Bereket Markos Law Office

Bereket Markos Law Office ጠበቃ እና የህግ አማካሪ

በገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ መሰረት-ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሆኑ እቃዎች፣:- #በረከትማርቆስጠበቃና የህግ አማካሪ
23/06/2024

በገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ መሰረት-ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሆኑ እቃዎች፣:-
#በረከትማርቆስ
ጠበቃና የህግ አማካሪ

05/06/2024

#አሁን አሁን ላይ ፖሊስ ግለሰቦች የተጠረጠሩበት ወንጀል ከባድም ይሁን ቀላል፤ እጅ ከፍንጅ የተያዙም ይሁን በክትትል ተጠርጣሪውን በእስር በማቆየት በ48 ሰዓታት ውስጥ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ይፈቀድልን ማለቱን ልምድ አድርገውታል።
#ጊዜ ቀጠሮ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 67 እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 6 ጥብቅ ጥበቃ ለተደረገለት ልዩ ሁኔታ (Exception) ነው።
#ይህ ልዩ ሁኔታ መሠረት የሚያደርገው ተጠርጣሪው ከእስር ውጪ ቢሆን የፖሊስን የምርመራ ሂደት ሊያደናቅፍ ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን ነጥብ በመመርኮዝ ነው።
👉በፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮ ላይ ቀርበው ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀብዎ እነዚህን ምላሾች ይስጡ!!!
#የተጠረጠሩበትን ወንጀል ያመኑ ከሆነ🤔የተከበረው ችሎት እኔ የተጠረጠርኩበትን ወንጀል መፈጸሜን እያመንኩኝ በዚህም መነሻነት ብቻ ክስ ተመስርቶብኝ ፍርድ ሊሰጥ እንደሚቻል እየታወቀ ጭማሪ ጊዜው አላግባብ ነው፤ በሕገ መንሥት የተጠበቀልኝን የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብቴን የሚጎዳ ነው። በመሆኑም ቀን መጨመር ሳያስፈልገው በዋስትና እንድወጣ ይደረግ፤ ካልሆነ ቀጥታ ክስ እንዲመሰረት ትዕዛዝ ይሰጥልኝ።
#ምስክሮችን ቃል ስላልተቀበልን ቀን ይጨመርልኝ ከተባለ🤔የተከበረው ችሎት ፖሊስ አስቀድሞ የግል ተበዳይንና የምስክሮችን ቃል ማሰባሰብ ሲገባው እኔን አስሮ ማጣራቱ ተገቢነት የለውም፤ እኔ በዋስትና ብወጣም ምስክሮች እነማን እንደሆኑ በማላውቅበት ምናልባትም ምስክሮቹ የፀጥታ አካላት በሆኑበት ምስክሮችን ሊያስፈራራና ሊያባብል ይችላል መባሉ አላግባብ ነውና በዋስትና እንድወጣ ይፈቀድልኝ።
#ምናሰባስበው ማስረጃዎች አሉን ከተባለ🤔የተከበረው ችሎት ፖሊስ ቀድሞ ማስረጃ አለማሰባሰቡ የእርሱ ጥፋት ሆኖ አሁን ላይ እኔን ከፍርድ ውጪ በእስር አውሎ ማስረጃ ላሰባስብ ማለቱ ተገቢነት የለውም፤ ማስረጃዎቹንም ላሰባስብ ያለባቸው ተቋማት እኔ ልደርስባቸውና ማስረጃነታቸውን ልለውጥባቸው ማልችልባቸው ነውና በዋስትና መውጣቴ ምርመራ ሂደቱን ሊያደናቅፍ ይችላል ምባልበት ምክንያት የለም።
#ግብረ አበሮችን መያዝ ይቀረናል ከተባለ🤔ወንጀሉን የፈጸሙት እንደሆነ ግብረ አበሮች እነ እግሌ ናቸው ባላልኩበት ሁኔታ እነማንን ግብረ አበር እያፈላለኩኝ ነው እንደሚል ግልጽ አይደለም፤ አሉ ቢባል እንኳን ለብቻዬ በተጠረጠርኩበት ወንጀል ልከሰስ እና ልቀጣ የሚገባኝ ሆኖ ሳለ ከሌሎች ጋር ተቀላቅዬ ምርመራ መደረጉ ተገቢነት ስለሌለው ለብቻዬ ፍርድ እንዲሰጠኝ እፈልጋለውኝ። በዋስትና እንድወጣ ይፈቀድልኝ።
በተጨማሪም
#ፖሊስ በተፈቀደልኝ ጊዜ የዘረዘራቸውን ተግባራት ፈጸምኩኝ ይበል እንጂ ምንም ያከናወነው ተግባር የለም፤ ፍርድ ቤቱ የምርመራ መዝገቡን አስቀርቦ ይመርምርልኝ፤ በተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ከጠበቃና ከቤተሰብ አባል ጋር እንዳልገናኝ እየተደረኩኝ ነው፤... የሚሉ የሕገ መንግሥታዊ መብቶቹ አለመጠበቅ ካለ ያሳስቡ።
ይግባኝ መብት ነው!!!
ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
በማንኛውም ፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
ከችሎት ሰዓት ውጪ ባሉ
በማንኛውም የሥራ ሰዓት በስልክ
የሕግ ነክ ጉዳዮችን ለማማከር
☎️ 09 10 61 69 50 ይጠቀሙ።
ቴሌግራም Username

