Dire Dawa University School of Law

Dire Dawa University School of Law This is Dire Dawa University School of Law official face book page.

የእንኳን ደስ አላችው መልክት ከድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም===================================ሀገራችን ኢትዮጲያ በተፈጥሮ ፀጋዎቿ የታደለች እንዲሁም ...
09/09/2025

የእንኳን ደስ አላችው መልክት ከድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም
===================================
ሀገራችን ኢትዮጲያ በተፈጥሮ ፀጋዎቿ የታደለች እንዲሁም በተለያዩ መልክአ ምድሮቿ እና ህብረ ብሔራዊ ህዝቦች ያጌጠች፣ ታሪክ በተለያየ ኩነቶች የሚዘክራት፣ ቅኝ ገዢዎችን አሳፍራ ቅኝ ሳትገዛ የኖረች፣ የመላው አፍሪካውያን የነፃነት ቀንዲል ጥንታዊ የሰው ዘር መገኛ ውብ ሀገር ናት፡፡

ሀገራችን ያላትን ፀጋ ለመቀራመት ቅኝ ገዢዎች ቢያማትሩም የአንድነታችንን ክንድ መቋቋም ተስኗቸው አፍረው ተመልሰዋል፡፡ ፊት ለፊት ገጥመው አንበርክከው ሊመዘብሯት ያልቻሉትን ሀገራችንን ውስጣዊ አንድነታችንን በማዳከም መንግስታት ከልማት ይልቅ የእለት ችግሮቻችን ላይ ተጠመደው እንዲከርሙ በማድረግ ሀገራችን ከልማቱም ከሰላሙም እንዳትሆን ብዙ ለፍተዋል፡፡ ድህነት እና ኋላቀርነት መገለጫችን ሆኖ በአለም መድረክ እስኪነገር ኢትዮጲያ አቀርቅራ ቆይታለች፡፡

ዛሬ ግን ያ የቁዘማ ዘመን ያ በራስ ሀብት እና ፀጋ የመሸማቀቅ ታሪክ ዳግሞ ላይመለስ ተቀይሯል፡፡ ኢትዮጲያዊያን አንድነታቸውን አፅንተው፣ ከእለት ጉርሳቸው ቀንሰው ለዘመናት የህዝባችን ጥያቄ የነበረውን የመልማት ፍላጎት እና የአባይ ወንዝ እንቆቅልሽ በተባበረ ክንድ መላሽ ሰጥተዋል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የእውነትም በህዝባችን ጥረት እና ድካም እውን ሆኗል።

ውድ ኢትዮጵያዊያን፦ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጲያ የማንሰራራት ምልክት፤ የለውጥ ጉዞ እና የታሪክ እጥፋት ጅማሮ ማብሰሪያ ነው፡፡ ግድቡ ውሃ ብቻ ሳይሆን ሉአላዊነታችን ላይ ለሚቃጡ ትንኮሳዎችም ልጓም የሚያበጅ ኃይል ነው፡፡ ኢትዮጲያዊያን እናቶች በእንጨት ለቀማ የሚደክሙት ድካም፣ የሚያባክኑት ጊዜ እና ጉልበት ከእንግዲህ አይኖርም። በኤሌክትሪክ ሀይል እጥረት ኢንዱስትሪዎቻችን ስራ አይፈቱም፣ በጋራ ተጠቃሚነት እና አብሮ የመልማት መርህ የህዳሴው ግድብ ከሀገራችን አልፎ ለጎረቤት ሀገራትም ጭምር በረከት ይዞ መጥቷል።

ውድ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ገና ከጅምሩ አንስቶ በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግ፣ በሀገር አቀፍ ሚዲያዎች ቀርባችሁ የተሳሳተ ትርክቶችን በመሞገት፣ ከእለት ጉርሳችሁ ሳይቀር ቀንሳችሁ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ህዝባዊ ንቅናቄዎችን ጭምር በማስተባበር ላበረከታችሁት አስተዋፅኦ፣ ላኖራችሁት ታሪካዊ አሻራ በራሴ እና በዩኒቨርሲቲያችን ስም እያመሰገንኩ በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እላለሁ።

ዶ/ር ኡባህ አደም

04/09/2025

This is the official face book page of Dire Dawa University College of Law. Follow the page for more information and updates.

02/09/2025
🚨 Notice 🚨This page with 11K followers is not the official page of Dire Dawa University College of Law. It is run by for...
02/09/2025

🚨 Notice 🚨
This page with 11K followers is not the official page of Dire Dawa University College of Law. It is run by former members and does not represent the College.
👉 For official updates, follow this page only.

Official NoticeThis page with 11K followers is no longer the official page of Dire Dawa University College of L...
02/09/2025

Official Notice

This page with 11K followers is no longer the official page of Dire Dawa University College of Law. It is currently being monitored and managed by its previous owners, who are no longer members of the College.

Therefore, any posts, comments, or content shared here do not and will not represent the former Dire Dawa University College of Law, nor the current Dire Dawa University School of Law.

The only official page of the Dire Dawa University School of Law is the one where this notice is being posted. For authentic updates, announcements, and events, please follow the official page only.

Address

Dire Dawa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa University School of Law posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category