Voice of Sidaama

Voice of Sidaama Sidaama News

 ❗  💥ዉድ የክለባችን ሲዳማ ቡና ደጋፊዎች እንደምታዉቁት ክለባችን ሲዳማ ቡና ሲቢኤ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ አሸንፎ ለድርብ ድል ለኢትዮጵያ ዋንጫ ስኔ 30 እየተጠባበቀ ይገኛል።ሆኖም...
25/06/2026

❗ 💥

ዉድ የክለባችን ሲዳማ ቡና ደጋፊዎች እንደምታዉቁት ክለባችን ሲዳማ ቡና ሲቢኤ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ አሸንፎ ለድርብ ድል ለኢትዮጵያ ዋንጫ ስኔ 30 እየተጠባበቀ ይገኛል።

ሆኖም ይህ ዉጤት እንዲመጣ የክለቡ ደጋፊዎች የከፈሉት ዋጋ ቀላል የሚባል አይደለም። ከእነዛ ልጆች መካከል ወንድማችን ኢዬ ቡኒዬ ደጋፊዎች ክለቡን እንዲደግፉ ባለፉት 15 ዓመት በላይ ለክለቡ ዋጋ ከፍሏል።

ሆኖም ዛሬ ኢዬ ቡኒዬ የራሱ የሆነ ነገር እንዲይዝ መንግስትን ጠይቀን ያለነዉ ጥያቄ ባለበት ሆነዉ.. የክለቡ ደጋፊዎች ከራሳቸዉ ተነሳሽነት የቻሉትን እንዲያደርጉ የ5ቀን ቻሌንጅ❗ጀምረናል።

ሁላችንም በተቻለን መጠን ለኢዬ ቡኒዬ የፍቅር ስጦታ በመስጠት የበኩላችንን እንወጣ።

👉CBE 1000309306566 Eyasu Side Harema

የቡና ቤተሰቦች እና የስፖርት አፍቃሪያን በሙሉ፣ ይህንን መልካም ጥሪ ለሌሎችም በማጋራትና የበኩላችሁን በማበርከት ቻሌንጁን በድምቀት እንቀላቀል☕⚽

Voice of Sidaama

ሰኔ 4 የወጣው የእስር ትዕዛዝ እስከ ሰኔ 18 የት ደረሰ? በሲዳማ ክልል በአደባባይ ሃይማኖትን የሰደበው ግለሰብ አለመያዝ ህዝባዊ ቁጣን ቀስቅሷል !​በሲዳማ ክልል የእስልምና ሃይማኖትን እና...
25/06/2026

ሰኔ 4 የወጣው የእስር ትዕዛዝ እስከ ሰኔ 18 የት ደረሰ? በሲዳማ ክልል በአደባባይ ሃይማኖትን የሰደበው ግለሰብ አለመያዝ ህዝባዊ ቁጣን ቀስቅሷል !

​በሲዳማ ክልል የእስልምና ሃይማኖትን እና አማኞችን በአደባባይ በመሳደብ የተከሰሰው ግለሰብ እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋሉ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታንና መነጋገሪያን እየፈጠረ ይገኛል። በተለይም ግለሰቡን ለመያዝ ሰኔ 4 ቀን የወጣው የአስር ትዕዛዝ እስከ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን ድረስ ተፈፃሚ ሳይሆን ለሁለት ሳምንታት መቆየቱ፣ በክልሉ ያለውን የፍትህ አሰራር ጥያቄ ምልክት ውስጥ ጥሎታል የሚሉ ድምፆች እየበረከቱ ነው።

​የእስልምና እምነት ተከታዮችን እና እምነቱን በአደባባይ በማንቋሸሽ ወንጀል የተጠረጠረውን ይህንን ግለሰብ ለመያዝ የህግ አካላት የሰኔ 4 ቀን የቁጥጥር ስር ማዋል ትዕዛዝ አውጥተው የነበረ ቢሆንም፣ ትዕዛዙ እስካሁን መሬት ላይ አልወረደም። ​ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች እንደሚሉት የፍርድ ቤት እና የህግ አካላት ትዕዛዝ ወጥቶ እያለ ግለሰቡ እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋሉ በክልሉ የህግ የበላይነት ላይ ትልቅ ጥያቄ አስነስቷል። ተከሳሹ ግለሰብ በህግ ጥላ ስር ካለመግባት አልፎ፣ አሁንም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ብቅ እያለ የሙስሊሙን ማህበረሰብ በአደባባይ መሳደብ እና ትንኮሳ ማድረጉን ቀጥሏል።