የቴሌግራም ግሩፕ
https://t.me/etonlinelegalchat
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/etonlinelegal

05/06/2024
08/05/2024

ህግን የማወቅ አስፈላጊነት

መግቢያ

ሰዎች በተለያዩ መስኮች እውቀት ሊኖራቸው ይችላል። ይህን እውቀታቸውን እንደ ሞያ ወይም እንደመተዳደሪያ ሊጠቀሙበት የሚችሉ ሲሆን ከሞያቸው ውጪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸው እውቀት ደግሞ እንደ ጠቅላላ እውቀት ሊጠቀሙበት ይችላሉ። ስለአንዳንድ ጉዳዮች ማወቅ በምርጫ ሊወሰን የሚችል ቢሆንም ሌሎቹን ማወቅ ግን ግድ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች ይታያል። ከነዚህም ውስጥ በባለሞያ ደረጃ ባይሆንም ህግን ማወቅ ግድ የሚሆንበትን ሁኔታ ከተለያዩ ህጎች መገንዘብ እንችላለን። በዚህ አጭር ፅሁፍ የህግን ምንነት፣ ህግን የማወቅ ጠቀሜታ እና ህግን አለማወቅ በህጉ የሚታይበትን ሁኔታ በአጭሩ እንመለከታለን።

የህግ ምንነት

ህግ የሚለው ቃል በማህበረሰቡ ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ቃል ሲሆን አስገዳጅ መሆኑን የሚገነዘብ ለመሆኑ ቀደም ባለው ጊዜ በየዕለት ኑሮ ፀብ ሲገጥመው እንኳን “በህግ አምላክ” ብሎ ፀብ የማብረድ ልምድ የነበረው መሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ሆኖም ማህበረሰቡ ህግን የሚረዳው በተለምዶአዊው ሁኔታ እንጂ የዘርፉ ባለሞያዎች በሚረዱበት መልኩ አይደለም፡፡

በእርግጥ ህግ ለሚለው ቃል ትርጓሜ መስጠት ቀላል ሥራ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የቃሉ ፅንሰ ሀሳብ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚለዋወጥ በመሆኑ እና የተለያዩ ምሁራን ቃሉን በተለያየ መንገድ የሚገልፁት በመሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም የቃሉ ፍቺ ሊደረስባቸው በሚፈለጉት የተለያዩ ዓላማዎች ምክንያት ሊለያይ ይችላል። ለህግ ቃላት ትርጉም በመስጠት የሚታወቀው ብላክስ ሎው የህግ መዝገበ ቃላት በተሻሻለው ስድስተኛ እትሙ (Black’s Law Dictionary, 6th ed.,) ለህግ ትርጉም ሲሰጥ law is “a body of rules of action or conduct prescribed by controlling authority, and having binding legal force, which must be obeyed and followed by citizens subject to sanctions or legal consequence is a law.” ወደ አማርኛ በግርድፉ ሲመለስ ህግ ስልጣን ባለው አካል የተደነገገው አስገዳጅ ኃይል ያለው እና ዜጎች አክብረው ሊተገብሩት የሚገባ፤ አለመከበሩ ደግሞ ተጠያቂነት የሚያስከትል የተግባር ወይም የምግባር ድንጋጌ ነው።

