ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ጽ/ቤት

ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ጽ/ቤት The Fear Of Lord is the Beginning of Wisdom!!!!
(5)

‎ # #ለክልላዊ ማንሰራራት ጉዞ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አይነተኛ ሚና አለው።‎‎በጎ ፈቃደኝነት በክልላችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ታላቅ ተግባር ...
07/25/2025

‎ # #ለክልላዊ ማንሰራራት ጉዞ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አይነተኛ ሚና አለው።

‎በጎ ፈቃደኝነት በክልላችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ታላቅ ተግባር ነው። ለማህበረሰባችን በችግር እና በድንገተኛ ጊዜ፣ በፈተና እና በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሁሉ ግንባር ቀደም ደራሻዎች በጎ ፈቃደኞች ናቸው።

‎ # በክልላችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ያለውን በጎ ፈቃደኝነት ተግባራት ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ የሚሆን ታላቅ ተግባር ነው። ለዚህም ሁሉም ሰው በጎ ፈቃደኝነት በሁሉም አከባቢ አዘወትሮ መሰራት ያለበት መልካም ተግባር ሁላችንም እንገነዘባለን ።

‎ #በክልላችን ደቡብ ኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከማህበረሰባችን የአኗኗር ዘይቤ፣ ከሃይማኖት፣ ከባህል እና ከእምነት አስተምርሆ ጋር በጥብቅ የተቆራኘና በደስታ፣ በሀዘንና ሌሎች ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮች ሲከሰቱ የመረዳትና የመደጋገፍ የረዥም ጊዜ ታሪክ ያለው መልካም ተግባርና የማህበረሰባችን ዕሴት ነው ፡፡

‎ #በወጣቶች አስተባባሪነት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በተደራጀ መንገድ የተለያዩ አገልግሎቶች በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህም ወጣቶችን ጨምሮ ዜጎች ለማህበረሰባቸው ብሎም ለክልላቸው በጎ አስተሳሰባቸውን፣ ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን እንዲያበረክቱ በማድረግ የልማት ክፍተቶችን መሙላት የሚያስችል ታላቅና መልካም ተግባር ነው ።

‎በክልላችን እየተከናወነ ባለው በጎ ፍቃድ አገልግሎት ሲጀመር ከነበረበት አሳታፊነቱና ምህዳር ሰፊነቱም በእጅጉ እያደገ ሁሉ ዓቀፍ ተደራሽ እየሆነ ያለ ከማህበረሰባችን የወረስነው እና ለትውልድ የምናስተላልፈው አኩር ዕሴታችን ነው ፡፡

‎ይህ የሚያሳየው አሁንም ወደፊትም በቅንነት ተነሳስተን ከተባበርንና በትጋት ከሰራን ችግሮቻችን ደረጃ በደረጃ መፍታትም ሆነ በዘላቂነት መቅረፍ የሚያስችል እምቅ አቅም በእጃችን ላይ ያለ መሆኑን ነው። እናም ይህን አቅማችንን አቀናጅተን በምልዓት ልንጠቀምበት ይገባል። የጋራ ቅንጅትም በእጅጉ ያሰፈልጋል ።

‎ተጠባቂው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሁን ላይ በክልላችን በሁሉም አከባቢ በአስደማሚ ሁነታ መካሄድ ከተጀመረ ሳምንታት ተቋጥሯል።

‎ይህንንም ተከትሎ ክልላዊ እቅዱን መነሻ ያደረገ እንቅሰቃሴ በየአካባቢው እየተጀማመረ በመሆኑ ከአምናው በተሻለ በጎ አስተሳሰብና በጎ አስተዋጾአችንን ማበርከትም ሆነ እምቅ አቅማችንን መጠቀም የምንችልበት ዘንድሮም ክልላዊ የማንሰራራት ጉዞን እውን ለማድረግ በጋራ መቀናጀት መቻል አለብን ።

‎ #ታዲያስ እርስዎ እንደአንድ በጎ፣ ቅን አሳቢ ዜጋ ላሉበት ማህበረሰብ፣ ለሚኖሩበት አካባቢ እና ክልላዊ ማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት ምን ለማበርከት ተዘጋጅተዋል?
‎የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ትንሸ የለውም።

