Cheta Woreda Communication

Cheta Woreda Communication Cheta woreda communication

የካፍቾ ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ" በዓል የእስካሁን የስራ አፈፃፀምና በቀር ስራዎች ዙሪያ ከበዓሉ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተደረገ። በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት 2019 ...
26/08/2026

የካፍቾ ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ" በዓል የእስካሁን የስራ አፈፃፀምና በቀር ስራዎች ዙሪያ ከበዓሉ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተደረገ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት 2019 ዓ/ም በሚከበረው የካፍቾ ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ" በዓል የእስካሁን ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ከኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

ውይይቱን የመሩት የወረዳ ምክትል አስተዳደርና ሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው የሳምንታት ዕድሜ ብቻ ለቀረው የካፍቾ ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ" በዓል ኮሚቴዎች በትኩረትና በፍጥነት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

በዓሉን በዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የተለያዩ ጥናታዊ ጹሑፎችን በማቅረብ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው በማለት ለውጤታማነቱ የባለድርሻ አካላቶች ርብርብ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።

አቶ ከተማ የሀብት አሰባሰብ ስራን ለማጠናከር በተሰራው ስራ ከወረዳ አመራር ጀምሮ ሁሉም መሳተፋቸውን ጠቁመው በማመስገን ያልተሳተፉ አካላቶችም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፍ ወ/ሮ አበባሽ አበበ ባህል የአንድ አካባቢን ማህበረሰብ ማንነትና የአኗኗር ሂደትን አጉልቶ ከማሳየት እረገድ የማይተካ ሚና የሚጫወት ነው በማለት በየግዜው ይህ ማንነት ደምቆ እንዲታይ ባለመታከት ለትውልድ የሚያስተላልፉ ኮሚቴዎች ልመሰገኑ ይገባል ብለዋል።

በዓሉ ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ በድምቀት እንዲከበርና የተሟላ የእንግዳ አቀባበል እንዲኖር የደመቀ የፌስቲቫልና የካርኒቫል ቅድመ ዝግጅት እንዲኖር አሳስበዋል።

የወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሸሻ መኩሪያ የእስካሁን የስራ አፈፃፀም ባቀረቡበት ወቅት የመንግስት ስራተኞችን ጨምሮ ሁሉንም ማህበራዊ መሰረት በማሳተፍ 1ሚልዮን 1መቶ 29ሽህ 5መቶ 70ብር መሰብሰብ ተችሏል ብልዋል።

በሀብት አሰባሰብ ስራ ላይ የሀይማኖት ተቋማቶችን ጨምሮ ሁሉም አካላቶች መሳተፋቸውን በማስታወስ የባለቤትነትና የእኔነት ስሜት በማህበረሰቡ ውስጥ መኖሩን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የበዓሉ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎችም በቀረቡ የእስካሁን የስራ አፈፃፀሞች ላይ በመነጋገር በአጭር ግዜ ውስጥ ቀሩ የተባሉ ስራዎችን ቆጥረው በመስራት ስኬታማ በዓል ለማክበር የድርሻውን እንደሚወጡ አሳውቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

ሻወራሻ ወልደሚካኤል ዳጫቾ ፡- የዕድሜ ፀጋ  በረጅም የታሪክ ምዕራፍ ያሻገራቸው ታላቅ  ታሪክ በሰነድ ብቻ ሳይሆን በሰዎች ሕያው ትዝታም ጭምር ይጻፋል፦ በካፋ ዞን ሺሾ እንዴ ወረዳ ኦማ ሾን...
25/08/2026

ሻወራሻ ወልደሚካኤል ዳጫቾ ፡- የዕድሜ ፀጋ በረጅም የታሪክ ምዕራፍ ያሻገራቸው ታላቅ

ታሪክ በሰነድ ብቻ ሳይሆን በሰዎች ሕያው ትዝታም ጭምር ይጻፋል፦ በካፋ ዞን ሺሾ እንዴ ወረዳ ኦማ ሾንጋ ቀበሌ የሚገኙት አዛውንቱ ሻወራሻ ወልደሚካኤል የዚህ የዘመን ዥረት እና የሕይወት መዘክር ማሳያ ናቸው።