ሕግን የማወቅ ጠቀሜታ

ሕግ የሀገርን ሰላም ለማስጠበቅ፣ የግለሰብ መብቶችን ለማስጠበቅ፣ ማኅበራዊ ፍትህን ለማስፈን (promote social justice) እና ሌሎች አገልግሎቶች ያሉት እንደመሆኑ ህግን ማወቅ በዋናነት
• መብትን ለመጠቀም እና ግዴታ ለመወጣት
• ለህግ ተገዢ ለመሆን
• የሌሎችን መብት ለማክበር
• እራስን ከሀላፈነት ወይም ከተጠያቂነት ለማዳን ጠቀሜታ አለው።
ህግን አለማወቅ/ስህተት ከተጠያቂነት የማያድን መሆኑ
የወንጀልም ሆነ የፍትሐብሔር ህጎቹ በህግ አውጪው አካል ወጥተው ከፀደቁበት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንደሚውሉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ዜጎች የህጎቹን መኖር ወይም መውጣት የማወቅ ግዴታ አለባቸው፡፡ ይህንም ህግን አለማወቅ ወይም የህግ ስህተት ከተጠያቂነት አያድንም የሚለው የህግ መርህ በላቲን Ignorantia juris non excusat ወይም በእንግሊዘኛ "ignorance of the law has no excuse" ከሮማውያን ህግ የተወሰደ ሲሆን ህግን የማያውቅ ሰው ይዘቱን ባለማወቅ ብቻ ህጉን በመተላለፍ ከተጠያቂነት ሊያመልጥ እንደማይችል የሚገልፅ የህግ መርህ ነው። ይህ ማለት አንድ ሰው ህግ ከጣሰ ህጉን ስለመጣሱ ምንም እውቀት ባይኖረውም ተጠያቂ ይሆናል ማለት ነው፡፡ በዚህም ሰዎች ህጉን አላውቀውም በማለት ድርጊታቸውን ሊከላከሉ አይችሉም፡፡ የዚህ መርህ ምክንያት ሰዎች የህጉን መኖር ቢያውቁም ህጉን አላወኩም በሚል ሰበብ ከተጠያቂነት ለማምለጥ እድል ሊያገኙ የማይገባ መሆኑ ነው፡፡

በኢትዮጵያም ህግ አለማወቅ ወይም የህግ ስህተት ከተጠያቂነት እንደማያድን መሆኑ በወንጀል ህጉ አንቀፅ 81 ስር ህግን አለማወቅ ወይም በህግ ላይ መሳሳት መከላከያ ሊሆን እንደማይችል እና በፍትሐብሔር ህግ አንቀፅ 2035/1 እና 2 ስር አንድ ሰው በህግ ላይ በትክክል የተገለፀውን ድንጋጌ፣ ልዩ ደንብና ሥርዓት የጣሰ እንደሆነ ጥፋተኛ እንደሆነ እና ህግን አለማወቅ ይቅርታ ሊያስገኝ የማይችል መሆኑ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ መንግስትም ማህበረሰቡ ህግን አውቆ እንዲያከብር ህጎችን በተያዩ ዘዴዎች ማሳወቅ ያለበት ሲሆን በሀገራችን ዋነኛው መንገድ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እንዲወጣ በማድረግ ነው።

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ ህግ የሀገርን እና የዜጎችን ሰላም ከማረጋገጥ አንፃር ጉል ሚና ያለው እንደመሆኑ እና ህግን አለማወቅም ከተጠያቂነት የማያድን በመሆኑ ዜጎች በህግ ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

የፍትህ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ትስስር ገፆችን ይቀላቀሉ
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...

