06/06/2019
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት
ዝክረ-ሕግ
ZIKRE-HIG
OF THE COUNCIL OF THE AMHARA NATIONAL REGIONAL STATE IN THE FEDERAL DEMOCRATIC REPUBLIC OF ETHIOPIA
ማውጫ
ደንብ ቁጥር 150/2009 ዓ/ም
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ አሰጣጥና የተገነቡ ቤቶች ድልድል ማስፈፀሚያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ CONTENTS
Regulation No. 150/2017
The Amhara National Regional State Teachers’ Dwelling Houses’ Construction Land Provision and the Distribution of Constructed Houses Ex*****on, Council of Regional Government Regulation
ደንብ ቁጥር 150/2009 ዓ/ም
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ አሰጣጥና የተገነቡ ቤቶች ድልድልን ለማስፈፀም የወጣ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ Regulation No. 150/2017
A COUNCIL OF REGIONAL GOVERNMENT REGULATION ISSUED TO PROVIDE FOR THE EX*****ON OF THE TEACHERS’ DWELLING HOUSES’ CONSTRUCTION LAND DELIVERY AND THE DISTRIBUTION OF CONSTRUCTED HOUSES IN THE AMHARA NATIONAL REGIONAL STATE
የመምህርነት ሙያ ዜጎችን በተገቢው እውቀት፣ ክህሎት፣ ቀና አመለካከትና በጎ እሴት የመቅረጽ ሀላፊነት ያለበት ከመሆኑም በላይ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወትና የህዳሴውን ጉዞ ለማሳካት የበኩሉን ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት እንደሆነ በመታመኑ Whereas, it is believed that the teaching profession would, far from entailing a responsibility to shape citizens with the appropriate knowledge, skills, fair attitude and good values, play a pivotal role for the multi-faceted development of our country and henceforth contribute its significant share to the successful accomplishment of the renaissance voyage;
የየደረጃውን መምህራን የመኖሪያና የመስሪያ አካባቢ የተመቻቸ በማድረግ ለአገር እድገት የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ግዴታ በተነቃቃ መንፈስ መወጣት ይቻላቸው ዘንድ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተረጋጋ ስምሪት የሚኖርበትንና በዚህም አማካኝነት ጥራት ያለው ትምህርት የሚሰጥበትን እድል መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ Whereas, it has been found necessary to create an opportunity in which the stabilized deployment of teachers shall exist and hence quality education shall be provided in all the localities of the region by facilitating their residential and working environment at all levels so that they would be able to discharge their professional duties in an activated spirit for the country’s development;
በሙያው የሰለጠኑና ብቃት ያላቸው የክልሉ መምህራን ከጊዜ ወደጊዜ ሙያቸውን እየተዉ ወደ ሌሎች የስራ መስኮች የሚያደርጉትን ፍልሰት ለመቀነስ ይቻል ዘንድ የመጠለያ ችግር በግል ሂወታቸው ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ተጽእኖ በማስቀረትና ማህበራዊም ሆኑ ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን ከወዲሁ በማቃለል ቤተሰቦቻቸውና መላው ህብረተሰብ ለሙያው አዎንታዊ አመለካከት ኖሯቸው የየበኩላቸውን ድጋፍና እንክብካቤ እንዲያደርጉላቸው የሚያበረታታ ራሱን የቻለ የህግ ማእቀፍ አውጥቶ ገቢራዊ ማድረግ በማስፈለጉ፤ Whereas, in order that it might be possible to minimize the turn-over of those professionally trained and competent teachers in the region fleeing from their respective fields of profession in favor of other sectoral occupations from time to time, it is essential to enact and implement an autonomous legal framework that would somehow encourage their families and the society as a whole to provide them with their own support and care having thus developed a positive attitude for the profession in question, by getting rid of the problem which the lack of shelter happens to create in respect of their private lives and thereby alleviating their social and economic difficulties therewith;
የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተሻሻለው የብሔራዊ ክልሉ ህገ-መንግስት አንቀጽ 58 ንዑስ አንቀፅ (7)ና በክልሉ አስፈጻሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያ፣ ማደራጃና ስልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 230/2008 ዓ.ም አንቀጽ 37 ድንጋጌዎች ስር በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይህንን ደንብ አውጥቷል፡፡ NOW, THEREFORE, the Council of the Amhara Regional Government, in accordance with the powers vested in it under the provisions of Art. 58 Sub-Art. (7) of the Revised National Regional Constitution and Art. 37 of the Revised Regional Executive Organs’ Re-establishment, Organization and Definition of their Powers and Duties Proclamation No. 230/2015, hereby issues this regulation.