‎ #ይነስም ይብዛም የእርስዎ አስተዋጾዖ ለውጥ ያመጣልና ከቅን ልቦና በመነጨ ለመልካም ስራ ዘወትር ይተባበሩ። ይጀግኑ፥ የድርሻዎን እየተወጡ የበጎ ፈቃድ አርበኛም ይሁኑ መልዕክታችን ነው።

‎ #ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመቻቻል የሠላምና የብልጽግና ጉዞን እውን እናደርጋለን!!🙏

የህይወት ክህሎት ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ከUNFPAእና ከክልሉ ወጣቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር ስልጠና በወላይታ ሶዶ ከተማ ላይ እ...
05/10/2025

የህይወት ክህሎት ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ከUNFPAእና ከክልሉ ወጣቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር ስልጠና በወላይታ ሶዶ ከተማ ላይ እየተሰጠ ነው ይገኛል።

ግንቦት 02/09/2017 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ከአህጉራዊ የህዝብ ብዛት ፕሮግራም (UNFPA)ከክልሉ ወጣቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር ለፕሮግራሙ ውስጥ ከሚካሄዱ ዞኖች ወረዳዎችና አጎራባች ዘኖች የተመረጡ
ባለሙያዎችና የወጣት አመራሮች ላይ በህይወት ክህሎት ዙሪያ የተዘጋጀ የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ወጣቶች ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል በተዛባ የሥርዓተ- ፆታ ግንዛቤና አስተሳሰብ ምክንያት በተለያየ መንገድ በሴቶች፣ ህፃናትና በወንዶች ላይ የሚፈፀም ጥቃቶች መወገዝ አለበት ቢለዋል።

አክለውም እንደተነገሩት በሁሉም ጾታና እድሜ ክልል ላይ ባሉ አካላት ላይ ሊፈጸም የሚችል ቢሆንም በብዛትና በስፋት በሴቶችና በህፃናት ላይ ስለሚፈጸም ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃቶችን ሁሉም የወጣቶች አደረጃጀት በወጣት ግንዛቤ መፈጠር አለባቸው ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፈ ሃላፊ ሚካኤል ዋዳ እንደገለፁት በማንኛውም ሴት እህቶቻችን ላይ በኣካል የሚፈፀም የሃይል ጥቃቶች በአደረጃጀት ልንከላከል ይገባል በማለት ገለጸዋል ፡፡

ወጣት ሚካኤል አክለውም ሴት እህቶቻችን መምታት፣ መገፍተር፣ መተንኮስ እና እስከ ግድያ ያለውን እንድሁም ወሲባዊ የጥቃትሃይልን በመጠቀም በሌላ በኩል ያለፍላጓቷ/ቱ የሚፈፀም ማንኛውም የወሲብ ድርጊትና የወሲብ ድርጊትን ወንጀል ከመሆኑ አንጻር በየአካባቢያችን በወጣቶች ክንፈ መታገል አለብን ስሉ አሳስበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ማህበር ስብሳቢ ወጣት ሰላማዊት ሃይሉ የመሰሉ ለመልካም ፀባይ ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶችና ትንኮሳዎችን አሰገድዶ መድፍር፣ የወሲብ ንግድ፣ ፆታዊ ትንኮሳ፣ግብረ-ሰዶምና የመሳሰሉት ድርጊቶች በዚህ ዘመን ወጣቶች ፡ ሊያበቃ ይገባል ስሉ ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሃላፊና የሴቶች ህጻናት ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ኩሪባቸው ታንቱ ስልጠና የተመረጡትን ተሳታፊዎች በተለይም በወጣቶች መካከል የተስፋ ህይወትን እንዲመሩ እና በአካባቢያቸው አመራቂ ውጤት በማህበረሰብ ዘንድ እንድመጣ የህይወት ክሎት ስልጤና በውስጣቸው እንዲያዳብሩ ለማድረግ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገለጻ አድረገዋል ።

