ሀይቅ ዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Hawassa
  • ሀይቅ ዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት

ሀይቅ ዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት ገቢ ለሀገር ልማት ብልጽግና 🌇🛣️🏥📚

የሀዘን መግለጫ😭😭😭ወ/ሮ ሮማን ሮባ፣ በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ገቢዎች ባለሥልጣን ባለሙያ ሆና በትጋትና በታማኝነት ሕዝብን ስታገለግል የነበረችው፣ ባደረባት ሕመም ስትታከም ቆይታ በቀን 17/...
23/08/2026

የሀዘን መግለጫ😭😭😭

ወ/ሮ ሮማን ሮባ፣ በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ገቢዎች ባለሥልጣን ባለሙያ ሆና በትጋትና በታማኝነት ሕዝብን ስታገለግል የነበረችው፣ ባደረባት ሕመም ስትታከም ቆይታ በቀን 17/12/2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።

የወ/ሮ ሮማን ሮባ ሞት በእጅጉ አሳዝኖናል። ለቤተሰቦቿ፣ ለዘመድ አዝማዶቿ፣ ለጓደኞቿ፣ እንዲሁም አብረዋት ለሰሩ የሥራ ባልደረቦቿና ለሚያውቋት ሁሉ ከልብ የመነጨ የሀዘን መግለጫችንን እናቀርባለን።

የቀብር ሥነ-ሥርዓቷም ነገ የሚፈጸም መሆኑን በሀዘን እናሳውቃለን።

በዚህ አስከፊ የሀዘን ጊዜ እግዚአብሔር ለቤተሰቦቿና ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን ይስጥ። ነፍሷን በሰላም ያኑርልን።

እግዚአብሔር ነፍሷን በሰላም ያኑር።

«ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ሀሳብ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተካሄደዛሬ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ «ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ሀሳብ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር...
03/08/2026

«ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ሀሳብ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተካሄደ

ዛሬ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ «ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ሀሳብ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተካሄደ።

በመርሀ ግብሩ የክፍለ ከተማው አመራርና ህዝብ በጋራ በመሳተፍ ችግኞችን ተክለዋል። በዚሁ ወቅት የክፍለ ከተማው አስተዳደር አቶ ታጁዲን እንድርስ ህብረተሰቡ የአረንጓዴ ልማትን በጋራ በማስፋፋት ለተሻለ አካባቢ ጥበቃ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ገብዎች ባ/ቅ/ጽ/ቤት
27/11/18ዓ.ም

ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2019 ዓ.ም የግብር ዘመን በይፋ ተከፈተየ2019 ዓ.ም የግብር ዘመን በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ በይፋ ተከፍቶ፣ ...
08/07/2026

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2019 ዓ.ም የግብር ዘመን በይፋ ተከፈተ
የ2019 ዓ.ም የግብር ዘመን በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ በይፋ ተከፍቶ፣ ግብራቸውን በቀዳሚነት ለመክፈል ከሌሊቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ የተገኙ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የማበረታቻ ሰርተፍኬት ተሸልመዋል።
የማበረታቻ ሰርተፍኬቶቹን የክፍለ ከተማው አስተዳዳሪ አቶ ታጁድን እንድርስ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማሀርሁን መኮንን በጋራ ለተሸላሚዎቹ አበርክተዋል። ይህም ግብራቸውን በወቅቱ ለሚከፍሉ ግብር ከፋዮች እውቅና እና ማበረታቻ ለመስጠት የተደረገ ተነሳሽነት መሆኑ ተገልጿል።
በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የተናገሩት አቶ ታጁድን እንድርስ፣ ግብር ለሀገር ልማት፣ ለመሠረተ ልማት ግንባታ እና ለሕዝብ አገልግሎቶች መሻሻል ወሳኝ ምንጭ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሁሉም ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በዚሁ መልኩ የ2019 ዓ.ም የግብር ዘመን የመክፈቻ ፕሮግራም በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ በስኬት ተጠናቋል።

ሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት
01/11/18 ዓ.ም
ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 ዓ.ም የገብ ንቅናቄ መድረክ ተካሄደበሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 ዓ.ም የገብ ንቅናቄ...
07/07/2026