ክፍል አንድ PART ONE
ጠቅላላ ድንጋጌዎች GENERAL PROVISIONS
1. አጭር ርዕስ 1. Short title
ይህ ደንብ “የመምህራን መኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ አሰጣጥና የተገነቡ ቤቶች ድልድል ማስፈጸሚያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 150/2009 ዓ.ም” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ This Regulation may be cited as “The Teachers’ Dwelling Houses’ Construction Land Delivery and the Distribution of Constructed Houses Ex*****on, Council of Regional Government Regulation No. 150/2017”.
2. ትርጓሜ 2. Definitions
1. የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ ደንብ ውስጥ፡- 1. Unless the context requires otherwise, in this regulation:-
ሀ. “መምህር” ማለት በክልሉ ውስጥ በሚገኝና ንብረትነቱ የመንግስት በሆነ ከቅድመ-መደበኛ እስከመሰናዶ 2ኛ ደረጃ ባለ ትምህርት ቤት፣ የመምህራን ትምህርት፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት፣ የግብርና፣ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ወይም የአካል ተሃድሶ ማሰልጠኛ ወይም የአገልግሎት መስጫ ማእከል አስተማሪ ወይም አሰልጣኝ በመሆን በቋሚነት ተቀጥሮ በሙያው የሚያገለግል ማንኛውም ሰው ሲሆን፤ ርእሳነ-መምህራንን፣ ምክትል ርዕሳነ-መምህራንን፣ ሱፐርቫይዘሮችን፣ የየኮሌጆቹን ወይም የየማእከላቱን ዲኖች፣ ዳይሬክተሮችና ምክትሎቻቸውን ይጨምራል፡፡ A. “Teacher” shall mean any person who has been permanently recruited and serves in his profession as a teacher or trainer from pre-school through preparatory secondary level school, teachers’ education, technical and vocational education, agriculture or health science college or physical rehabilitation training or service delivery center found in the regional state and belongs to the government and may include principals, deputy principals, supervisors of such schools, deans, directors and their deputies of each and every college or center thereof.
ለ. “ትምህርት ቤት” ማለት በክልሉ ውስጥ ተቋቁሞ በመንግስት ይዞታ ስር የሚተዳደር ከቅድመ-መደበኛ እስከ መሰናዶ 2ኛ ደረጃ ያለ ማናቸውም ትምህርት ቤት ሲሆን የመምህራን ትምህርት፣ የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና፣ እንዲሁም የግብርና፣ የጤና ሳይንስ ኮሌጆችንና የአካል ተሃድሶ ማሰልጠኛ ወይም የአገልግሎት መስጫ ማእከላትን ይጨምራል፡፡ B. “School” shall mean any school set up in the Regional State and managed under the government ownership from preschool through preparatory secondary-level and include teachers’ education, technical-vocational education and training, agriculture and health science colleges as well as physical rehabilitation training or service delivery centers.
ሐ. “የመምህራን መኖሪያ መንደር” ማለት ህጋዊ ባለቤትነቱ የክልሉ መንግስትና ህዝብ የሆነና የመምህራንን የመጠለያ ችግር ለመፍታት ታስቦ በመንግስት ወይም በመንግስትና በህብረተ-ሰቡ የጋራ ተሳትፎ የሚገነቡ ሆነው መምህራን በማስተማር ስራቸው ላይ እስካሉ ድረስ የሚጠቀሙባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያረፉበት ስፍራ ነው፡፡ C. “Teachers’ Residential Village” shall mean a place whose lawful ownership is to the Regional Government and people and wherein condominiums to be constructed either by the government or through the joint participation of the government and the community with the intention of resolving teachers’ shelter problem and used by teachers as long as they stay in their teaching career, are situated.