ታሪካዊ መረጃዎችን መሠረት አድርጎ ሲሰላ ሻወራሻ ቢያንስ ከ 125 እስከ 135 ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳላቸው በግልጽ መረጃዉ የሚያመላክት ሲሆን፤ ከቤተሰባቸው እና ከአካባቢው ማህበረሰብ የሚነሱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ ግን ዕድሜያቸው ከ 156 እስከ 180 ዓመት ይደርሳል ተብሎ ይገመታል።

ሻወራሻ የካፋው ንጉሥ ጪንቶ ጋሊቶ ለአጼ ምኒልክ ሰራዊት እጅ ከሰጡበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሰማኒያዎቹ አስተዳደር መረብ መዘርጋት ድረስ ያሉትን ታሪካዊ ክስተቶች አውቃለሁ በማለት በግልጽ ያስረዳሉ።

ከዚህም በተጨማሪ የባሪያ ንግድ የነበረበትን አሰቃቂ ጨለማ ዘመን እና ተያያዥ ጉዳዮችን ማወቃቸዉ እንዲሁም በፈረንጆቹ 1936 (በኢትዮጵያ 1928 ዓ.ም) የማይጨው ጦርነት ላይ ለወደቁት ጀግኖች በካፋ ባህል የተደረገውን የለቅሶ ሥርዓትና የካፋን ጦር መርተው የወጡትን የራስ ጌታቸው አባተን ስም እያነሱ የሚተርኩት ትዝታ ከየትኛውም የዘመን መለኪያ በላይ እጅግ የረጅም ዘመን ባለጸጋ መሆናቸውን ይመሰክራል።

ዛሬ ላይ በወረዳው የሚገኘው አሁን ያለው ትውልድ ሁሉ ከእሳቸው ዕድሜ በብዙ ዓመታት ርቀት ወደ ታች ስለመሆኑና በእድሜ አቻ ሊሆናቸው የሚችል ማንም የሌለ ፍጹም የዘመን ጥንታዊ አባት አድርጓቸዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በጊነስ ወርልድ ሪኮርድ ከተመዘገቡት የዕድሜ ባለጸጎች አንጻር ሲታይ፤ በታሪክ በሰነድ ተረጋግጦ ረጅሙን ዕድሜ ኖራለች የተባለችው ፈረንሳዊቷ ጂን ካልመንት (122 ዓመት ከ164 ቀን) ስትሆን፣ በአሁኑ ወቅት በህይወት ካሉት ደግሞ እንግሊዛዊቷ ኤቴል ካተርሃም በ117 ዓመቷ ትገኛለች።

ከሻወራሻ ታሪካዊ መነሻዎችና ከቤተሰብ አባላት ማስረጃዎች አንጻር ሲታየ ግን፣ ሻወራሻ ከእነዚህ ዓለም አቀፍ የዕድሜ ባለጸጎች ጋር በእጅጉ የሚወዳደሩ ወይም የሚበልጡ የዘመን ክስተት ባለቤት መሆናቸውን በጉልህ ያሳያል።

ሻወራሻ ወልደሚካኤል ዳጫቾ በረጅም ዘመን የህይወት ጉዟቸው ውስጥ ትልቅና ግዙፍ ማህበራዊ ቤተሰብ ማፍራት ችለዋል።

ከዚህ በፊት ከነበሩትና አሁን በህይወት ካሉት ጋር በድምሩ 9 የትዳር ሕይወትን አሳልፈዋል።
ከልጆች እስከ ቅምጥል ልጅ ልጆች ድረስ እስከ 150 የሚደርሱ የቤተሰብ አባላትን ማፍራት ችለዋል።

ለእኚህ የዕድሜ ባለጸጋ ታሪክና ሕይወት ትኩረት እንዲሰጠው አበክረው ላሳሰቡት ለካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንደሻው ከበደ ልባዊ ምስጋና ይገባቸዋል።