17/04/2024

የወንጀል ህግ መርሆች

መግቢያ

ወንጀል ማለት በህግ አስቀጪነቱ የተደነገገውን ድርጊት በማድረግ ወይም ባለማድረግ የህግ ተጠያቂነት እና ቅጣትን የሚያከትል ድርጊት ነው። የወንጀል ህግ ደግሞ ወንጀል ስለሆኑ ድርጊቶች እና አለማድረጎች እንዲሁም ቅጣታቸውን የሚዘረዝር የህግ አይነት ነው። የወንጀል ህግ የራሱ የሆኑ መርሆች ያሉት ሲሆን በሀገራችንም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት እና የወንጀል ህጉ አለማቀፋዊ ባህርይ ያላቸውን መርሆች አካተው የወጡ ናቸው። በዚህ ፅሁፍ በህገ መንግስቱ እና በወንጀል ህጉ የተደነገጉ የወንጀል ህግ መርሆች በአጭሩ እንመለከታለን።

• የወንጀል ህግ መርሆዎች

“መርህ” ማለት የአንድ ነገር ማጠንጠኛ መሰረት ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን በቀላሉ የማይለወጥ፣ የማይሸረሸር፣ ሊጣስ የማይገባውና ከተጣሰ ግን ያ በሱ ላይ የተመሰረተው ፍሬ ሀሳብ ህልውናው ሊናጋ ስለሚችል መርሁ ወይም መሪው ሀሳብ በሚገባ ሊጠበቅና ሊያዝ የሚገባው ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል ደስታ ተክለ ወልድ በአማርኛ የመዝገበ ቃላት መፅሐፋቸው “መርህን” “የመራ፣ የሚመራ፣ መሪ” በሚል የተረጎሙት። በመሆኑም ህጎች ሲወጡም ሆነ ሲተገበሩ የህግ መርሆችን መሰረት ያደረጉ መሆን ይኖርባቸዋል። በአለም አቀፍ ደረጃም ሆነ በሀገራችን ተቀባይነት ያላቸው እና በሥራ ላይ እየዋሉ የሚገኙ የወንጀል ህግ መርሆችን እንደሚከተለው እንመለከታለን።

1. የሕጋዊነት መርህ (Principle of Legality)፡- የህጋዊነት መርህ

መሰረታዊ ሀሳብ በህግ ከተደነገገው ውጪ ቅጣት ሊኖር አይችልም የሚል ነው። በመሆኑም ማናቸውም ሰው የተከሰሰበት ድርጊት በተፈፀመበት ጊዜ ድርጊቱን መፈፀሙ ወይም አለመፈፀሙ ወንጀል መሆኑን የሚደነግግ ህግ ከሌለ በወንጀል ተጠያቂ ሊሆንና ሊቀጣ አይገባውም የሚል ነው፡፡ አንድን ሰው ሆነ ብሎም ይሁን በቸልተኝነት አንድ ድርጊት ፈፅመሀል ወይም መፈፀም የሚገባህን አልፈፀምክም ብሎ ለመክሰስና በወንጀል እንዲቀጣ ለማድረግ የወንጀል ፈፃሚው ድርጊት ወይም ተዓቅቦ በወንጀልነት የሚፈርጅና የወንጀል ቅጣት የሚደነግግ አስቀድሞ የታወጀ ህግ መኖር አለበት፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ሕገ-ወጥነቱ በህግ ያልተደነገገን ድርጊት ወይም ግድፈት እንደወንጀል ሊቆጥረው እና ቅጣትን ሊወስን እንደማይችል በወንጀል ህጉ እንቀፅ 2(2) ስር ተደንግጎ ይገኛል። እንዲሁም ፍርድ ቤቱ በህግ ከተደነገገው በቀር ሌሎች ቅጣቶችንና የጥንቃቄ እርምጃዎችን መወሰን አይችልም።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ የተመሳሳይነት (analogy) ጉዳይ ሲሆን በህግ ላይ ከተደነገጉት ወንጀሎች ጋር ይመሳሰላል በማለት ወንጀልነቱ በግልፅ ያልተደነገገን ድርጊት ወይም ግድፈት እንደወንጀል ሊቆጠር እንደማይችል የወንጀል ህጉ አንቀጽ 2(3) ይደነግጋል።

2. የወንጀል ሕግ ወደኋላ ተመልሶ የማይሰራ መሆኑ (Non-Retroactivity of Criminal Law)