ወ/ሮ ኩሪባቸው የሴቶች እህቶቻችን ጥቃት:- የወጣቶች ኃይልን በመጠቀም የሚፈጸም ድርጊት አካላዊ፣ስሜታዊ፣ ስነ ልቦናዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ ወይም በማንኛዉም መንገድ የሚገለጽ ሊሆን አይገባም ወጣቱ ይሄንን በሁሉም አደረጃጀቶ ሊያቆም ይገባል በማለት አሳስበዋል ፡፡

የስልጤና ተሳታፊዎቹም ያቀረቡት እይታ መሠረት ስልጠናው በህይወታቸው ላይ አውጪ ውጤት እንደሚመጣ ተሰፋ አለኝ ስሉ አፈፃፀም እንዲኖረው ተስፋ ተሰጥቷል።

ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ተጀመረወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 2/2017 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች አደረጃጀት "ወጣቱ ትውልድ ሀገርንና ተ...
05/10/2025

ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ተጀመረ

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 2/2017 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች አደረጃጀት "ወጣቱ ትውልድ ሀገርንና ተፈጥሮን የመጠበቅና የመንከባከብ ታራካዊ ኃላፊነት ይወጣል" በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የ2017 አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በይ አስጀምሯል።

በማስጀመሪያው መርሃግብር ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሳሙኤል ወጣቱ ትውልድ ሀገርን እና ተፈጥሮን የመጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነትን መውጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

በመቀናጀት፣ በመተባበርና እጅ ለእጅ ተያይዘን በመስራት በሀገራችን ብልፅግና ጉዞ ላይ አሻራን ማሳረፍ ይጠብቅብናልም ብለዋል።

መርሃግብር እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በተቀናጀና በተደራጀ አገባብ በንቅናቄ መመራትና መጠናከር እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፈ ኃላፊ ወጣት ሚካኤል ዋዳ ችግኝን መትከል ብቻ ሳይሆን የመጠበቅና የመንከባከብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።

የሚተከሉ ችግኞች በብዛት በወጣቶች ስብዕና መገንቢያ አከባቢዎች መሆን እንዳለበት ያሳሰቡት ወጣት ሚካኤል የሚንተክላቸው ችግኞች ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው መሆን እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ለውጤታማነቱ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት መሰራት ያስፈልጋል ያሉት ወጣት ሚካኤል በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ማሳተፍ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ዛሬ የተጀመረው ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሁሉንም ወጣቶችን ባሳተፈ መልኩ መሆን እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።

የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ም/ፕሬዚዳንት ወጣት ምህረቱ ዳና በበኩላቸው ወጣቱ በልማት በማሳተፍና ሰላምን ለማጽናት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የተተከለውን በመንከባከብ የማሳደግ ኃላፊነት አለብን ያሉት ወጣት ምህረቱ የተከለውን እስከሚያድግ ድረስ የመጠበቅና የመንከባከብ ስራ መሰራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ይህ መርሃግብር በዞኖች፣ በወረዳና ከተማ አስተዳዳሮች ወጣቱን በማሳተፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።

የጋሞ ዞን ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ የቀጣይ ቀሪ ወራት የማህበሩ ሥራ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።መጋቢት 30 2017 ዓ/ም የጋሞ ዞን ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ የቀጣይ ቀሪ ...
04/08/2025

የጋሞ ዞን ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ የቀጣይ ቀሪ ወራት የማህበሩ ሥራ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

መጋቢት 30 2017 ዓ/ም

የጋሞ ዞን ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ የቀጣይ ቀሪ ወራት የማህበሩ ሥራ ተግባራትና እና በፋሲካ በዓል በጎ ተግባር ዝግጅት ዙሪያ ከማህበሩ አባላትና ከዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

የጋሞ ዞን ወጣቶች ማህበር ፕረዝዳንት ወጣት ደፋሩ ጉልላት የውይይቱ ዋና ዓላማ በዞኑ ውስጥ ባሉት በሁሉም መዋቅሮች የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ አቅመ ደካሞችን ለመርዳት ልየታ በማድረግ በጎ ወጣቶች እና በጎ አድራጊ ማህበራት በማቀናጀት ከወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የማዕድ ማጋራትን ሥራን ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት እንዲሰራ ለማስቻል እንደሆነ ተናግሯል።