መ. “መኖሪያ ቦታ” ማለት በራሳቸው ምርጫ ገንብተው የሚጠቀሙበትን ቤት ለመስራት የሚያስችላቸውና በክልሉ መንግስት አማካኝነት በምደባ፣ በነፃ ወይም ካሳ ተከፍሎበትና በይፋ ተፈቅዶ ለመምህራን የተሰጠ ቦታነው፡፡ D. “Dwelling land” shall mean that plot of land which has been granted to teachers by the Regional Government, upon its official approval, through allotment, free of charge or payment of compensation thereon and enables teachers to construct a house they would use, having built it with their own preference.
ሠ. “ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልገው መምህር“ ማለት በፌደራሉ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የስራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 568/2000 ዓ.ም አንቀጽ 2 ንኡስ አንቀፅ (1) ድንጋጌ ስር የሚሸፈንና በሜዲካል ቦርድ የተረጋገጠለት አካል ጉዳተኛ ሆኖ የጉዳቱ ደረጃ በእኩል የስራ እድል ተጠቃሚነት መብቱ ላይ ተጽእኖ የሚያስከትልበት መሆኑ በአስፈጻሚ ኮሚቴው የታመነበት ማንኛውም መምህር ነው፡፡ E. “Teacher Needing Special Support” shall mean any teacher who is physically disabled and covered under the provision of Art. 2, Sub-Art. (1) of the Federal Government Physically Disabled Persons’ Right to Employment Proclamation No.568/2008 and whose status has been established by a medical board and henceforth believed by the executive committee that the extent of his disability would cause an impact on his right to benefit from equal opportunity for employment. .
ረ. (ንዑስ ማዘጋጃ-ቤት) ወይም (ታዳጊ ከተማ) ማለት እንደቅደም ተከተላቸው በአንድ መሪ ማዘጋጃ-ቤት ስር የተዋቀረ ከባቢያዊ የከተማ ማህበረ-ሰብ ወይም ማዘጋጃ-ቤት ያልተቋቋመበት ሆኖ ወደ ከተማነት በመሸጋገር ላይ ያለ ማናቸውም የማህበረ-ሰብ ስብስብ ነው፡፡ F. (Sub-municipality) or (Emerging town) shall mean a local urban community structured under a certain lead municipality or any communal group that is found in a condition of emergence into a status of a town, wherein no municipality has not been established, in order of their priorities.
ሰ. “መሪ ማዘጋጃ-ቤት” ማለት በአንድ ወረዳ ውስጥ የሚገኙትን ንዑሳን ማዘጋጃ-ቤቶችና ታዳጊ ከተሞች በማእከልነት ይዞ ስራቸውን እንዲያስተባብርና በበላይነት እንዲመራ ሀላፊነት የተሰጠው ማዘጋጃ-ቤት ነው፡፡ G. “Lead Municipality” shall mean a municipality which embraces those sub-municipalities and emerging towns found in a Woreda and is thus vested with the responsibility of coordinating and directing over their respective duties thereof.
ሸ. “አነስተኛ የከተማ አስተዳደር” ማለት በቀበሌዎች የተከፋፈለ ሆኖ ከወረዳ ተለይቶ የራሱ ውስጣዊ አስተዳደር ያለው ማናቸውም ከተማ ነው፡፡ H. “Smaller City Administration” shall mean any city which has been categorized into Kebeles and acquired its own internal administration, having broken away from the Woreda thereof.
ቀ. “መካከለኛ የከተማ አስተዳደር” ማለት በአነስተኛና በሜትሮፖሊታን የከተማ አስተዳደሮች መካከል ያለ ማናቸውም የከተማ አስተዳደር ሲሆን የዞን አስተዳደር ማዕከላትን ይጨምራል፡፡ I. “Medium City Administration” shall mean any city administration which is found between small and metropolitan city administrations and include the centers of zonal administrations.
በ. “ሜትሮፖሊታን የከተማ አስተዳደር” የሚለው ሀረግ የባህርዳር፣ የጎንደርና የደሴ ከተሞችን ይገልፃል፡፡ J. The term “Metropolitan City Administration” shall refer to those cities of Bahir Dar, Gondar and Dessie.
