Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ I am an Attorney and a Legal Advisor at all Federal and Oromia Courts with more than 15 years of experience.

I have an LLM Degree(Master of Laws) in Commercial and Investment Law and I have an LLB Degree from Mekelle University in 2007

24/04/2026
  (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 271726ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 249795 ላይ “ሠራተኛዉ በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ቢቀር...
24/04/2026

(ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 271726

ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 249795 ላይ “ሠራተኛዉ በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ቢቀር እንኳ ከሥራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን አሠሪዉ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) ሳይሰጥ የሥራ ዉልን ለማቋረጥ እንደማይችል” ተገልጾ የተሰጠው የህግ ትርጉም ተለውጦ “የአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27(1)(ለ) ድንጋጌ ሠራተኛዉ በዚሁ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ዉጭ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ላይ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ዉልን ያለ ማስጠንቀቂያ ማቋረጥ ይቻላል” በሚል ተተርጉሟል፡፡

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ



  በአብጫ ድምጽ ንብረትን እንዲሸጥና እንዲለውጥ ልዩ ውክልና ስልጣን የተሰጠው ተወካይ ንብረቱን አስይዞ መበደር አይችልም የወካይን ንብረት የማፍራት ህገመንግስታዊ መብትን ይጥሳል በማለት የው...
15/04/2026

በአብጫ ድምጽ ንብረትን እንዲሸጥና እንዲለውጥ ልዩ ውክልና ስልጣን የተሰጠው ተወካይ ንብረቱን አስይዞ መበደር አይችልም የወካይን ንብረት የማፍራት ህገመንግስታዊ መብትን ይጥሳል በማለት የውሳኔ ሀሳብ ያቀረበውን ውድቅ በማድረግ በልዩነት ሀሳብ የቀረበውን ንብረትን የመሸጥና የመለወጥ ሙሉ ውክልና ያለው ተወካይ ንብረቱን አስይዞ መበደር ይችላል በማለት ህገ መንግስታዊ ትርጉም አያስፈልገውም በማለት የቀረበውን የልዩነት ሀሳብ በማጽናት ውሳኔ ሰቷል። ከውክልና ህግ መርህ ጋር ሲታይ የመሸጥና የመለወጥ ሙሉ ውክልና ያለው ተወካይ ለወካይ ጥቅም ንብረቱን አስይዞ ከባንክ ገንዘብ ቢበደርበት ህጉ አይፈቅድም እንዴ? apparent authority ምንድን ነው? የመሸጥ ስልጣን ትዩዩ የሆኑ የበለጠ ሳይሆን የሚያንሱ እና እኩል ስልጣን የሆኑትን መፈጸም አያካትትም? የልዩነት ሀሳብ የቀረበው ምክንያታዊ ነው የሚልም የግል ሀሳብ አለኝ። የፌደሬሽን ምክርቤትም ይህንኑ የልዩነት ሀሳብ በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ የህገመንግስት ጥሰት አልተፈፀመበትም በማለት ውሳኔ ሰቷል።

#ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

15/04/2026

/ቤት ያወጣው የቅጥር ማስታወቂያ።
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልክቱ
መልካም እድል
ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

15/04/2026
  ውስጥ ተሰማርተው ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሃብቶች ከገቢ ግብር ነጻ እንዲሆኑ መፈቀዱን በሚመለከት ከገንዘብ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም - የአገራችን የኢንዱስት...
13/04/2026