የጋሞ ዞን ወጣቶችና ስፓርት መምሪያ የወጣት አደረጃጀት ድጋፍና ክትትል ባለሞያ ወሮ እናትነሽ ዘሪሁን በበኩላቸው ማህቡሩ በቀሪ ወራት የወጣት አደረጃጀት ስራ አስፈፃሚዎችን በሁሉም ቀበሌያት በማጠናከር ወጣቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን በሁሉም መዋቅሮች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አሳስባለች።

"ከጥላቻ የፀዳ አዕምሮ ለአንድነታችን የግልና የአከባቢ ንፅህና ለጤንነታችን" በሚል መሪ ሀሳብ የቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት ከቦዲቲ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ጋር  በመተባበር የደም ልገሳ ተካሂ...
03/20/2025

"ከጥላቻ የፀዳ አዕምሮ ለአንድነታችን የግልና የአከባቢ ንፅህና ለጤንነታችን" በሚል መሪ ሀሳብ የቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት ከቦዲቲ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የደም ልገሳ ተካሂዷል።

ቦዲቲ፣ መጋቢት 11/2017ዓ.ም በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር "ከጥላቻ የፀዳ አዕምሮ ለአንድነታችን የግልና የአከባቢ ንፅህና ለጤንነታችን" በሚል መሪ ሀሳብ የቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት ከቦዲቲ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የደም ልገሳ አካሂዷል።

ምትክ የለሌዉን የሰዉ ልጅ ህይወት ከሞት ለመታደግ ሁሉም ሰዉ ደም እንድለግስ የተደረገዉን ጥሪ ተቀብለዉ ለወገን አለኝተኝነታቸዉን እያሳዩ ነዉ።

ይህንን በጎ ተግባር እየፈፀማችሁ የምትገኙ ወጣቶች ትልቅ ዋጋ እንዳለቸዉ በማሰብ ሁላችሁም ተቀላቀሉ።

!

ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠብቅባቸዋል፦አቶ መስፍን ቶማስወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 8/2017 በወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከዞኑ ጤና መምሪያ ጋር በመተባ...
03/17/2025

ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠብቅባቸዋል፦አቶ መስፍን ቶማስ

ወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 8/2017 በወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከዞኑ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር በወጣቶች ተሳትፎ ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ያለመ ንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

ቀጣይ አቅጣጫን ያስቀመጡት የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ መስፍን ቶማስ ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ወጣት አደረጃጀት ከጤናው ጋር ተቀናጅቶ ያዘጋጁት እጅግ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።

ከጥላቻ የፀዳ ወጣቱን መፍጠር ወቅቱ የሚጠይቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን የተናገሩት አቶ መስፍን አንዳችን ለአንዳችን መተጋገዝና መደጋገፍ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ያለመ ትልቅ ኢንሼቲቭ በበጎ ፊቃደኝነት የሚተገበር መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ለተግባራዊነቱ ወጣት አደረጃጀቶች ቁልፍ ሚናውን እንዲጫወቱ አሳስበዋል።

የጤና ዘርፍ አመራሮች ለንቅናቄው ተግባራዊነቱና ውጤታማነቱ፥ ወጣቱን አቅም አድርጎ ተጠቅመውና ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸውም ጠቅሰዋል።

በሁሉም ዘርፍ የተጀማመሩ ስራዎችን ለማስቀጠል ወጣት አደረጃጀቶች ወጣቶችን በሙሉ አቅም ማሳተፍና ማነቃነቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በልማት፣ በሰላም ግንባታ እና በደም ልገሳ ላይ ወጣቶች ግንባር ቀደም ሚናውን ማበርከት እንዳለባቸውም ጠይቀዋል።

የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ ህብረተሰቡ በጤናው ዘርፍ ማገኘት የሚገባውን እንዲያገኝ ወጣቱ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ አለበት ብለዋል።

ወጣት አደረጃጀቶች በጤናው ላይ የሚንሰራቸው ስራዎች አቅም ይሆናሉ ያሉት ኃላፊው በጤናው ዘርፉ ውጤት እንዲያመጣ ወጣቶች ተጽዕኖ መፍጠርና የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ጽዱ አከባቢና መንደር የመፍጠር ኢንሼቲቭ ውጤታማ እንዲሆን ከወጣቱ አደረጃጀቶች ጋር ቀጣይነት ባለው መልኩ ተቀናጅተን እንሰራለንም ብለዋል።

