Gamo Zone Geressie Zuria woreda People's Council Office

Gamo Zone Geressie Zuria woreda   People's Council Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo Zone Geressie Zuria woreda People's Council Office, Arba Minch'.

የጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወርዳ ሕዝብ ምክር ቤት በዞናችን ሦስት ወረደዎች በጋጮ ባባ፣ በቦንኬ ወረዳና በካምባ ዙሪያ ወረዳ በተከሰተ የናዳና የጎርፍ አደጋ ከ 52 ሰዎች በላይ ሕይወት ማለፉን ...
12/03/2026

የጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወርዳ ሕዝብ ምክር ቤት በዞናችን ሦስት ወረደዎች በጋጮ ባባ፣ በቦንኬ ወረዳና በካምባ ዙሪያ ወረዳ በተከሰተ የናዳና የጎርፍ አደጋ ከ 52 ሰዎች በላይ ሕይወት ማለፉን በመስማታችን የገረሴ ዙሪያ ወረዳ የተሰማንን መሪር ሐዘን እንገልፃለን።

የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አየለ ቦላ ድንገተኛ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ፤ ለአደጋው ሰለባ የሆኑ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለመላው የዞኑ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል።

​መጋቢት 3/2018 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት ኮሙዩኒኬሽን /ጽ/ቤት)

ጋሞ ዞን ገረሴ ቦንኬ ምርጫ ክልል የ6ኛው ዙር የህዝብ ተወካዮች ክልል ም/ቤት 5ኛ ዓመት  የሥራ ዘመን የውክልና ሥራ ተወካዮች ከመረጠው ህዝብ ጋር ውይይት እያደርጉ ይገኛሉ።ገረሴ:30/7/2...
09/03/2026

ጋሞ ዞን ገረሴ ቦንኬ ምርጫ ክልል የ6ኛው ዙር የህዝብ ተወካዮች ክልል ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የውክልና ሥራ ተወካዮች ከመረጠው ህዝብ ጋር ውይይት እያደርጉ ይገኛሉ።

ገረሴ:30/7/2018 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝቡ ም/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳይ አገልግሎት)

የቦንከ -ገረሴ ምርጫ ክልል ተወካይ ፕሮፌሰር ይስኃቅ ካጫሮ፣የቦንከ-ገረሴ ምርጫ ክልል ተወካይ አቶ አቅመ አርዞ
የቦንከ ገረሴ ምርጫ ክልል የገረሴ ምርጫ ክልል የሁለቱ መዋቅር ዋና አፌ ጉባኤዎች፣የሀገር ሻማግለዎች፣ባጠቃላይ ሲቪል ሰርቫንት እና አከባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

በምክክር መድረኩም የሁለቱ መዋቅር ከባለፈው ምርጫ ጊዜ ደምሮ እስከዚህ የተሠሩ የልማትና ከመልካም አስተዳደር ሥራዎች አኳያ የጋራ ውይይት እንደሚያካሄዱ ተገልፀዋል።

በመቀጠልም በሚቀጥለው ምርጫ ዙሪያ መሠራት ያለባቸውን ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ምክክር ለማድረግ መሆኑን ፕሮፌሰር ይስኃቅ ካጫሮ ተናግረዋል።

ዘገባው :- የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ም/ቤት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ነው።

የጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አፌ-ጉባኤ  የተከበሩ አቶ አየለ ቦላ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የእንኳ...
06/01/2026

የጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አፌ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ አየለ ቦላ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
የተከበሩ አቶ አየለ ቦላ ባስተላለፉት መልዕክት የገና በዓል አምላክ ለሰው ልጅ ያለውን ወሰን የሌለው ፍቅርና ትህትና የገለጠበት፣ የጨለማው ዘመን አብቅቶ የብርሃን መውጣትና የድነት የምስራች የተሰማበት ታላቅ ዕለት መሆኑን ገልጸዋል።