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 ዓ.ም የገብ ንቅናቄ መድረክ ተካሄደ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 ዓ.ም የገብ ንቅናቄ መድረክ በተለያዩ የመንግስት አመራሮች፣ ነጋዴዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

የንቅናቄውን መድረክ የክፍለ ከተማው አስተዳዳሪ አቶ ታጁዲን እንድሪስ እና የገቢ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፋስካ ህርቦራ በጋራ መርተውታል። በመድረኩም የ2018/2019 ዓ.ም የገብ ንቅናቄ ሰነድ በአቶ አየለ በጠና ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተካሂዶበታል።

በውይይቱ ወቅት የገቢ ማሰባሰብ ስርዓትን ለማጠናከር፣ የግብር ህግ ተገዢነትን ለማሳደግ እና የመንግስት ገቢን በማሳደግ ለአካባቢው ልማት የሚያስፈልጉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሀሳብ ተለዋውጧል።

በመጨረሻም የክ/ከተማ አመራሮች፣ነጋዴዎች፣ በቀበሌ አመራሮች እና በሌሎች ተሳታፊዎች የተገኙበት አስተያት ሀሳብ ተሰቶ የገብ ንቅናቄ መድረክ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ተሳታፊዎችም የመንግስት ገቢን ለማሳደግ እና የግብር ሥርዓቱን ለማጠናከር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።.

ሀዋሳ 30/10/18 ዓ.ም

በሀዋሳ ከተማ ሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 የግብር ዘመን ለመጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸበሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ...
06/07/2026

በሀዋሳ ከተማ ሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የ2018/2019 የግብር ዘመን ለመጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፋስካ ህርቦራ፣ የ2018/2019 የግብር ዘመን ከሀምሌ 1 ጀምሮ በይፋ እንደሚጀመር በመግለጽ፣ ለዚህም የሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ኃላፊዋ እንዳሉት፣ የአዲሱን የግብር ዘመን በተሳካ ሁኔታ ለመጀመር የግብር ከፋዮችን የማሳወቅና የማስገንዘብ ሥራ፣ የመረጃ ማደራጀት፣ የሰራተኞች ዝግጁነት እንዲሁም አገልግሎትን በተቀላጠፈ መንገድ ለመስጠት የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች በትኩረት እየተፈጸሙ ነው።

ወ/ሮ ፋስካ አክለውም፣ ሁሉም ግብር ከፋዮች የግብር ግዴታቸውን በወቅቱ በመወጣት ለሀገር ልማትና ለመንግስት የአገልግሎት ሥራዎች መጠናከር የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም የገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት ሙሉ ዝግጅት ማድረጉን በመግለጽ፣ የግብር ከፋዮችም በወቅቱ በመቅረብ የሚጠበቅባቸውን ግዴታ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወራት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀምን ከማዕከል ከመጡ አስተባባርዎች ጋር ገመገመ።****መድረኩን የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ...
21/04/2026

የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወራት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀምን ከማዕከል ከመጡ አስተባባርዎች ጋር ገመገመ።
****
መድረኩን የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት ሀላፍ ወ/ሮ ፋስካ ህርቦራ እና ሀዋሳ ከተማ ገ/ባ/ዋና ቅ/ጽ/ቤት ግብር ህጎች አስተባባር አቶ አበበ አልቶ የመሩት ሲሆን በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተከናወኑ የመንግስት ስራዎች ሪፖርት በጽ/ቤቱ ቀርቦ በዝርዝር ተገምግሟል።

መደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ እና ሌሎችም የገብና የመንግስት ስራዎች በትኩረት ውይይት የተደረጉባቸው አጀንዳዎች ናቸው ።

በመጨረሻም በውይይቱ በጉድለት የተለዩትን ቆጥሮ በመያዝ ፈጥኖ ማረምና ጥንካሬውን ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል ።

በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ገ/ባ/ዋ/ቅ/ጽ ቤት ከአቶ አበበ አልቶ ጋር የምመሩ እና የሀይቅ ዳር ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት ማነጅሜንት ተሳትፈዋል ።

የሐይቅዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባ/ቅ/ጽ/ቤት
ሀዋሳ
‎ ሚያዝያ 13/08/2018ዓ/ም

Address

Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀይቅ ዳር ክ/ከተማ ገብዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category