​ይህ ድርጊት በብዙሃኑ ዘንድ ታላቅ ህዝባዊ ትዝብትንና ቁጣን የፈጠረ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ እንዲህ ያሉ ድርጊቶች በዝምታ መታለፋቸው በአካባቢው ለዘመናት የኖረውን የሃይማኖቶች አብሮ መኖር እና ሰላም አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው። ህግን አለማክበር እና የጥላቻ ንግግሮች በአደባባይ እንዲቀጥሉ መፍቀድ የፍትህ ስርዓቱን ታማኝነት በእጅጉ እንደሚጎዳው እየተገለጸ ይገኛል።

በመጨረሻም ​የክልሉ የፀጥታና የፍትህ አካላት ህግን በማስከበር ረገድ ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳየት እንዳለባቸውና የወጣውን የእስር ትዕዛዝ በአስቸኳይ ተፈፃሚ በማድረግ ተከሳሹን ለህግ ማቅረብ እንደሚገባቸው ማህበረሰቡ በፅኑ እየጠየቀ ይገኛል።



Voice of Sidaama

የሕዝበ ሙስሊሙ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ አገኘ፤ አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ፀደቀ​የሕዝበ ሙስሊሙን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስና የዳኝነት አካሉ...
25/06/2026

የሕዝበ ሙስሊሙ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ አገኘ፤ አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ፀደቀ

​የሕዝበ ሙስሊሙን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስና የዳኝነት አካሉን አደረጃጀት ለማዘመን ሲጠበቅ የነበረው አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ። ይህ አዲስ ሕግ ላለፉት 25 ዓመታት አገልግሎት ላይ የነበረውንና ጊዜው ያለፈበትን የአዋጅ ቁጥር 188/1992 ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።

​የሕጉ መነሻና የዝግጅት ሂደት

የሕግ ማርቀቅ ሥራው የተከናወነው በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥያቄ አቅራቢነት ነው። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ባዋቀሩት ባለ 7 አባላት የዳኞችና የባለሙያዎች ኮሚቴ አማካኝነት የውጭ አገራት ተሞክሮዎችንና የባለድርሻ አካላትን ጠቃሚ ግብዓቶች በማካተት ተዘጋጅቷል። ረቂቁ ለፓርላማው የሕግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከተመራ በኋላም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል።

​የአዲሱ አዋጅ ዋና ዋና ይዘቶች

በሰባት ክፍሎች ተከፋፍሎ በአዲስ መልክ የተዘጋጀው ይህ አዋጅ የሚከተሉትን ወሳኝ ጉዳዮች በዝርዝር ደንግጓል፦

​የፍርድ ቤቶቹን የዳኝነት ሥልጣን፣ አደረጃጀትና አሠራር ማዘመን፣

​የዳኞች አሿሿም ግልጽነትና የበጀት አስተዳደር፣

​የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤን በአዲስ መልክ ማቋቋም።

​ምስጋናና የጋራ ጥሪ

ይህ ታሪካዊ አዋጅ እንዲጸድቅ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ጀምሮ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮች፣ ረቂቁን ያዘጋጁ የኮሚቴ አባላት፣ የፓርላማው የህግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋና ቀርቧል።

​የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ቁመናቸው ተስተካክሎ ለሕዝበ ሙስሊሙ ደረጃውን የጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የተጀመረው የለውጥ ጉዞ ስኬታማ ይሆን ዘንድ የአዋጁ መጽደቅ ብቻውን በቂ ባለመሆኑ፣ የመላው ሕዝበ ሙስሊም ድጋፍና እገዛ እንደሚያስፈልግ ተመልክቷል።

Voice of Sidaama

በሲዳማ ክልል የሚገኙ 417 መስጂዶች የሚሳተፉበት የፍትህ ጥየቃ መርሃ-ግብር ይፋ ተደረገበሲዳማ ክልል የሚኖሩ ሙስሊሞች ሰብአዊና ህገ-መንግስታዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ ለመጠየቅ የሚያስችላቸው...
23/06/2026

በሲዳማ ክልል የሚገኙ 417 መስጂዶች የሚሳተፉበት የፍትህ ጥየቃ መርሃ-ግብር ይፋ ተደረገ

በሲዳማ ክልል የሚኖሩ ሙስሊሞች ሰብአዊና ህገ-መንግስታዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ ለመጠየቅ የሚያስችላቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሰላማዊ መርሃ-ግብር ይፋ ማድረጋቸውን የአስተባባሪ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