በተለይም የሺሾንዴ ወረዳ አስተዳደር በገጠር አካባቢ ተመራጭ የሆነውን ሶላር ለአዛውንቱ ገዝቶ በማቅረብና ለሌሎችም ተከታታይ ድጋፎችም እንደዚሁ።

ባለታሪካችን ሻወራሻ እንደሚሉት ከሆነ፤ ለዚህ የዕድሜ ባለጸጋነት ማዕረግ የሚያበቃው ዋናው ነገር «ፈሪሃ እግዚአብሔር እና ንጹህ አእምሮ» ነው።
አዛዉነቱ ዛሬም ድረስ መላው ካፋ፣ ህዝቡ እና መሬቱ ጭምር የተባረከ እንዲሆን ዘወትር እያደረጉት ላለው ልመናና ጸሎት የካፋ ቴሌቪዥን የከበረ አክብሮቱን ያቀርባል ስሉ የካፋ ማህበረሰብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ዘግቧል።

በሻማ ማዘጋጃ አዲስ የከተማ ቀበሌ መዋቅራዊ አደረጃጀት ተቋቋመ። በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ሻማ ማዘጋጃ ሻማ01 የከተማ ቀበሌ መዋቅራዊ አደረጃጀት ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል። የወረዳ ምክር ቤት ዋ...
25/08/2026

በሻማ ማዘጋጃ አዲስ የከተማ ቀበሌ መዋቅራዊ አደረጃጀት ተቋቋመ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ሻማ ማዘጋጃ ሻማ01 የከተማ ቀበሌ መዋቅራዊ አደረጃጀት ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል።

የወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አጦ ወ/ስላሴ የተከበሩ አቶ ብርሃኑ ከበደና የተከበሩ አቶ ፈጠነ ታመነ የሻማ 01 ቀበሌ ምክር ቤት ዋና እና ምክትል አፈ ጉባኤ በመሆን እንዲያገለግሉ የሰየሙ ስሆን ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

የተከበሩ አቶ አጦ ወ/ስላሴ አክለው ከዚህ በፊት 21የገጠር ቀበሌዎች መኖራቸውን በመናገር በአሁን ወቅት በወረዳ ደረጃ ሁለት ተጨማሪ የከተማ ቀበሌዎችን ማዋቀር መቻሉን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል አቶ አምባው ኃይሌ የሻማ 01 ቀበሌ አስተዳዳሪ ሆነው በመሾም አቶ ደግቶ ወዲሞ፣ አቶ መንግስቱ ማሞ መቹሎ፣ አቶ ባህሩ ደጎ፣ ቆጭቶ ወ/ስላሴና ገበየሁ ገ/ዮሃንስ የቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤት ሁነው እንዲያገለግሉ ለምክር ቤት አቅርበዋል።

የሻማ 01 ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ አምባው ኃይሌ ለአካባቢያችን እድገትና ለውጥ በአንድነት መስራት ይጠበቅብናል ስሉ ጠይቀዋል።

የሻማ ማዘጋጃ ቤታዊ ስራአስኪያጅ አቶ አሸብር ገ/ማርያም የከተማችንን እድገት ለማፋጠን በትኩረት እየተሰራ ነው በማለት የከተማ ቀበሌ መዋቅሮችን ማጠናከር ለፈጣን እድገት መሰረት ነው ብለዋል።

ሻማ 01 ቀበሌ መቋቋሙ የህዝብን በቅርበት የመገልገል ፍላጎት የሚመልስ እንደሆነ በመናገር መሰረተ ልማቶችን ለማምጣትና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያችል እንደሆነ ጠቁመዋል።

በሁሉም ስራዎች ሞዴል በመሆን ከተሞች ለሌሎች አርዓያ መሆን ይጠበቅባቸዋል ያሉት ስራ አስከያጅ የአደረጃጀቶች መጠናከር ለሁሉም መስክ ውጤታማነት ለማስመዝገብ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል።