ወጣቱ ይህንን ኢንሼቲቭ ተቀብሎ እንዲፈጽምና ተግባራዊ እንዲያደርጉ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።

የወላይታ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋ በጋራ ተቀናጅተን ከሰራን የህዝቡን ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንችላለን ብለዋል።

ወጣቱን ባሰተፈናቸው ተግባራት ትልቅ ውጤት እየተገኘ ነው ያሉት ወጣት ታደለ ጽዱ አከባቢና መንደር ንቅናቄን ወጣቱን በማሳተፍና ለውጤታማነቱ ተቀናጅተን መሰራት ይጠብቅብናልም ብለዋል።

ለወጣቱ ያለው እምቅ አቅምን በአገባቡ መጠቀም ይገባል ያሉት ወጣት ታደለ በጉልበት፣ በእውቀትና ሌሎች በማሳተፍ በሁሉም ዘርፍ የሚጠበቅብንን ድርሻ ማበርከት አለብንም ብለዋል።

በወጣቱ ንቁ ተሳትፎ የማይሳካ ተግባር የለም፦ አቶ መስፍን ቶማስወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 8/2017 በወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከዞኑ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር በወጣቶች ተሳትፎ ጽዱ አካባ...
03/17/2025

በወጣቱ ንቁ ተሳትፎ የማይሳካ ተግባር የለም፦ አቶ መስፍን ቶማስ

ወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 8/2017 በወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከዞኑ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር በወጣቶች ተሳትፎ ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር ያለመ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ መስፍን ቶማስ እንደሀገር ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር ንቅናቄ ተደርጎ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።

በወጣቱ ተሳትፎ የማይሳካ ተግባር የለም ያሉት አቶ መስፍን ሁሉአቀፍ ልማት ስራ ላይ የወጣቱ ተሳትፎ ጎልተው እየታየ ይገኛልም ብለዋል።

አከባቢን ፅዱና ውብ በማድረግ ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ እና ሞዴል ቀበሌዎችን ለመፍጠር የወጣቱን ሚና የላቀ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

ወጣቶች የተሰጠውን ትኩረት በሚገባ በማገናዘብና ማጤን ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

አሁን ከምንም ጊዜ በላይ ለእኛ አንድነት ያስፈልጋል ያሉት አቶ መስፍን ወጣቶች ከጥላቻ የፀዳ አዕምሮን በመያዝ የልማት አደናቃፊዎችን የመታገል ስራ መሰራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን የወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ምህረቱ ዳና በበኩላቸው ጽዱ አካባቢንና መንደርን ለመፍጠር የወጣቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑን ድርሻቸውን እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋን ጨምሮ የዞኑ ወጣት አደረጃጀቶች፣ የወረዳና ከተማ የመንግስት ረዳት ተጠሪዎች እና የወጣት አደረጃጀቶች እየተሳተፉ ናቸው።

"በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች በጎ ፈቃደኞችን በማስተባብር ጊዚያቸውና ጉልበታቸውን በበጎ ሥራ ማዋል ይገበዋል :-ብለዋል ወጣት አማኑኤል ሣሙኤልወ/ሶዶ መጋቢት 08/2017 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ...
03/17/2025

"በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች በጎ ፈቃደኞችን በማስተባብር ጊዚያቸውና ጉልበታቸውን በበጎ ሥራ ማዋል ይገበዋል :-ብለዋል ወጣት አማኑኤል ሣሙኤል

ወ/ሶዶ መጋቢት 08/2017 ዓ/ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን በወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቶሜ ገሬራ ቀበሌ የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ አካል የሆነውን አንዲት አቅመ ደካማ አረጋዊያን ቤት ግንባታ አካሂደዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሣሙኤል ባስተላለፉት መልዕክት በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች በጎ ፈቃደኞችን አስተባብሮ ጊዚያቸውና ጉልበታቸውን በበጎ ሥራ ማዋል እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

