን የህግ ትርጉም በመለወጥ የህንፃውን/የቤቱን የሰራበትን ወጪ ከመጠየቅ ውጭ የይዞታው ባለቤት መሆን አይችልም በማለት አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰቶበታል። የፌደሬሽን ምክርቤትም በቀድሞ ውሳኔዎች የህንፃው ባለቤት ይሆናል በማለት በተሰጡ ውሳኔዎች ላይ የህገ መንግስት ትርጉም አቤቶታ ቀርቦ ሰሞኑን የሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ውሳኔን በሚደግፍ መልኩ ግምቱን ከመጠየቅ ውጭ የይዞታው ወይም የህንፃው ባለቤት መሆን አይችልም በማለት የህገ መንግስት ትርጉም ሰቷል።

ይሁን እንጂ እራሱ ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ችሎት በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም ህንፃ የሰራ ሰው ህንፃውን የሰራበትን ግምት ከመጠየቅ ውጭ የህንፃው/የይዞታው ባለቤት መሆን አይችልም በማለት አስገዳጅ ውሳኔ የሰጠው አካል በሌላ መዝገብ ቁጥር 244308 በሆነው ደግሞ የከተማ ይዞታ መሬት ክርክር ባለይዞታው መብቱን በአስር(10) ዓመት ጊዜ ውስጥ ካልጠየቀ መብቱ በይርጋ ቀሪ ይሆናል በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ሰቷል። እነዚህ ሁለቱን የሰበር ችሎት ውሳኔዎች አንድ እውቅ የህግ ምሁር የቀድሞ የሰበር ችሎት ዳኛ የአሁኑ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ የሆነው በማህበራዊ ሚዲያ ባጋራው ጽሑፍ ላይ ''በአንዱ በር የዘጋውን በሌላ በር ከፈተው'' በማለት የገለፀበት ሂስ በጣም አስደንቆኛል። በአንዱ በር የዘጋው በሌላ ሰው የከተማ ይዞታ ላይ ያለ ተቃውሞ ህንፃ/ቤት የገነባ ሰው ህንፃውን የሚገነባበትን ወጪ ከመጠየቅ ውጭ ህንፃው የተገነባበትን ይዞታ ባለመብት አያደርገውም ይዞታውን ይለቃል ሲል ይርጋ መቃወሚያም ማንሳት አይችልም የሚል አንድምታ ያለው በመሆኑ በዚህ ውሳኔ በሩን የዘጋውን በሌላ የሰበር ውሳኔ ደግሞ የከተማ ይዞታ ክርክር በአስር(10) ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት የሰጠው ውሳኔ በሩን ከፍቶ አስገዳጅ የሰበር ትርጉም ሰቷል። የሚገርመው ደግሞ ሁለቱም ውሳኔዎች የተሰጡት ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት መሆኑ ነው። በመሆኑም የከተማ መሬት ይዞታ በሊዝ አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሠረት የሊዝ ዘመኑ ከ60 ዓመት እስከ 99 ዓመት ሆኖ ሳለ፣ እንዲሁም የከተማ መሬት ስልጣን ካለው የመንግስት ተቋም ፍቃድ ውጭ መያዝ እንደማይቻል ብዙ በተለያዩ ጊዜያት የተሰጡ አስገዳጅ ውሳኔዎች ያሉ በመሆኑ የከተማ ይዞታ ክርክር በአስር(10) ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት በተሰጠው የህግ ትርጉም ላይ ህግ አውጪው የከተማ ይዞታ ባዶ መሬት ክርክር የይርጋ ጊዜ ሊዝ አዋጁን በማሻሻል በአዋጁ መፍትሄ በመስጠት ወይም የፌደሬሽን ምክርቤት ህገ መንግስታዊ ትርጉም በመስጠት መፍትሄ ካልተበጀለት ፍርድ ቤቶች አስገዳጅ የሰበር ችሎት ውሳኔዎችን መሠረት በማድረግ ውሳኔ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ከመንግሥት በምሪት ያገኙትን የከተማ መሬት በህገ ወጦች ሀሰተኛ የሰው ምስክር በማደራጀት የሰው ይዞታ በመያዝ የአስር አመቱን ይርጋ በማንሳት የህጋዊ ባለይዞታዎችን መብት ሊያሳጡ ይችላሉ። እያሳጡም ይገኛል። በቅርብ የተሰጡ ውሳኔዎች እያየን ቢሆንም ጉዳዮቹ በይግባኝ ክርክር ላይ በመሆናቸው በጉዳዮቹ ላይ ሀሳብ ከመስጠት ተቆጥበናል። በመሆኑም ሰበር ሰሚ ችሎት በተለይ ሰባት ዳኞች የሚሰየሙበት ችሎት የህግ ትርጉሙ ውሳኔዎች ሲሰጡ ውሳያቸው አንዱ ከአንዱ ተቃርኖ እንዳይኖረው ጉዳዮችን ነጥሎ ከማየት ከጠቅላላው የህግ ጽንሰሀሳብ፣ ጅሪስፕሩደንስ መርህን በመከተል የአንዱ የህግ ትርጉም ሌላው የህግ ትርጉም ላይ በር እንዳይከፍት ሊጤን ይገባዋል።

ይህ ጽሑፍ የማንም ሀሳብ ሳይሆን የእኔ የግሌና የተሰማኝን፣የተረዳሁትን በአቅሜ ሀሳቤን ለማጋራት የቀረበ መሆኑን መግለጽ እወዳለሁ።

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

09/08/2026

የሥዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ የሆነው ዮናስ መኳንንት፤ ተወልዶ ያደገባትን፣ የእንጀራ ገመዱ የነበረችውን አዲስ አበባን ጥሎ ገጠር ከገባ ከጥቂት ወራት በኋላ ሁለት ዓመት ይሞላዋል።

ዮናስ ከተማን እርግፍ አድርጎ ጥሎ ገጠር እንዲገባ ያደረገው፤ በአዲስ አበባ ተጀምሮ በሌሎች የክልል ከተሞች የተተገበረው የኮሪደር ልማት መሆኑን ይናገራል።

የካቲት 2016 ዓ.ም. በአራት ኪሎ፣ ፒያሳ እና በሌሎችም የከተማዋ ቦታዎች የተጀመረው የኮሪደር ልማት ዮናስ እና ቤተሰቡ ወደሚኖሩበት ዑራኤል አካባቢ የደረሰው ብዙም ሳይቆይ ነበር።

ዋና ዋና መንገዶችን በማስዋብ፣ የእግረኛ መንገድን በማስፋት እንዲሁም የመዝናኛ ቦታዎችን በመገንባት ላይ በሚያተኩረው በዚህ ፕሮጀክት ሳቢያ፣ "ከቤተሰቤ ጋር የምኖርበት ቤት ፈረሰ" ይላል ዮናስ።

ይህ አጋጣሚ ታዲያ ብዙ ጊዜ ሲያስበው የነበረውን፣ ግን ደግሞ ሊሳካ ያልቻለውን ከተማን ጥሎ የመውጣት ምኞቱን ዕውን አደረገለት።

👉🏾 https://bbc.in/4wjGtN8

Address

Oromia Regional State
Adama

Telephone

+251910266507

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ:

Shortcuts

Share

Category