ሻማ 01 የከተማ ቀበሌ 12ጣቢያዎችን በማቀፍ የተዋቀሩ እንደሆነ በማከል የሰፈሮች ተጠሪነት ለጣቢያ እንደሆነና ጣቢያዎችም ተጠሪነታቸው ለከተማ ቀበሌ እንደሆነ አስረድተዋል።

የወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መንግስቱ ኃይሌ በበኩላቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ አደረጃጀቱ ለከተማችን እድገት አንድ እርምጃ ከፍታ የሚፈጥር እንደሆነ አሳውቀዋል።

ወረዳውን በጤና ሞዴል ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ነው በማለት ይህ አደረጃጀት ከተሞችን በሁሉም ተልዕኮዎች አካባቢያችንን ሞዴል ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም አስተዳዳሪው ከተማችንን ለማዘመንና የተሻለች ለማድረግ ተቀራርቦ መስራት ያስፈልጋል በማለት የተሰሩ ልማቶችን የመጠበቅና የተሻሉ የልማት እድሎች መፍጠር ከሁላችንም የሚጠበቅ ነው ብለዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

አፈሳ እየተደረገ ነው የሚባሉ መረጃዎች ከእውነት የራቁና ሀሰተኛ መረጃዎች እንደሆኑ ረዳት ኢንስፔክተር አንዳርጌ ደራ ተናገሩ።በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ውስጥ ከሰሞኑ ወጣቶች ላይ አፈሳ እየተደረገ...
25/08/2026

አፈሳ እየተደረገ ነው የሚባሉ መረጃዎች ከእውነት የራቁና ሀሰተኛ መረጃዎች እንደሆኑ ረዳት ኢንስፔክተር አንዳርጌ ደራ ተናገሩ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ውስጥ ከሰሞኑ ወጣቶች ላይ አፈሳ እየተደረገ ነው እየተባለ የሚናፈሱ መረጃዎች ከእውነት የራቁና ሀሰተኛ መረጃዎች እንደሆኑ የወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አንዳርጌ ደራ ተናግረዋል።

ወረዳችን ማንም በሰላም ወጥቶ የሚገባባት እና ፍፁም ሰላማዊ እንደሆነች የተናገሩት አዛዡ ይሄንን ሰላም ለማናጋት እና አለመረጋጋትን ለመፍጠር ከሰሞኑ ትክክል ያልሆኑ መረጃዎች እየወጡ ነው ብለዋል።

ፖሊስ የአካባቢን ሰላም ለማስፈንና የህብረተሰቡን ሰላም ለማስጠበቅ ከፀጥታ አካላቶች ጋር በመቀናጀት ከመቸውም ግዜ በላይ በንቃት እየሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።

የወረዳችን ወጣቶች ሰራ ወዳድና በየተሰማሩበት የስራ መስክ እምርታን እያስመዘገቡ የሚገኙ እንዲሁም ከፀጥታ አካላቶች ጋር በትብብር የሚሰሩ ናቸው ያሉት ረዳት ኢንስፔክተሩ በተሰማራበት ሁሉ ስኬታ ስራዎች ሰርቶ እንዳይኖር ያልተረጋገጡ ወሬዎች እየወጡ እንደሆኑ ጠቁመዋል።

ማህበራዊ ሚዲያዎችን ተጠቅሞም ሆነ በሌላ መንገድ አላስፈላጊ መረጃዎችን በማሰራጨት የህዝብን ሰላም የሚነሱ አካላቶች ላይ ሕጋዊ እርምጃዎችን ለመወሰድ እየተሰራ እንደሆነ በማሳወቅ የተሳሳቱ መረጃዎች የሚያሰራጩ አካላቶችም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የእስካሁን የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀምን አስመለክቶ የዞን ትምህርት መምሪያ ድጋፍ ባለሙያዎች ከትምህርት ማኔጅመንት አካላቶች ጋር ውይይት አደረጉ።በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የ20...
25/08/2026