በዓሉ በሃይማኖታዊ እሴቱ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ቤተሰብ በፍቅር የሚሰባሰብበት፣ እንደ ገና ጨዋታ ያሉ ባህላዊ እሴቶች የሚንፀባረቁበትና አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት የሰላምና የደስታ ተምሳሌት መሆኑን አብራርተዋል።

የዘንድሮውን የገና በዓል ልዩ የሚያደርገው ኢትዮጵያ የነበረችበትን የፈተና ወቅት አልፋ በሉዓላዊነቷና በኢኮኖሚ ነጻነቷ ከፍታ ላይ በምትገኝበት የታሪክ ምዕራፍ ላይ የምናከብረው በመሆኑ ይህን ታሪካዊ አጋጣሚ ተጠቅመን ለሀገራዊ ከፍታችን በአንድነት የምንቆምበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በመሆኑም በዓሉ በታላቅ የድልና የልማት ብስራት የሚከበር እንደሆነ የገለፁት ስሆን ለሀገራዊ ስኬት መሰረቱ የወረዳችን ሁለንተናዊ እድገት መሆኑን በመጥቀስ ሰላምን በማስፈን፣ መሰረተ ልማት እንድታረጋግጥ ጥሬውን አስተላልፏል።

​ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት

28/11/2025
በገረሴ ዙሪያ ወረዳ  ህዝብ ምክርቤት አዘጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በደማ...
28/11/2025

በገረሴ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ ምክርቤት አዘጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።
ህዳር 19/2018 ዓ.ም ገረሴ ዙሪያ ሕዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት)
"ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ስሆን።
ኢትዮጵያውያን የመቻቻልና የአብሮነት እሴቶች ያሉን ረጅም ዘመናትን አብረን ያሳለፍን በጋራ ተጋድሎአችን አኩሪ ታሪክ እያስመዘገብን የመጣን በጉዟችን የባህል የወግና ልማድ ውህደት እና ጠንካራ ትስስር ፈጥረን የመጣን የአኩሪ ታርክ ባለቤቶች ነን ሲሉ የወረዳው ዋና አፈጉ-ጉባኤ አቶ አየለ ቦላ በመክፈቻ ንግግራቼ የገለፁት ስሆን።
ህብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም ስርዓት ህዝቦች ማንነታቸውን ሳይክዱ በመግባባትና በመፈቃቀድ ላይ የተመሠረተ ዴሞክራሲያዊ አንድነት የሚገነቡበት ስርዓት እንደሆነም ክቡር አቶ አየለ ቦላ በመግለጽ ውይይቱ በተለያዩ ኩነቶች ስከበሪ ቆይቶ ማጠቃለያ በወረዳ ማዕከል ተከብሯል።

''የሐሳብ ጠብታ ለሀገር ግንባታ'' በሚል መሪህ ቃል በገረሴ ዙሪያ ወረዳ የቀበሌ ም/ቤቶች አፌ ጉባኤዎች የወረዳ ምክር ቤት ተንቀሳቃሽ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙቤትየጋራ የምክክር ፎሬም እየ...
21/11/2025

''የሐሳብ ጠብታ ለሀገር ግንባታ'' በሚል መሪህ ቃል በገረሴ ዙሪያ ወረዳ የቀበሌ ም/ቤቶች አፌ ጉባኤዎች የወረዳ ምክር ቤት ተንቀሳቃሽ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙቤትየጋራ የምክክር ፎሬም እየተካሄደ ነው።

ኅዳር 12/2018 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ም/ቤት)

በፎሬሙ መክፈቻ የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አየለ ቦላ ባደረጉት ንግግር የቀበሌ ም/ቤት አባላት የስልጣን ባለቤት በመሆናቸው ኃላፊነታቸውን በአገባቡ እንዲወጡና በየምክር ቤቶች ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመቀመር ይኸ የስልጠናና የምክክር መድረክ እንደተዘጋጀ ተናግሯል።