የክልሉ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሣሙኤል አቅመ ደካማዎችን ማገዝና በጎ ማድረግ ለወጣቱ ሁሉ ጊዜ ተግባር ሆነው መለመድ ይገባዋል ብለዋል።

የተጀመረውን አቅመ ደካማ አረጋዊያን ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ የቤት ቁሳቁስ አሟልተን ወደ ቤታቸው ለማስገባት የባለድረሻ አካላት ቅንጅት እንደሚጠይቅ ወጣት አማኑኤል ሣሙኤል አስረድተዋል።

በየአከባቢው ያሉ ወጣቶች የአከባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር ያልተቋረጠ ድጋፍ በማድረግ ሁለንተናዊ ትብብሩን አጠናክሮ እንድያስቀጥል አሳስቧል ።

ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ምህረቱ ዳና ወጣቶች የአከባቢውን ማህበረሰብ አስተባብሮ ሙሉ ቅድመ ዝግጅት አድርገው በዚህ ልክ ለበጎነት ራሱን ማዘጋጀቱ ለቀጣይ ተስፋ የሚሰጥ ስለሆነ ወጣቱን አመስግነው ። ለቀጣይ የሚያስፈልገውን ቁሳቁስ ሁሉ ህብረተሰቡን በማስተባበር አቅመ ደካማ እናት ቤት እስከሚገቡ ድርስ የበኩላቸውን እንዲወጡ አጽኖኦት ሰጥተዋል ።

ቀጣይ የዝናብ ወቅት ስለሆነ በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁላችንም በጋራ ተባብረን ቤቱን ጨርሰን አቅመ ደካማ እናታችን ወደ ቤታቸው ለማስገባት ያልተቋረጠ ድጋፍ ለማድረግ ለባለድርሻው አካላት ጥሪውን አቅርበዋል ።

የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ሰፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አየሌ ለራሞ የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን አቅመ ደካማ አረጋዊያን በመደገፍ የማህበራዊ ሀብት ሃላፊነቱን እየተወጣ ያለበት መንገድ እጅግ በጣም የሚያስመሰግን እንደሆነ ገልጸው ለቀጣይ በሙሉ ሃላፊነት በአንድ ሳምንት ውስጥ ቤቱን ጨርሰው ለማስረከብ ቃል ገብተዋል ።

በሌላበኩል አቅመ ደካማ አረጋዊያን ወ/ሮ አልማዝ እልታሞ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርቧል ።

በዕለቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሣሙኤል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ምህረቱ ዳና የወላይታ ዞን ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አወቄ በዛብህ; የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ሰፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አየሌ ለራሞ እና የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ወጣት አደረጃጀት አመራሮች በጋራ በመሆን ሥራውን አስጀምረዋል ።

የገቢ አቅማችንን ለማሳደግ ወጣቶች የገቢ አምባሳደር በመሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ተጠየቀወላይታ ሶዶ፤የካቲት 27/2017 የወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከወላይታ ዞን ገቢዎች መ...
03/06/2025

የገቢ አቅማችንን ለማሳደግ ወጣቶች የገቢ አምባሳደር በመሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ተጠየቀ

ወላይታ ሶዶ፤የካቲት 27/2017 የወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከወላይታ ዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በገቢ አሰባሰብ ዙሪያ ለወጣቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ የተዘጋጀ ንቅናቄ መድረክ ተጠናቀቀ።

ማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የወላይታ ዞን የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ቀጣይነት ያለው ልማትና ሰላም በራሳችን አቅም ለማረጋገጥ ገቢን በአገባቡ መሰባሰብ ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢኮኖሚ እንዲቀየር ማርሽቀያርው ገቢ መሆኑን ያስገነዘቡት ኃላፊው በጉባኤው የተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች መካከል አንዱ ለኢኮኖሚ ዕድገት ገቢን ማሰባሰብ እንደሆነም ገልፀዋል።

ወጣቶች ህብረተሰቡን ጋር በማስተባበር ህገወጥነት መታገልና መከላከል እንዳለባቸው ያሳሰቡት ኃላፊው ትክክለኛውን መረጃና ጥቆማን የመስጠት ስራም መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በዞኑ ገቢን ለማሰባሰብ ከፍተኛ ፖቴንሽያል መኖሩን የገለጹት ኃላፊው ወጣቱ በገቢ አሰባሰብ ላይ በጎ ጫናን በማሳደር ከፍተኛ ሚናውን መጫወት እንዳለበትም ጠቅሰዋል።

