Beteህግ

Beteህግ ህግ ፅሁፎችን ማጋራት

19/06/2026

እንኳን አደረሳችሁ!! ቅዱስ ሚካኤል በያላችሁበት ከክፉ ነገር ይጠብቃችሁ!!!!
ሰኔ ሚካኤል(2018ዓ.ም)

15/06/2026

''የብዙ ሟች ቤተሰቦችን ማግኘት አልተቻለም'' 🚨 ⚠️ አስቸኳይ መልዕክት፡ #ሸር ይደረግ! ⚠️ የሟቾች ቤተሰቦችን ማግኘት ባለመቻሉ አስቸኳይ እገዛ ይፈለጋል። 🚨''

ዛሬ ማለዳ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም በደሴ እና ኮምቦልቻ መካከል በሚገኘው ''ሀረጎ'' መንገድ ላይ በደረሰ የመኪና አደጋ የ31 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ነው።

የሟቾች አስክሬን ደሴና ከምቦልቻ ሆስፒታሎች የሚገኝ ሲሆን ''በዚህ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ብዙ ሰዎች መታወቂያ እና ማንነታቸውን የሚገልፅ መረጃ ባለመኖሩ'' አስከሬን ለማስረከብም ሆነ ሁኔታውን ለማሳወቅና የቤተሰቦቻቸውን አድራሻ ማግኘት ከባድ ሆኗል ተብሏል።

አደጋ የደረሰበት ''አውቶቡስ ሰኔ 07/2018 ዓ.ም መነሻው ከቦረና መካነ-ሰላም ከተማ እንደሆነም የተገለፀ ሲሆን'' ይህ መልዕክት ለሚመለከታቸው ቤተሰቦች በፍጥነት እንዲደርስ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ።

በተላይ ከመካነ-ሰላም ወደ አድስ አበባ የተጓዘ የቤተሰብ አካል ካለና አድራሻው የጠፋባችሁ ወይም የምታውቁት ሰው ካለ መረጃዎችን በማመሳከር እንድትተባበሩና መረጃው ለሌላቸው ደግሞ ይህንን ፅሁፍ በየግሩፑ እና በየገጻችሁ በማድረግ አግዙ።

የአንድ ሰው ''ሼር'' ማድረግ ለአንድ ቤተሰብ መጽናኛና መረጃ ሊሆን ይችላል።

ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለተጎጅ ቤተሰቦችም መጽናናትን እንመኛለን!

15/06/2026

ነፍስ ይማር!!

15/06/2026

የረዥም ዘመን የባህል ሙዚቃ አምባሳደሩ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ — በሀገራችን የባህል ሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂነትን ያተረፈውና በብዙሃን ዘንድ ሰሜ ባላገሩ"እየተባለ በሚጠራው ተወዳጁ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን።

ባደረበት የድንገተኛ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ የቆየው ድምጻዊው፣ በተወለደ በዛሬው ዕለት (ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም) በተደረገለት የህክምና ክትትል ህይወቱ ማለፉን የቅርብ ቤተሰቦቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያን ባህል፣ ወግና ታሪክ የሚያንጸባርቁ በርካታ የሙዚቃ ስራዎችን ለአድማጮች ያበረከተው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው፣ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ የራሱን ደማቅ አሻራ ጥሎ ማለፍ የቻለ ከያኒ ነበር።

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ከቤተሰቦቹ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የኪነ-ጥበብ አድናቂዎቹ በሙሉ መጽናናትንና ብርታትን ይመኛል።

ፈጣሪ ነፍሱን በገነት ያኑራት!

🌴🌴🌴

15/06/2026

ጭነት ይዞ ጠፍቶብናል
የመኪናው ሰሌዳ ኮድ3- A38432 ተሳቢው ኮድ 3-41262 የሆነ ተሳቢ ተሽከርካሪ ከዳንሻ ማሽላ በ 27/09/2018 ዓም ጭኖ የሄደ ቢሆንም እስካሁን ሰአት ድረስ አድራሻውን አጥፍቶብናል አሁን ላይ ጭነቱን አዳማ ላይ ሸጦ ወደ ሌላ መኪና መገልበጡን ሰምተናል ይህንን ተሽከርካሪ ያያችሁ በትጠቁሙን ወረታ ከፋይ ነን በማለት መልዕክት አድርሰውናል

+251 91 457 3354

14/06/2026

መናገር አይችሉም መንገድ ላይ ወድቀው የተገኙ ካህን ናቸው

እኒሁ አባታችን ደቡብ ጎንደር ፋርጣ ወርዳ ልዩ ስሙ ጎርጓ እየሱስ ከሚባለው ቦታ ወድቀው የተገኙ ሲሆን በመጀመሪያው ቀን ሰኔ 5/10/2018 ወደቀው የተገኙ ሲሆን...

የት ነዎት ሲባሉ የተናገሩት ቃል ከጋሸና በላይ ዳውንት ነው ስሜ ቄስ ጣፋጤ ይባላል የሚል ቃል ሰጥቷል ።

ሌላ መታወቂያ የላቸውም መናገር አልቻሉም ስለዚህ የአባታችን ቤተሰቦች እንዲደረሳቸው #ሼር በማድርግ እንተባበራቸው ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን ።

የምታውቋቸው ከሆነ ወይም ተጨማሪ መረጃ ከፈለጋችሁ በዚህ ስልክ 0910228738 እንድደውሉልን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን ። መረጃውን በማጋራት ሼር በማድረግ ቤተሰቦቻቸው እናገናቸው እኛም ከዚህ በረከት እንሳተፍ🙏

Via፦ Fekede Asnake

ግዮን ማለዳ

13/06/2026

ሰበር !

በአሜሪካ እና ኢራን መካከል የሚደረገው ስምምነት ነገ እሁድ ይፈረማል ፤ ፊርማውን ተከትሎ የሆርሙዝ ሰርጥ ወዲያውኑ ለሁሉም ክፍት ይኾናል ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መግለፃቸውን White House ይፉ አድርጓል።

BREAKING:
According to White House, President Donald Trump has announced that the Deal between his country and Iran is scheduled to get signed tomorrow, and immediately after it is signed, the Hormuz Strait is OPEN TO ALL.

13/06/2026

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ። ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
BBC Amharic

በጣም ያሳዝናል!!!
02/06/2026

በጣም ያሳዝናል!!!

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Beteህግ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category