ተ. “ቢሮ” እና “የቢሮ ኃላፊ” ማለት እንዳግባብነቱ የክልሉ ትምህርት፣ ጤና፣ ከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን፣ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም፣ ግብርና ወይም ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና የዚሁ ቢሮ ኃላፊ ነው፡፡ K. “Bureau and Bureau Head” shall be the Regional Education, Health, Urban Development, Housing and Construction or Rural Land Administration and Use, Agriculture, and Labor and Social Affairs Bureau and the head of such Bureau, as appropriate. .
ቸ. “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፡፡ L. “Person” shall mean any natural or juridical person.
2. በዚህ ደንብ ውስጥ በወንድ ፆታ የተገለፀው ማናቸውም ጉዳይ የሴትንም ፆታ ይጨምራል፡፡ 2. All provisions of this regulation set out in the masculine gender shall also apply to the feminine gender.
3. የተፈጻሚነት ወሰን 3. Scope of Application
ይህ ደንብ ከዚህ በላይ በአንቀጽ (2) ንኡስ አንቀፅ (1) ፊደል ተራ ቁጥሮች ሀ.ና ለ. ስር የተጠቀሱትን የክልሉን መምህራን፣ ትምህርት ቤቶችና ኮሌጆች በሚመለከት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ 1. This regulation shall apply with regard to the region’s teachers, schools and colleges specified under Art. 2 Sub-Art. (1) letter numbers A. and B. herein above.
4. አላማዎች 4. Objectives
ደንቡ የሚከተሉት አላማዎች ይኖሩታል፡- The Regulation shall have the following objectives:
1. መምህራን የተመቻቸ የመኖሪያ አካባቢ ተፈጥሮላቸው ሙያዊ ብቃታቸውንም ሆነ ስነ-ምግባራቸውን እያሳደጉ በስራቸው ላይ በመቆየት የተማሪዎችን ውጤታማነት በቀጣይነት በማሻሻል በክልሉ ውስጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲረጋገጥ ማድረግ፤ 1. Following the creation of favorable living environment for teachers as well as improvement of their professional competence and ethical conduct and retain them in their career, cause the realization of quality education throughout the region by continuously enhancing the performance results of students;
2. መምህራን በተሰማሩበት የስራ መስክ ተረጋግተው በመቆየት የማስተማር ፍላጎታቸውም ሆነ ተነሳሽነታቸው እንዲጨምርና ለመማር-ማስተማሩ ሂደት የበኩላቸውን ገንቢ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማበረታታት፤ 2. By having them maintained in the career they have engaged themselves in, to encourage teachers so that their interest and initiation would be boosted and thereby contribute their own constructive share for the learning-teaching process per’se;
3. ለመምህርነት ሙያ ተገቢውን ክብር በመስጠት ይኸው በተማሪዎችና በህብረተ-ሰቡ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት በማሳደግ የተሻለ እውቀት ያላቸው ዜጎች ወደሙያው እንዲሳቡ ማድረግ፤ 3. To cause those citizens having better knowledge to be attracted into the field by giving appropriate respect to the teaching profession and increasing the acceptance of such by students and the community;
4. የትምህርት ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ የመምህራንና ተማሪዎችን ስነ-ምግባር በማሻሻል በትምህርት ውጤታማነት ላይ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ፤ 4. To cause the bringing about of positive change with regard to the success in education by having properly used the academic duration and improving the ethical conduct of both teachers and students alike;
5. የልዩ ድጋፍ ተጠቃሚ የሆኑ አካል ጉዳተኛ መምህራን በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 41 ንኡስ አንቀፅ (5) ስር የሰፈረውን አላማ በሚያሳካ መንገድ መደገፍ፡፡ 5. To back up those teachers with physical disabilities benefiting from special support in a way as to achieve the objective laid down under Art. 41 Sub-Art. (5) of the Constitution.
ባህር ዳር
የካቲት 17 ቀን 2009 ዓ.ም
ገዱ አንዳርጋቸው
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
ርእሰ-መስተዳድር Done at Bahir
Dar This 24th day of February, 2017
Gedu Andargachew
Head of Government of the Amhara National Regional State