ወጣቱ ሚናውን በአግባቡው በመረዳት የመፍትሔ አካል ለመሆን የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የገቢ ባለድርሻ አካላት በርካታ መሆናቸውን የገለጹት ያሉት ኃላፊው በየደረጃው የሚገኙ የወጣት አደረጃጀቶች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።

ነገ የሀገራችን ዕድገት ማሳየት የምንችለው የእኛ ቁርጠኝነት ይጠይቃልም ብለዋል።

የወላይታ ዞን የወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አወቀ በዛብህ ለገቢ አሰባሰብ ላይ ከራሳችን የሚጠበቅብንን ተግባር መፈጸም ያስፈልጋል ብለዋል።

የገቢ አማራጮችን አሟጠን ለማሰባሰብ የራሳችንን ድርሻ ማበርከት አለብን ያሉት ወጣት አወቀ ለህብረተሰቡ ግንዛቤን የመፍጠር ስራ መሰራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ለስራው ውጤታማነት ሚዲያን በአገባቡ መጠቀም እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተን መሰራት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋ ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን የወጣት አደረጃጀቶች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት መሰራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ህገወጥ ደረሰኞችና ደረሰኝ የማይሰጡ የንግድ ተቋማትን ትግል ማድረግ ከእኛ ይጠበቃል ያሉት ወጣት ታደለ ለዚህም በባለቤትነት አስፈላጊውን ድርሻ ማበርከት ይጠብቅብናልም ብለዋል።

ወጣቶች የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን በተገቢው ሁኔታ ተረድተው ለተፈጻሚነቱ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡም ጠይቀዋል።

ወጣቱ የገቢ አምባሳደር መሆን ይገባል ያሉት ወጣት ታደለ ደረሰኝ ጠይቆ የሚቀበል ህብረተሰቡን ለመፍጠር ወጣቱ ድርሻውን ማበርከት ያስፈልጋልም ብለዋል።

ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢን አሟጦ ለማሰባሰብ ወጣቶች ከፍተኛ ሚናውን መጫወት አለባቸው፦ አቶ ዘካሪያስ ታደሰወላይታ ሶዶ፤የካቲት 27/2017 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ ዞን ወጣቶች አደ...
03/06/2025

ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢን አሟጦ ለማሰባሰብ ወጣቶች ከፍተኛ ሚናውን መጫወት አለባቸው፦ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ

ወላይታ ሶዶ፤የካቲት 27/2017 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከወላይታ ዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በገቢ አሰባሰብ ዙሪያ ለወጣቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ የተዘጋጀ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የወላይታ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ገቢ የሀገር ኢኮኖሚን ለማንቀሳቀስ እና የህዝብን አዳጊ ፍላጎትን ለመመለስ አይተኬ ሚናን እንደሚጫወት ገልፀዋል።

እንደዞን ከ6 ቢሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት ኃላፊው ይህንን ለማሳካት በየደረጃው ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ሲደረግ መቆየቱንም አስታውሰዋል።

የኢኮኖሚ የሚያመነጨውን የገቢ አማራጮችን አሟጦ ለማሰባሰብ የወጣቱ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

በዞኑ በተለያዩ ምክንያት ሳይሰባሰቡ ታንቆ የቆዩ የገቢ አማራጮች መኖራቸውን የገለጹት ኃላፊው ለዚህም ወጣቱ ጉልህ ሚናውን እንዲያበረክት አሳስበዋል።

ገቢ የማሰበሰበው ገቢ የእኔ ነው የሚል ማህብረሰብን መፍጠር እንደሚጠይቅም አስገንዝበዋል።

ገቢ ተሰብስበው የሚውለው ለህብረተሰቡ ነው ያሉት ኃላፊው የህዝቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት የሚቻለው ገቢ በአገባቡ መሰብሰብ ሲችል ብቻ እንደሆነም ገልፀዋል።

በገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ ማነቆ ከመሆኑ ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው በግብይት ወይም በአገልግሎት ጊዜ በደረሰኝ እየተፈጸመ እንዳይደለም ጠቅሰዋል።

ለዚህም ህብረተሰቡ ለተጠቀመው አገልግሎት ደረሰኝ ጠይቆ እንዲወሰድ ለማድረግ እና ህገወጥ የፎርጅድ ደረሰኝ ለማከላከል ወጣቶች የራሳቸውን ሚና እንዲወጡም ጠይቀዋል።

ከመድረክ ባለፈ በተጨባጭ ወደ መሬት በመውረድ ለውጥ ለማምጣት የክንፉ መዋቅር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መሰራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋ ወጣቱ ኢኮኖሚ የሚያመነጨው ገቢን አሟጦ ለማሰባሰብ የበኩሉን ድርሻ ማበርከት ያስፈልጋል ብለዋል።

በግብይት ወይም በአገልግሎት ወቅት ደረሰኝን ጠይቆ የሚቀበል ህብረተሰቡን ለመፍጠር የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑንም የገለጹት ወጣት ታደለ ወጣቱ የገቢ አሰባሰብ ላይ አምባሳደር መሆን እንዳለበትም አሳስበዋል።

መንግስት ከተለያዩ ገቢ አማራጮች ማግኘት የሚገባውን ገቢን እንዲያገኝ ወጣቱ ለሎች አርአያ በመሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን የማህበርና ፌዴረሽን ሰብሳቢዎች እና የወረዳና ከተማ አስተዳደር የወጣቶች የክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የማህበርና ፌዴረሽን ሰብሳቢዎች እየተሳተፉ ናቸው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን የክልሉን ታዳጊ ወጣቶች ወንድ እግር ኳስ ቡድን የምድብ ጫዋታ በብቃት አሸንፈው ለዋንጫ በመድረሳቸው በመደሰት ለዋንጫ ጫዋታ መልካም ምኞት በመግለፅ ም...
02/11/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን የክልሉን ታዳጊ ወጣቶች ወንድ እግር ኳስ ቡድን የምድብ ጫዋታ በብቃት አሸንፈው ለዋንጫ በመድረሳቸው በመደሰት ለዋንጫ ጫዋታ መልካም ምኞት በመግለፅ ምሳ ግብዣ አካሂደዋል።

ወላይታ ሶዶ በቀን 04/06/2017 ዓ/ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን የክልሉን ታዳጊ ወጣቶች ወንድ እግር ኳስ ቡድን የምድብ ጫዋታ በብቃት አሸንፈው ለዋንጫ በመድረሳቸው በመደሰት ለዋንጫ ጫዋታ መልካም ምኞት በመግለፅ ምሳ ግብዣ አካሂደዋል።

በዕለቱም የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሳሙኤል የክልሉ ታዳጊ ወጣቶች እያሳዩት ያለው ድንቅ ብቃት የኢትዮጵያ ሰፖርት ስብራትን ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ ታዳጊ ወጣቶች ስፖርታዊ ሥነምግባር በማጎልበት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።
አዘጋጅ እንደመሆናችን መጠንና ካለን ስፖርታዊ ሥነምግባርና ብቃት አኳያ ያለምንም ጥርጣሬ ዋንጫውን ለማንሳት ጠንካራ ሥነልቦና መገንባት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል ።

የፌደሬሽን ም/ፕሬዚዳንት ወጣት ምህረቱ ዳና ስፖርታዊ ጨዋነትና ብቃትን ማዕከል ያደረገ እንቅስቃሴ ከታዳጊ ወጣቶች እየተመለከትን ስለሆነን ዋንጫውን ለማንሳት በቁርጠኝነት መጫወት እንዳለባቸው ገልጸዋል ።
አክለውም ታዳጊ ወጣቶች ስፖርትን ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማሳደግና ከዘርፉም ተጠቃሚ ለመሆን በስፖርታዊ ጨዋነት በፍጹማዊ ማሸነፍ ስሜት ለነገ መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

መልካም ዕድል እንመኛለን ለወጣቶቻችን!!

Address

Washington D.C., DC

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ጽ/ቤት:

Featured

Share

Category