22/06/2025
የግል እይታ
📝📝📝📝📝
""""""""""""ሕጉ ምን ይላል""""""""""""
የፍትሐብሔር ክስ ይግባኝ ይርጋ ዉሳኔ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ እስከ 60 ቀን እንደሆነ ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 323(2) ይገልፃል
እንድሁም የወንጀል ክስ ይርጋም 30ቀን እንደሆነ ይታወቃል
ይሁን እንጂ ከ 70%በላይ(በራሴ ግምት ነው ጥናት ያስፈልጋል) ይግባኞች ለይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት የሚቀርቡት 1ቀን ወይም ቢበዛ 2ቀን እየቀረ ነው:: በዚሁ ልክ ግዜ አልፎ የማይቀርቡም ሊኖሩ እንደምችሉ ግምት መውሰድ ይቻላል::
ታዲያ ለዚህ ሁሉ መዘግየት
{ከአብዛኛ ባለጉዳዮች እንዳጣራነው}
👉የሥር ፍርድ ቤት ሬጅስትራር ይግባኙን በጊዜ ኮፒ አድርጎ ያለመሸኘት እንደሆነ ይናገራሉ
👉ይግባኙም በሸኝ ደብዳቤ ላይ የሚያስረዳው በግዜ እንዳልተሸኙ ነው
👉ኮፒ ተደርገው የተሸኝኑትም ቢሆኑ ግልፅ ያልሆነና የማይነበብ ኮፒ ይሰጣችዋል
በዚህ ምክንያት ለብዙ መመላለስና መንገላታት እስከ መብት ማጣት ድረስ እያደረሰ ፍትህ ፈላጊ ማህበረሰብ ፍትህ እያጣ ይገኛል::
ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ
ቸል ሳይባል አፋጣኝ ጥናት ተደርጎ መፍትሄ ብፈለግ የፍትህ ትራንስፎርመ ሽን እቅድ ለማሳካት ጉልህ ምና አለው እላለሁ::
"""""""""""""""""""""""""""""""
በሳሙኤል ተሰማ (LLB,LLM)
Attorney