የእስካሁን የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀምን አስመለክቶ የዞን ትምህርት መምሪያ ድጋፍ ባለሙያዎች ከትምህርት ማኔጅመንት አካላቶች ጋር ውይይት አደረጉ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የ2019 ዓ/ም የእስካሁን የተማሪዎች ምዝገባ ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ የዞን ትምህርት መምሪያ ድጋፍ ባለሙያዎች ከትምህርት ማኔጅመንት አካላቶች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱን የመሩት ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ ገበየሁ እድሜው ለትምህርት የደረሰ ማንኛውም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዲሆን የመርሱ አባላትን ከመመደብ ጀምሮ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።

በሁሉም ትምህርት ቤቶች ትምህርት ማስጀመሪያ ንቅናቄ ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱን ያስታወሱት ኃላፊው ውጤታማ የሆነ ምዝገባ እንዲኖር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የትምህርት ጽ/ቤት የመረጃ ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ታዬ ታርኩ በእስካሁን የተማሪዎች ምዝገባ ዙሪያ መነሻ ሰነድ አቅርበዋል።

በወረዳ ደረጃ የቅድመ አንደኛ ተማሪዎች ምዝገባን አስመለክቶ 4ሽህ 4መቶ 63ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ 8መቶ 40ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልፀው በተመሳሳይ እስካሁን በቅድመ መደበኛ 27 በመቶ መመዝገብ መቻሉን አሳውቀዋል።

ምዝገባው በታቀደለት ግዜ እንዳይገፋ የመምህራን እጥረት፣ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤት መዘግየትና ይፋ አለመሆን፣ የኔትወርክ መቆራረጥ፣ የባለድርሻ አካላቶች ትኩረት ማነስ ተግዳሮት መሆኑን በማንሳት የሰው ኃይል ማሟላትን ጨምሮ ድጋፎች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።

የተማሪዎች ምዝገባ ሂደት በአጭር ግዜ ለመጨረሻ በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ድጋፍ ባለሙያዎች አሳውቀዋል።

እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ተማሪዎች በየትምህርት ቤቶች እየቀረቡ እንዲመዘገቡ ከመርሱ አካላት በተጨማሪ የቤተሰቦችና አሳዳጊዎች ሚና የጎላ ነው በማለት ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የተመራ የፌደራል ሱፐርቪዥንና ክትትል ቡድን በክልሉ በክረምት በጎ አገልግሎት የተከናወኑ ስራዎች አፈጻጸምን ገመገመከፌደራል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች...
24/08/2026

በኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የተመራ የፌደራል ሱፐርቪዥንና ክትትል ቡድን በክልሉ በክረምት በጎ አገልግሎት የተከናወኑ ስራዎች አፈጻጸምን ገመገመ

ከፌደራል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚንስቴር እና ከባለድርሻ ተቋማት የተወጣጡ የሱፐርቪዥንና ክትትል ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የክረምት በጎ አገልግሎት የእስካሁኑን አፈጻጸም በቦንጋ ገምግሟል።

ዓላማውም በዕቅዱ መሠረት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ወርደው በመመልከት ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ለክልሉ ግብረ መልስ መስጠት፤ ተሞክሮ ካሉ መቀመርና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ያለመ ነው።

በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የሚንስተሩ አማካሪና የሴቶች ማብቃት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን አስፋው፤ ክትትሉ የዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍን በተናበበ እና በተቀናጀ መልክ ከመምራት እስከ ተግባር ምዕራፍ በአግባቡ የተመራ ስለመሆኑ ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