ውስጥ ተሰማርተው ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሃብቶች ከገቢ ግብር ነጻ እንዲሆኑ መፈቀዱን በሚመለከት ከገንዘብ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ
ሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም - የአገራችን የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፤ የግብአት አቅርቦት ችግርእና የባለሙያ እጥረት በዋንኛነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን ማሳደግ ይገባል፡፡
በዚህም መሰረት ግብአቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን የሆነውን ካፒታላቸውን በመያዝ ረገድ የሚያሳድረባቸውን ጫና ማቃለል ያስፈልጋል።
በእነዚህ ምክንያቶች አስመጪዎች ግብቶችን እና ምርቶችን ቀረጥ እና ታክስ ሳይከፍሉ ወደአገርአስገብተው ለግብአቱ ወይም ለምርቱ ገበያ ባገኙ ጊዜ ቀረጥ እና ታክሱን የሚከፍሉበትን አሰራር የሚፈቅድ የነጻ የንግድ ቀጠና አሰራር የተዘረጋ ሲሆን፤ ይህንን ስርአት የሚያስፈጸሙ ነጻ የንግድ ቀጠናዎች በየካባቢው የተቋቋሙ መሆኑ ይታወቃል::
እነዚህ ነጻ የንግድ ቀጠናዎች ባለሃብቶችን የበለጠ የሚሰቡ እንዲሆኑ ለማድረግ ከላይ ከተገለጸው በተጨማሪ በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ውስጥ ተሰማርተው ግብአቶችን እና ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ ስራ ላይየተሰማሩ ባለሃብቶች ከገቢ ግብር ነጻ እንዲሆኑ ተፈቅዷል፡፡
ሰለዚህ ባለሃብቶች ይህንን እድል በመጠቀም በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ እናሳሳባለን።




09/04/2026

የሆርሙዝ የበሀር ትራንዚት እንደተዘጋ ወዲያውኑ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ተደረገና የምርቶች ዋጋ ጭማሬ ጦዘ አሁን ሲከፈት ደግሞ ለምን ቅናሽ የማይደረገው? ቢከፈትም ነዳጅ አልገባም እንዳትሉኝ፣ እንደተዘጋ ተጽዕኖው ወዲያው ኢትዮጵያ ላይ አይደርስም ግን ወዲያው ጭማሪ ተደረገ፣ ሲከፈት ደግሞ ወዲያው ቅናሽ ሊደረግ አይገባም ነበር?

7 (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 246230ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 186946 የተሰጠው ውሳኔ ‘‘በአንድ ቦታ ላይ ሁለት የተለያዩ ሰዎች የይዞታ ማረ...
09/04/2026

7 (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 246230
ከዚህ ቀደም በሰ/መ/ቁ 186946 የተሰጠው ውሳኔ ‘‘በአንድ ቦታ ላይ ሁለት የተለያዩ ሰዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቢኖራቸው አንደኛው ቤት ቢሰራ ሌላኛው ወገን በይዞታዬ ላይ እየተቃወምኩኝ ቤት ስለሰራ ያፍርስልኝ በማለት መጠየቅ የማይችል መሆኑን’’ የሚገልጸው ውሳኔ ተለውጧል፡፡

7 (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት መዝገብ ቁጥር 246230

“በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ186946 በሚያዝያ 26/2013 ዓ.ም የተሰጠው አስገዳጅ ትርጉም እና ሌሎች መዝገቦች ላይ የተያዘዉ ተመሳሳይ አቋም ተለውጦ፤ በአንድ ባለይዞታ ሊመዘገብ የሚገባን የከተማ ይዞታ ከአንድ በላይ የሆነ የይዞታ ማረጋገጫ ወይም ካርታ ለተለያዩ ሰዎች ተደርቦ ተሰጥቶ ሲገኝ ለቦታው ባለመብትነት ቅድሚያ የሚሰጠው መጀመሪያ ያስመዘገበው ሰው ነው’’ በሚል ተተርጉመዋል፡፡

ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ

07/04/2026

ማስታወቂያ

06/04/2026

#ናፍጣ የጨመረው ከ20% አይበልጥም ትራንስፖርት ግን ከ400% በላይ ጨምሯል! የባለንብቶቹ ስግብግብነት በህዝብ ችግር መበልጸግ የጉድ አገር ማለት ይሄ ነው????

Address

Oromia Regional State
Adama

Telephone

+251910266507

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Attorney Demelash Nigatu ጠበቃ ደመላሽ ንጋቱ:

Share

Category