ከዚህ ስልጠና በኃላ የቀበሌ ም/ቤት አፌ ጉባኤዎች ኃላፊነታቸውን በአገባቡ በመወጣት ጉባኤዎችን በወቅቱ አለማድረግና ሪፖርቶችን ማንጠባጠብ ማስተካከያ እንደሚደረግ ይጠበቃል ብሏል።

የብልፅግና ጉዟችን ዕውን ለማድረግ የክትትል ቁጥጥር ቁጥጥር ሥርዓት በማጠናከር ውስን ሀብቶችን ለታለመለት ዓላማ ለማዋል የተዘጋጀውን ስልጠና የቀበሌ ምክር ቤቶች ቀጣይ ሥራ ለመሥራት አባላት በትኩረት ስልጠናውን እንድከታተሉ አሳስቧል።

በመድረኩ የአፌ ጉባኤዎች የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ፣ የክትትል ቁጥጥር ምንነትና አስፈላጊነት ዙሪያ ስልጠናና የሴት ምክር ቤት ኮከስ አባላት ስልጠና እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

18/10/2025
የጋሞ ዞን ገረሴ ዙርያ ወርዳ ወና አፌ-ጉባኤ አቶ አየለ ቦላ የደመራ እና የመስቀል በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉለክርስትና እምነት ተከታዮችና ለመላው ኢትዮጵያ...
26/09/2025

የጋሞ ዞን ገረሴ ዙርያ ወርዳ ወና አፌ-ጉባኤ አቶ አየለ ቦላ የደመራ እና የመስቀል በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ለክርስትና እምነት ተከታዮችና ለመላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን የፍቅር፣ የይቅርታ፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ እና የመከባበር እሴት ማሳያ ለሆነው የመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!
የመስቀል በዓል በሀገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ኃይማኖታዊ ይዘት ካላቸው በዓላት አንዱ ሲሆን ሀገራችን በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸዉ ከማይዳሰሱ ከዓለም ቅርሶች መካከልም አንዱ ነው።
በመሆኑም ሀገራችን አሁን ኢኮኖሚ ከምታመነጭባቸው ዘርፎች አንዱ ለሆነው ለቱሪዝም መስፋፋትና ማንሰራራትም ትልቅ ሚና ያለው ነው።
መስቀል ፍቅርና ይቅርታ የተገለጠበት የሰው ልጅ ሁሌም ቦታ ሊሰጠው የሚገባው መለኮታዊ ፕሮግራም ያለው በህዝበ ክርስቲያን ዘንድ በደማቅ ሁኔታ የሚከበር በዓል ስለሆነ በዓሉን ስናከብር የሚከፋቸው ወገኖች እንዳይኖሩ የተጣላን በማስታረቅ፣ የበደሉን ይቅር በማለት፣ የበደልናቸዉን ይቅርታ በመጠየቅ፣ ጥላቻን ከዉስጣችን በማስገድ በፍፁም ፍቅርና ሰብዓዊነትን በትክክል በሚያሳይ መልኩ ሊሆን ይገባል።
መጪው ጊዜ ሀገራችን በሁሉም ዘርፎች ምርታማና ውጤታማ የምትሆንበት፣ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ይበልጥ የሚጠናከርበት እንዲሁም በአብሮነት ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና መረጋገጥ የበኩላችንን ድርሻ የምንወጣበት ዓመት እንዲሆን እመኛለሁ።

15/08/2025

የቦንኬ ገረሴ ምርጫ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተወካዮችን በገረሴ ከተማ ከመረጣቸው ሕዝብ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሄዱ።

ነሐሴ 8/2017 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ም/ ኮሚኒኬሽን /ጽ/ቤት)

የቦንኬ ገረሴ ምርጫ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተወካዮችን ፕሮፌሰር ይስሐቅ ከጨሮ እና አቶ አቅሜ አርዞ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር የልማት፣ የመልካም አስተዳደር ሥራወችን የተፈጸሙና ያልተፈጸሙት ጉዳዮች ላይ በገረሴ ከተማ ከመረጣቸው ሕዝብ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሄደዋል።