የበጎ ተግባር ዓላማው የማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር የመንግስት ወጪን በመቀነስ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንዳለው የገለጹት አቶ ሰለሞን፤ ይህ ውጤታማ የሚሆነው በተቀመጠው የአሰራር ስርዓት በቅንጅት ሲሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የክረምት በጎ አገልግሎት የእስካሁኑ የአፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ብልጽግና ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ ግርማ ባሻ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በክልሉ በ14 ዋና ዋና የስምርት ዘርፎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ የተነሳ ሲሆን በበጀት ዓመቱ 1.5 ሚሊየን በጎ ፍቃደኞችን በማሳተፍ 1.5 ቢሊየን ሀብት በማሰባሰብ 2.5 ሚለየን የህብረተሰብ ክፍልን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ አቶ ግርማ ገልጸዋል።

በአረንጓዴ አሻራ በችግኝ ተከላና እንክብካቤ በክልሉ 134 ችግኝ በመትከል 580 ሚለየን ብር በላይ ሀብቱን ማትረፉ መቻሉ ነው የተገለጸው።

የደም ልገሣ ባህል ከዐጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን በማንሳት ከታቀደው 2500 ዩኒት ደም 1744 የዕቅዱ 70% መከናወኑ ተገልጿል።

ከአረጋውያንና አቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ በሚመለከት 650 አዳዲስ ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ 271 መከናወኑ፤ ከዚህ ውስጥ 22 በብሎከት መሆኑ ተጠቅሷል።

በትምህርት ዘርፍ 701 በጎ ፍቃደኞችን በማሳተፍ ከ18ሺ በላይ ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ተጠቃሚ በማድረግ ከ1.6 ሚለየን ብር በላይ የሚተመን ከወጪ ማዳኑ ተገልጿል።

237 አዲስ የመማሪያ ክፍል ግንባታ እንዲሁም 2013 ደርዘን ደብተርና 3274 ፓኬት ስክብርቶ ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት ማሰባሰብ መቻሉ በሪፖርቱ ላይ ተነስቷል።

በአጠቃላይ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሁሉም ዘርፎች ተሳትፎና የስራ ስምርት፤ የዜጎች ተጠቃሚነት እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እያደገ መምጣቱ አቶ ግርማ በሪፖርቱ ላይ አንስተዋል።

በውይይቱ ላይ በጥንካሬና በጉድለት የተነሱ ጉዳዮችን በጥልቀት ተሳታፊዎቹ በመገምገም አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን የሱፐርቪዥንና ክትትል ቡድኑ በካፋ ዞን በተመረጡ ወረዳዎች የመስክ ምልከታ በማድረግ ለክልሉ ግብረ መልስ እንደሚሰጥ ተጠቁሟል ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨታ ቅርንጫፍ ባለሙያዎች ለማዕድ ማጋራት በተከፈተው የሀብት ማሰባሰቢያ አካውንት ላይ የስድስት ሽህ ብር ድጋፍ አደረጉ።ድጋፍ የሚሹና ጠያቂ የሌላቸው ወገኖችን በበዓል ...
24/08/2026

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨታ ቅርንጫፍ ባለሙያዎች ለማዕድ ማጋራት በተከፈተው የሀብት ማሰባሰቢያ አካውንት ላይ የስድስት ሽህ ብር ድጋፍ አደረጉ።

ድጋፍ የሚሹና ጠያቂ የሌላቸው ወገኖችን በበዓል ለማዕድ ለማጋራት ታስበው በተከፈተው የሀብት ማሰባሰቢያ አካውንት ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨታ ቅርንጫፍ ባለሙያዎች ስድሰት ሽህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።

ካለን ላይ በማካፈል ለተቸገሩ ወገኖች በማንችለው ሁሉ አቅም እንሁንላቸው መደጋገፍና እርህራሄ ባህላችን ይሁን።

የክረምት በጎ አድራጎት ሀብት ማሰባሰቢያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000780758329 ስሆን https://www.facebook.com/elias.galo.75 የፎቶ መረጃ በዚህ መስፈንጠሪያ ይላኩልን።

የወረዳ መንግስትና የሀብት አሰባሰብ ኮሚቴ ልባዊ ምስጋናውን እያደረሰ ሌሎች አካላቶችንም የበኩላችሁን እንዲትወጡ ስል በአክብሮት ይጠይቃል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

