21/04/2026
የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወራት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀምን ከማዕከል ከመጡ አስተባባርዎች ጋር ገመገመ።
****
መድረኩን የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት ሀላፍ ወ/ሮ ፋስካ ህርቦራ እና ሀዋሳ ከተማ ገ/ባ/ዋና ቅ/ጽ/ቤት ግብር ህጎች አስተባባር አቶ አበበ አልቶ የመሩት ሲሆን በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተከናወኑ የመንግስት ስራዎች ሪፖርት በጽ/ቤቱ ቀርቦ በዝርዝር ተገምግሟል።
መደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ እና ሌሎችም የገብና የመንግስት ስራዎች በትኩረት ውይይት የተደረጉባቸው አጀንዳዎች ናቸው ።
በመጨረሻም በውይይቱ በጉድለት የተለዩትን ቆጥሮ በመያዝ ፈጥኖ ማረምና ጥንካሬውን ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል ።
በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ገ/ባ/ዋ/ቅ/ጽ ቤት ከአቶ አበበ አልቶ ጋር የምመሩ እና የሀይቅ ዳር ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት ማነጅሜንት ተሳትፈዋል ።
የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባ/ቅ/ጽ/ቤት
ሀዋሳ
ሚያዝያ 13/08/2018ዓ/ም