በዚህ መርህ መሰረት ህግ ሊተገበር ወይም ሊፈፀም የሚችለው ህጉ ከፀደቀ በኋላ በተፈፀሙ ድርጊቶች ላይ ነው። ይህ ማለት አዲስ ህግ ሲወጣ ህጉ ከመውጣቱ በፊት የተፈፀሙት ድርጊቶች በአዲሱ ህግ ወንጀል መሆናቸው ቢደነገግም ለበፊቱ ድርጊት ተፈፃሚ አይሆንም። አንድ ሕግ የዜጎችን መብትና ግዴታ የሚወስን በመሆኑ ሰዎች ሕጉ እስከሚለወጥ ድረስ ድርጊቶቻቸውን ወይም ግንኙነታቸውን ሕጉ በሚፈቅደው ወሰን ውስጥ ያካሂዳሉ፡፡ አንድን ሁኔታ የሚለውጥ ወይም የሚያሻሻል ሕግ ቢወጣ ሕጉ ተፈፃሚ መሆን ያለበት ቢያንስ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ ወደፊት መሆን አለበት፡፡

ይህ መርህ በወንጀል ህግ አንቀፅ 5 እና በህገ መንግስቱ አንቀፅ 22 ስር ተደንግጎ ይገኛል። በዚሁ መሰረት በአዲሱ ወይም በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ እና በተሻረው የወንጀል ህግ እንደወንጀል የተቆጠረ ድርጊት የተፈፀመው አዲሱ ህግ ከመፅናቱ በፊት ከሆነ፣ ጉዳዩ የሚታየው በተሻረው የወንጀል ህግ መሰረት ነው። ድርጊቱ በአዲሱ ህግ መሰረት ወንጀል ሆኖ በተሻረው ህግ ግን እንደወንጀል ካልተቆጠረና የተፈፀመው አዲሱ ህግ ከመፅናቱ በፊት ከሆነ ሊያስቀጣ አይችልም። እንዲሁም የተሻረው ህግ ይሰራ በነበረበት ጊዜ የተፈፀመ ወንጀል ሲኖር በአዲሱ ህግ ግን እንደወንጀል ያልተቆጠረ ሲሆን ሊያስከስስም ሆነ ሊያስቀጣ አይችልም፤ ክሱም ተጀምሮ እንደሆነ እንደሚቋረጥ በወንጀል ህጉ ተደንግጓል።

የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ሄዶ አይሰራም ሲባል በመሰረታዊ ሕጉ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤቶችን ያስከትላል፡፡ አንደኛው አንድ ድርጊት በሚፈፀምበት ጊዜ ድርጊቱ በጊዜው የማያስቀጣ ከነበረ ይኸው ድርጊት ከጊዜ በኋላ በወጣ ሕግ ወንጀል ነው ሊባል አይችልም፡፡ ሁለተኛው ድርጊቱ በተፈፀመበት ወቅት ወንጀል ቢሆንም እንኳን ወንጀለኛው መቀጣት ያለበት ድርጊቱ በተፈፀመበት ወቅት ተፈፃሚነት የነበረው የወንጀል ሕግ በደነገገው ጣሪያ መሆን አለበት የሚሉ ናቸው፡፡ ስለዚህም ከድርጊቱ በኋላ የወጣው ሕግ የቅጣት ጣሪያውን ከፍ ቢያደርገው ይህ ቅጣት ሕጉ ከመታወጁ በፊት ለተፈፀመ ወንጀል ተፈፃሚ መሆን የለበትም፡፡ ይሁንና አዲሱ ህግ ለተከሳሹ ወይም ለተቀጣው ሰው የሚጠቅም በሆነ ጊዜ ከድርጊቱ ኋላ የወጣው ህግ ተፈፃሚነት እንደሚኖረው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 22(3) ይደነግጋል። በተጨማሪ በወንጀል ህጉ አንቀፅ 6 ስር እንደተደነገገው አዲሱ የወንጀል ህግ እንዲፀና ከተደረገ በኋላ አድራጊው ህጉ ከመፅናቱ በፊት ላደረገው ወንጀል ሲፈረድበት፣ ወንጀሉን በፈፀመበት ጊዜ በሥራ ላይ ከነበረው ሕግ ይልቅ ይሄኛው ሕግ ቅጣት የሚያቀልለት ሲሆን በአዲሱ ህግ ላይ የተመለከተው ቅጣት ይፈፀምበታል።

3. ለአንድ ጥፋት አንድ ቅጣት መርህ (Principle of Double Jeopardy)