ያዶታ  ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 39  ሰልጣኞችን እያስመረቀ ነው።በካፋ  ዞን ሳይለም ወረዳ የያዶታ  ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ ለመጀመሪ...
23/08/2026

ያዶታ ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 39 ሰልጣኞችን እያስመረቀ ነው።

በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ የያዶታ ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ዙር ከደረጃ 1 እስከ 4 በመደበኛ መርሀ ግብር በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 39 ሰልጣኞችን አያስመረቀ ነው ስል የወረዳ ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

4ቱን የገጠር ቀበሌዎች የሚያማክል የገበያ ማዕከልና የመንገድ ከፈታ ስራ በኦጃ ቀበሌ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ።በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የዘመናት የህዝብ ጥያቄ ከነበሩት አንዱ የኮራ ክላስተር ...
22/08/2026

4ቱን የገጠር ቀበሌዎች የሚያማክል የገበያ ማዕከልና የመንገድ ከፈታ ስራ በኦጃ ቀበሌ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የዘመናት የህዝብ ጥያቄ ከነበሩት አንዱ የኮራ ክላስተር የገበያና የከተማ ጥያቄዎችን ለመመለስ ዘርፍ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

የእስካሁን የስራ እንቅስቃሴዎችን በመመልከት ንግግር ያደረጉት የወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ 4ቱን የገጠር ቀበሌዎች የሚያገናኝ የገበያ ማዕከልና የመንገድ ከፈታ ስራ በኦጃ ቀበሌ እየተከናወነ እንደሆነ ተናግረዋል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ ከመቸውም ግዜ በላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት አስተዳዳሪው ተግባሩ የኮራ ክላስተር ነዋሪዎች እና የወረዳ ህዝብ የመልማት ጥያቄን የሚመልስ ነው ብለዋል።

ስኬች ፕላንን መሠረት ያደረገ የመንገድ ከፈታና ጥገና ስራ እንዲሁም የገበያ ቦታ ማስፋፊያ ስራን ለማጠናከር የወረዳ መንግስት ማሽን በመከራየት እየሰራ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን የህብረተሰብ ድጋፍና ርብርብ እንዲታከል ጠይቀዋል።

ሌሎች የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ በመጠቆም የአካባቢ ማህበረሰብም የተፈጠረውን ዕድል ወደ ውጤት እንዲቀይር አሳስበዋል።

የወረዳ ብልፅግና ፓርት ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ዘውዴ በበኩላቸው ሰው ተኮር የሆነው ብልፅግና ፓርቲ የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

እየለማ የሚገኘው የኦጃ ከተማ የዴቻ ወረዳ ቀበሌዎችን ጨምሮ በዙሪያው የሚገኙ አካባቢዎችን በማቀፍ ተጨማሪ የግብይት ማዕከልና የኢኮኖሚ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።

ከፓርቲያችን ኢኒሼቲቭ አንዱ የሆነው የገጠር ኮሪደርና የጤና ሞዴል መንደር ግንባታ ስራ በማጠናከር አካባቢን ፅዱ የማድረግ ስራ በክላስተሩ ላይ እንዲበረታታ በመጠየቅ ኢኒሼቲቩ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ለመቀየር የጎላ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል።

በመጨረሻም አቶ ሰለሞን የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ በማስጠበቅ ተመራጭና ተፈላጊ ገበያ እንዲሆን ሁሉም የቀበሌ ነዋሪዎች በቅንጅት እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

በወረዳ አስተባባሪዎችና አመራሮች፣ የቀበሌ አመራሮችና የሀገር ሽማግሌዎች ጨምሮ በርካታ አካላት ተገኝተዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ፣ ተዓማኒ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል - ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴሩ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል ፡፡በዘንድሮ የ 12 ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 96...
22/08/2026

12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል - ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴሩ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል ፡፡

በዘንድሮ የ 12 ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።

ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።

Address

Kafa Cheta
Bonga

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Cheta Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share