17/08/2024
ፍትህ!
የ7 ዓመት ህፃንን በአሰቃቂ ሁኔታ ደፍሮ ለገደለ ትክክለኛው #ቅጣት ምንድነው? #ጠማማው የወንጀል ህጋችንስ ስለፍትህ እና ቅጣት ምን ይላል?
በኔ መረዳት ፍትህ ማለት ሰዎችንና ፍጥረትን እግዚአብሔር በምፈልገው መንገድ ማስተናገድ ነው (Justice is a practice of treating human beings and nature in a way God wants them to be treated)::
እግዚአብሔር ከብዙ ሺ ዘመናት በፍት በስና ተራራ የዚህ አይነት ወንጀል የምፈጽሙ እንዲገደሉ ህግን ሰጠ (ዘጻ 21:14)::
በ20ኛው እና 21ኛው ክፍለ ዘሜን የተነሱ ጠማማ ምሁራን ከፈጣሪ በላይ እኛ ጥበበኞች ስለሆንን ነፍሰ-ገዳዮችን መንግስት አይግደላቸው ይልቁንስ አስሮ እየቀለባቸው ትምህርት ይስጣቸው አሉ:: አብዘኛዎቹ የሰለጠኑ የተባሉ ሀገራት መንግስታት ይህንን ፍልስፍና በመቀበል ከተበዳይ ይልቅ ለወንጀለኛው መብት ተቆርቋሪ በመሆን ከአመፀኛዎች ጋር ወገኑ:: ለሁሉም ወንጀል ቀለል ያለ ቅጣት ፈበረኩ::
ሀገራችን ኢትዮጵያም የዚህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ሰለባ ሆነች :: የወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 1 የወንጀል ህጉ "ዓላማና ግብ" በምለው ክፍል ወንጀለኛ የሚቀጣው ለላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠብ ወይም ለሌሎች ማስተማርያነት ወይም እንድታረም በማድረግ ሌላ ወንጀል እንዳይፈጽም ነው ይላል:: እስር ቤቶቹ ማረሚያ ተብለው የሚጠሩትም በዚህ ምክንያት ነው:: በአጭሩ በኢትዮጵያ ወንጀለኛ የሚቀጣው አሁን ለፈፀመው ወንጀል ወይም ለወንጀል ተጠቂው ፍትህ ለመስጠት ሳይሆን ወንጀለኛውን አባብሎ እና እሹሩሩ ብሎ ለማስተማር ነው :: የወንጀል ህጋችን ከፍትህ ጋር የተፋታ ህግ ነው::
የፈረደበት ህዝብ ይህንንም ወንጀል ፈፃሚ ከሁላችን በሚሰበሰበው ግብር አስሮ እንደምቀልበው
ይገመታል:: ከነዚህ ልጃቸውን በግፍ ከተነጠቁ ወላጆች ጭምር በሚሰበሰብ ግብር ወንጀለኞች ይቀለባሉ::
ይህ ደግሞ ከተፈፀመው ወንጀል የማይተናነስ ግፍ ነው::
ህጋችን ልሻሻል ይገባል! በጠማማ ህግ የተቃና ፍርድ የለም !