የመራጭ ሕዝብን ወክለው በአዳራሽ ከተገኙ ተወካዮች ከተነሱ ጥያቄዎች የገረሴ ከተማና የድመሌ ከተማ የውሃ ችግር፣ የመብራት መቆራረጥ ችግር እስከአሁን አለመቀረፍ፣ አርባምንጭ ገረሴ የመንገድ ትራንስፖርት የሕዝብ መጉላላት፣ ከታርፍ በላይ ጭማሪ ማስከፈል፣ በመነሐሪያ ከሹፈሮች ጋር ተግባቡ በሚል ሕዝብን ማንገላታት የሚሉ ተነስቷል።

የገረሴ ሆስፒታል ችግር፣ መንግስት የሠራተኛን በተመለከተ የጤና ባለሙያዎችና የመምህራን ጥቅማጥቅም፣ የደመወዝ በጊዜ አለመከፈል እንደት ይፈታል? የመንግስታዊ ዕዳዎች እንደት ይከፈላል፣ የግብርና ግብዓት ዋጋ መናር ጋር ተያይዞ አርሶ አደሩ በአገባቡ እየተጠቀመ አይደለም፣ ጡረተኞች አበል አከፋፈል ከፊተኛ መጉላላትና በደል እየደረሰ ነው።

የገረሴ ከተማን አቋርጦ የሚያልፈው አርባምንጭ ሳውላ መንገድ በ10 ዓመት ዕቅድ ተይዟል ስባል መቼ ነው? የኮርደር ልማቱን ተግባራዊ ለማድረግ ከከተማ አስተዳደሩ አቅም በላይ ነውና እንደት ማሳካት ይቻላል? የመንግስት ሠራተኛው ደመውዝ ዝቅተኛ በመሆኑ ኑሮን መቋቋም አለመቻለሉ ተገስቷል።

በክልል ተጀምሮ ያልተጠናቀቀ የገረሴ-ድሜሌ-ኮሻሌ መንገድ፣ የገረሴ-ጋርባንሳ-ኮሌ መንገድ አለመጠናቀቅ፣ በዞኑ ደግሞ ገረሴ - ዱርቤ - ጎቦባኬ - መለጋጉሌ - ጋርባንሳ ካርቼ መንገድ አለመጠናቀቁን ጠይቋል።

የሁለተኛ ደረጃ ትምርህት ቤት የICT ግብዓትና የኃይል አቅራቦት ችግር፣ የገረሴ ቴክኒክና ሙያ ኮለጅ ግንባታ አለመካሄድ፣የደሽከለ የታሸገ ውሃ ግንባታ በተመለከተ ከተነሱ ጥያቄወች ዋናዎቹ ናቸው።

በወረዳ ደረጃ ምላሽ በሚሹ ጉዳዮች ላይ የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ቦርሴ ቦታ በሰጡት ምላሽ የህዝብ አንድነት እንዳይጠበቅ ባለማወቅ እየተሠራ ባለ ሥራ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካ አብረን እንዳናድግ ሳንካ እየተፈጠረ ስላሌ ጥንቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ በመግለጽ በማህበራዊ ሚዲያ እየተፃፃፉ ያሉ ምንም ነገር ሳይፈጠረ እንደተፈጠረ አድርገው የሚጋነኑ ጉዳዮች ረገብ ማለት እንደሚገባ ገልጿል።

ያለብንን የኢኮኖሚ ችግር ለመቅረፍ ገቢ አሟጠን መሰብሰብ በአቅማችንን ማደረግ የሚገባንን ማድረግ አለብን ያሉት ዋና አስተዳዳሪው አንድ ጊዜ ሁሉን መሥራት ስለማይቻል በጊዜ ህደት እንደሚፈታ መጠበቅ አለብን ብሏል።