​ማህበረሰቡ በክልሉ እያጋጠመው ያለው የፍትህ እጦትና የመብት ረገጣ ከአቅሙ በላይ መሆኑን የገለጸው ኮሚቴው፤ መጅሊስም ሆነ የመንግስት አካላት ችግሩን በሚገባ እንደሚያውቁት ጠቁሟል። በመሆኑም መብትን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ ስልታዊ የቅሬታ ማሰሚያ መርሃ-ግብር ማዘጋጀት ማስገደዱ ተገልጿል።

​እንደ መግለጫው ከሆነ፣ የመጀመሪያው ምዕራፍ መርሃ-ግብር ከፊታችን ሐሙስ ሰኔ 18 ቀን ጀምሮ እስከ ዓርብ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 12:30 ድረስ በተለያዩ መንፈሳዊና ሰላማዊ ተግባራት ይከናወናል።

​የጾም፣ የዱዓ እና የህዝብ ንቅናቄ መርሃ-ግብር

​ሐሙስ ሰኔ 18 ቀን የሚውለውን ዓመታዊውን የዓሹራ (ሙሀረም 10) ዕለት መነሻ በማድረግ፣ መላው የክልሉ ሙስሊም ማህበረሰብ ቀኑን በጾም፣ በሰደቃና በልዩ ዱዓ እንደሚያሳልፍ ተነግሯል። ዕለቱ ነቢዩ ሙሴና ተከታዮቻቸው ከፈርዖን ጭቆና ነፃ የወጡበት ታሪካዊ ቀን በመሆኑ፣ ለፍትህ ጥየቃው ልዩ መንፈሳዊ ጉልበት እንደሚሰጠው ተመላክቷል።

​በማከታተልም ዓርብ (ጁሙአ) ሰኔ 19 ቀን ማህበረሰቡ ተጨማሪ ጾም እንዲጾም የተመከረ ሲሆን፣ በዕለቱ በሚከናወነው የጁሙአ ሰላት ወቅት የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራት እንደሚከናወኑ ኮሚቴው አስታውቋል፦

​ምዕመናን ወደ መስጂድ በጊዜ እንዲገቡ ማድረግ፣

​በክልሉ ሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ያለው የተቀናጀ በደል በዝርዝር ለህዝቡ ማስረዳት፣

​በእያንዳንዱ መስጂድ በሶስት ምሁራን/አባቶች ልዩ ዱዓ ማቅረብ።

​የተቃውሞ መፈክሮች እና የተፈጻሚነት ወሰን

​ከዓርብ ሰላት ማጠቃለያ በኋላ ማህበረሰቡ ወደ መስጂድ ግቢዎች በመውጣት ድምጹን በህብረት እንደሚያሰማ ታውቋል። ምዕመናኑ በጋራ የሚያስተጋቧቸው አራት ዋና ዋና መፈክሮችም፦ «ፍትህ ለሲዳማ ክልል ሙስሊም!!!»፣ «ሲዳማን የሚያስተዳድረው ብልፅግና የተለየ ነውን?»፣ «ከሃይማኖታችን እጃችሁን አንሱ!!!» እና «ሕገ-መንግስቱ ይከበር!!!» የሚሉ መሆናቸውን መግለጫው ጠቅሷል።

​ይህ ህዝባዊ መርሃ-ግብር የክልሉን ዋና ከተማ ሀዋሳን ጨምሮ በአምስቱም ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 417 የተመረጡ መስጂዶች ላይ ብቻ በጥብቅ ዲስፕሊንና በአስተባባሪዎች መሪነት እንደሚተገበር ተገልጿል።

​የአስተባባሪዎች ጥሪ

​አስተባባሪ ኮሚቴው በማሳሰቢያው ላይ እንደገለጸው፣ የንቅናቄው ብቸኛ ዓላማ ፍትህንና ሕገ-መንግስታዊ መብቶችን ማረጋገጥ ብቻ ነው። በመሆኑም መላው ማህበረሰብ ሰላማዊነቱን ጠብቆ፣ ዓላማን ከሚያስቱና አቅጣጫን ከሚያስቀይሱ ማናቸውም ድርጊቶች ራሱን እንዲጠብቅ በጥብቅ አሳስቧል።

​ኮሚቴው በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ የዚህን ሰላማዊ የፍትህ ጥየቃ ቀጣይ ምዕራፎች በየጊዜው ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

Voice of Sidaama

የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የቦታ ለውጥ ተደረገበት​የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (EFF) ባወጣው አዲስ መግለጫ መሠረት፣ በጉጉት የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የቦታ ለውጥ ...
23/06/2026

የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የቦታ ለውጥ ተደረገበት

​የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (EFF) ባወጣው አዲስ መግለጫ መሠረት፣ በጉጉት የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የቦታ ለውጥ ተደርጎበታል።

​አስቀድሞ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንዲካሄድ መርሐ ግብር ተይዞለት የነበረው ይህ የዋንጫ ጨዋታ፣ አሁን ባለው ማሻሻያ ወደ አዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም መዛወሩ ታውቋል።

​የጨዋታው ዝርዝር መረጃ፡

​ቀን፡ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም.