የዚህ መርህ መሰረታዊ ሀሳብ ሰው በአንድ የወንጀል ድርጊት ክስ ቀርቦበት የመጨረሻ በሆነ ውሣኔ ጥፋተኝነቱ ተረጋግጦ በተቀጣበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና መከሰስና መቀጣት የለበትም የሚለው ነው፡፡ በዚህ መርህ ላይ አግባብነት ያላቸው የሕገ-መንግስቱና የወንጀል ሕጉ ድንጋጌዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 23 “ማንኛውም ሰው በወንጀል ሕግና ሥነ-ሥርዓት መሰረት ተከሶ የመጨረሻ በሆነ ውሳኔ ጥፋተኝነቱ በተረጋገጠበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና አይከሰስም ወይም አይቀጣም” በማለት ሲደነግግ የወንጀል ሕጉም በአንቀፅ 2(5) ስር “ማንም ሰው በሕግ መሰረት የመጨረሻ በሆነ ውሳኔ ጥፋተኝነቱ ተረጋግጦ ከዚህ ቀደም በተቀጣበት ወይም ሌላ ሕጋዊ እርምጃ በተወሰደበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና አይከሰስም ወይም አይቀጣም” በማለት ደንግጓል፡፡

4. የእኩልነት መርህ (Principle of Equality)

የእኩልነት መብት ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ከሚመነጩ እና ከማይገረሰሱ አለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች አንዱ ነው። ሰዎች ሁሉ በህግ ፊት እኩል ናቸው የሚለው መርህ የመጣውም ከዚሁ የእኩልነት መብት ነው። በህገ መንግስቱ አንቀፅ 25 ስር እንደተደነገገው ሁሉም ሰዎች በህግ ፊት እኩል ናቸው፤ በመካከላቸውም ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ሳይደረግ በህግ እኩል ጥበቃ ይደረግላቸዋል። በመሆኑም በዘር፣ በብሄር፣ ብሄረሰብ፣ በቀለም፣ በፆታ፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት፣ በፖለቲካ፣ በማህበራዊ አመጣጥ፣ በሀብት፣ በትውልድ ወይም በሌላ አቋም ምክንያት ልዩነት ሳይደረግ ሰዎች ሁሉ እኩልና ተጨባጭ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው ተደንግጓል። የወንጀል ህጉ አንቀጽ 4 ይህንን መርህ በተመሳሳይ ሁኔታ ያስቀመጠ ሲሆን በወንጀል አድራጊዎች መሐከል ልዩነት የሚደረገው ምንጩ የአለም አቀፍ ህግ ወይም ህገ መንግስት ሆኖ በወንጀል ህጉ የተደነገገ መሰረታዊ መብት ሲኖር ወይም የወንጀሉ ከባድነት፣ የጥፋቱ ደረጃ ወይም የአድራጊው ዕድሜ፣ ሁኔታ ወይም ልዩ ግላዊ ጠባዩ ወይም ወንጀሉ በሕብረተሰብ ላይ ያስከተለው አደጋ ከግምት ውስጥ እንዲገባ ህጉ ሲደነግግ እንደሆነ ያስቀምጣል።

ከላይ ከተዘረዘሩት የወንጀል ህግ መርሆች በተጨማሪ ሁሉም ተጠርጣሪዎች እና ተከሳሾች ጥፋተኝነታቸው እስኪረጋገጥ ድረስ ንፁህ ሆነው የመገመት (Presumption of innocence)፣ ዝም የማለት መብት (the right to remain silent) እና ሌሎችም የተያዙ እና የተከሰሱ ሰዎች መብቶች በህገ መንግስቱ ተደንግገው ይገኛሉ።

ማጠቃለያ

በህገ መንግስቱም ሆነ በወንጀል ህጉ የተመለከቱ የወንጀል ህግ መርሆች ከላይ የተብራሩት ሲሆኑ ህግ አስከባሪ አካላት የወንጀል ምርመራ እና ክርክር ሥራዎችን ሲያከናውኑ እነዚህን የወንጀል ህጉን መርሆች በጥብቅ መከተል ይጠበቅባቸዋል፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