ከመንገድ አንፃር በገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መንገድ ብቸኛ ተጠቃሚ ነን፣ የመጀመሪያ ዙር ተጀምሯል። ለቀጣይ 5 ዓመታት በርካታ ቀበሌያትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ይጠበቃል ስሉ እንደገለጹት ከዳንብሌ- ሻለ የተጀመረው ጋሳን ይዞ ክይራ መኩላ - ዛጋና ድመለን እንደሚያገናኝ፣ ዛዝኤ-ካምአለ ባርኤኦሮ- ዛላዶ የተጀመረው ከቡላና ከኮሌ ጋር አገናኝቶ የሚጠናቀቅ መሆኑን ተናግሯል።

የገረሴ - ድመሌ - ኮሻሌ እና ገረሴ - አልጉደ - ጋርባንሳ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከክሊሉ መንገዶች ባለስልጣን ጋር እየተነጋገሩ መሆኑንም ገልጿል።

የድመለ ውሃ በተመለከተ በዞን ደጋፍ ለማስገንባት ጥናት እየተካሄደ በመሆኑ በቅርቡ ሥራ ተጀምሮ እንደሚፈታ ገልጸዋል።

ከግብርና አንፃር ምርት በበቂ ሁኔታ ቢኖርም የህገ ወጥ ነጋዴ ምርቱን እየደበቀ ስላለ የንግድ ሰንሰለቱን ለማሳጠር አቅም ያላቸው ህብረት ሥራ ማህበር እና እንተርፕራይዞችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጿል።

የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኤርምያስ እሼቴ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ እንደ ከተማ አስተዳደር ከማህበራዊ ዘርፉ አንፃር ከዙሪያ ካሉ አጎራባች መዋቅሮች ጋር አንድነትና ግኑኝነት የኢኮኖሚ ትስስርና በሚያሳድጉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት አሳስቧል ።

የገረሴ ሆስፒታል ጉዳይ በቅርብ መብትሄ ላይ ለመድረስ እየተሠራ መሆኑን በመግለጽ የኦፕሬሽን ሥራ ተጠናቆ በማጥራት ተግባር ላይ መሆናቸውን አስታውቋል።

ከመሠረተ ልማት አኳያ መብራት ያለውን ችግር ለመፍታ ከፍተኛ ጥረት እየተሠራ መሆኑ፣ የገረሴ ውሃ ለጊዜው ፓምፕ በመቃጠሉ ጊዜያዊ ችግር ገጥሟል ይህ ለጊዜው የሚፈታ ቢሆንም ለሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመሆን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚሠራ ተናግሯል።

የገረሴ ተክኒክና ሙያ ጉዳይ በርካታ ችግሮች ያሉ በመሆኑ እየተሠራ ሲሆን በተለይ የመብራት ችግር ለመፍታት እራሱን የቻለ ትራንስፎርመር እንዲኖር ግዥ መፈጸሙን ገልጿል።

የቦንኬና የገረሴ ምርጫ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተወካይ ፕሮፌሰር ይስሐቅ ከጨሮ ስያጠቃሊሉ በማህበራዊ ሚዲያ ጥናታዊ ትንታኔ በመስጠት የሚጠቅሙ የማይጠቅሙትን በመለየት ሚዛናዊ መሆን አለብን ስሉ መክረዋል።

የሕዝብ አንድነት ወሳኝ በመሆኑ በሕዝብ አንድነት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት አለበት፣ የሃይማኖትና የባሕል አንድነትም መጠበቅ አለበት ብሏል።

የገረሴ አከባቢ ፓለቲካ ወደ መረጋጋት እየመጣ መሆኑን ከተሰብሳቢዎቹ እየቀረበ ባለው አስተያየት መረዳታቸውንና ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በተደጋጋሚ ለፌደራል፣ ለክሊሉና ለዞን የሚያደርሱ መሆኑን ተናግሯል።

የቦንኬና የገረሴ ምርጫ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተወካይ አቶ አቅመ አርዞ ስያጠቃሊሉ እኛ የእናንተ ቃል አቀባይ በመሆናችን የጠየቃችሁትን ሁሉ ለሚመለከታቸው የሚናደርስ ይሆናል በሜለት በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ምክረ ሐሳብ በመስጠት የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል።

Address

Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Geressie Zuria woreda People's Council Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share