በሚኒስትሮች ምክር ቤት በ25/7/16ዓ.ም የጸደቀዉ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ያካተታቸውን ኣዳዲስ ነገሮች  ከታክሱ ነፃ የተደረጉ ዝርዝር አቅርቦቶች፣ ከታክሱ ነጻ ሆነዉ ወደ ሀገር እንዲገ...
05/04/2024

በሚኒስትሮች ምክር ቤት በ25/7/16ዓ.ም የጸደቀዉ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ያካተታቸውን ኣዳዲስ ነገሮች ከታክሱ ነፃ የተደረጉ ዝርዝር አቅርቦቶች፣ ከታክሱ ነጻ ሆነዉ ወደ ሀገር እንዲገቡ የተፈቀደላቸዉ እቃዎች እንደሚከተለው ተጠቅሰዋል።

20/03/2024

ሰ/መ/ቁ. 184371 /ያልታተመ/
***
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 106560 መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ/ም በዋለው ችሎት እና በሰበር መዝገብ ቁጥር 116583 ታህሳስ 4 ቀን 2008 ዓ/ም በዋለው ችሎት ከመሬት ይዞታ ክርክር ልዩ ባህር እና ጉዳዩን በተለይ የሚገዛው ከአዋጅ ቁጥር 25/1988 በኋላ የወጣው ልዩ ሕግ አዋጅ ቁጥር 456/1997 መሠረት የተከራካሪ ወገኖች መደበኛ ነዋሪነት የተለያየ ቢሆንም/ባይሆንም የተከራካሪዎቹ ማንነት ከግምት ውስጥ ሳይገባ የገጠር መሬት ይዞታን በተመለከተ የሚነሱ ክርክሮችን በመጀመሪያ ደረጃ የማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የገጠር መሬት ይዞታው የሚገኝበት ክልል የገጠር መሬት አዋጅ በሚደነግገው መሰረት መሆኑን አገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል።
በመሆኑም ተከራካሪዎቹ ነዋሪነታቸው በተለያየ ክልል መሆኑ ጉዳዩን የፌዴራል ጉዳይ አያደርገውም ።

21/02/2024

በወንጀል ጉዳይ የሚጠረጠሩ ሰዎች በብዛት የሚዘነጉትና የማይረዱት ጉዳይ በተጠረጠሩበት የወንጀል ክስ ተቃውሞ አላቹ ወይ? የሚለውን የፍርድ ቤት ጥያቄ ነው።
የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 130
የወንጀል መቃወሚያዎች ማለት ተጠርጣሪው፦
#1ኛ. በዚሁ ነገር ክስ በሌላ ፍርድ ቤት ተጀምሮ በቀጠሮ ላይ ያለ ከሆነ ወይም፤
#2ኛ. በዚሁ ክስ ከዚህ ቀደም ተከሶ ነፃ የወጣ ወይም የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠበት ከነበረ፤
#3ኛ. ክስ የቀረበበት ወንጀል በይርጋ ሕግ የታገደ ወይም ምሕረት ወይም የአዋጅ ምሕረት (ይቅርታ) የተደረገለት ከሆነ፤
#4ኛ. ከሌሎች ወንጀለኞች ጋራ በተከሰሰ ጊዜና ለብቻው ከሌሎቹ ተነጥሎ ክስ ባይታይለት የሚጎዳው መሆኑን፤
#5ኛ. ክሱን ለማቅረብ በሕጉ መሠረት ፈቃድ ያልተሰጠ መሆኑን፤
#6ኛ. በሌላው ችሎት የቀረበው ክስ ሳይፈጸም በዚህ የወንጀል ክስ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ መሆኑን፤
#7ኛ.ለፈጸማቸው ተግባር ኃላፊ አለመሆኑን በማንሳት የቀረበበትን ክስ መቃወም ይችላል።
መች ይቀርባል?
#ተጠርጣሪው ያለውን መቃውሚያ ፍርድ ቤቱ የክስ አቤቱታውን እንዳነበበለት ወዲያውኑ ካልተቃወመ በስተቀር ቆይቶ ሊያነሳ አይችልም።
#በክርክር ሂደት መቃወም የሚቻለው መቃወሚያው የሚጸና ፍርድ ከመሰጠት የሚያግድ በሆነ ጊዜ ብቻ ነው።

#ጠበቃና የህግ አማካሪ

Address

Addis Ababa
Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bereket Markos Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share