​ሰዓት፡ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት

​ቦታ፡ አበበ ቢቂላ ስታዲየም

23/06/2026
 ፦ የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የወንሾ ወረዳ ሙስሊሞች ሰላማዊ ሰልፉን ተቀላቀሉ !​በሲዳማ ክልል በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘሩ ስድቦችን እና የጥላቻ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም ትናንት የተጀ...
22/06/2026

፦ የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የወንሾ ወረዳ ሙስሊሞች ሰላማዊ ሰልፉን ተቀላቀሉ !

​በሲዳማ ክልል በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘሩ ስድቦችን እና የጥላቻ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም ትናንት የተጀመረው ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬም በሌሎች አካባቢዎች በከፍተኛ ሁኔታ ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ አሁን በደረሰን አስቸኳይ መረጃ መሰረት የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የወንሾ ወረዳ ሙስሊሞች ሰልፉን በይፋ ተቀላቅለዋል።

ትናንት በክልሉ ምስራቃዊ ዞን በዳዬ ከተማ የተጀመረውን የተቃውሞ መፈክሮችና ሰላማዊ ሰልፍ፣ በዛሬው እለት የቡራ ወረዳ ሙስሊም ማህበረሰብ አባላት በነቂስ በመውጣት በይፋ የተቀላቀሉት ሲሆን፣ አሁን ደግሞ የወንሾ ወረዳ ማህበረሰብ አባላት መሳተፋቸውን ተከትሎ የተቃውሞው ድምጽ ይበልጥ እየጎላ መጥቷል።

የሰልፉ አስተባባሪዎችና ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ መብትንና የእምነትን ክብር ለማስከበር የሚደረገው ይህ ሰላማዊ ትግል ሳይቀዘቅዝ በተጠናከረ መልኩ በሁሉም የሲዳማ አካባቢዎች የሚቀጥል ይሆናል።

Voice of Sidaama

በሀዋሳ ቱላ ጤና ጣቢያ በሊምፋቲክ ፊላሪያሲስና ፖዶኮኒዮሲስ ለተጠቁ ዜጎች የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍ ተደረገ​ሀዋሳ (ቱላ)፤ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም​በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር...
22/06/2026

በሀዋሳ ቱላ ጤና ጣቢያ በሊምፋቲክ ፊላሪያሲስና ፖዶኮኒዮሲስ ለተጠቁ ዜጎች የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍ ተደረገ

​ሀዋሳ (ቱላ)፤ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

​በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ቱላ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ፣ በሊምፋቲክ ፊላሪያሲስ (የዝሆን በሽታ) እና በፖዶኮኒዮሲስ (ቁርባ) ለተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች ሰብአዊ ድጋፍ ተደረገ።

​ይህ የድጋፍ መርሃ ግብር የተከናወነው የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ “GLRS” ከተባለው መንግስታዊ ካልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በጋራ በመተባበር መሆኑ ተገልጿል።

​የተደረጉ የድጋፍ አይነቶች

​በዛሬው ዕለት በሽታው ተጋርጦባቸው ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሰጡት ድጋፎች በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች የተከፈሉ ናቸው፡

​የንፅህና እና የህክምና መጠበቂያ ቁሳቁስ፦ ታካሚዎቹ የበሽታውን ስርጭት እንዲከላከሉና ቁስሎችን በአግባቡ እንዲንከባከቡ የሚያግዙ መሠረታዊ ቁሳቁሶች ተከፋፍለዋል።

​የመቋቋሚያ የገንዘብ ድጋፍ፦ ህመምተኞቹ በበሽታው ሳቢያ ከደረሰባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና አገግመው ራሳቸውን በዘላቂነት እንዲችሉ ለማገዝ የተሰጠ የገንዘብ እገዛ ነው።

​ከተግባሩ በጀርባ ያለው መልዕክት

​የሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት እና የቱላ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የስራ ኃላፊዎች እንደገለጹት፤ እንዲህ መሰሉ የተቀናጀ ድጋፍ የታካሚዎችን የጤና እክል ከመቅረፍ ባለፈ፣ ማህበረሰባዊ መገለል እንዳይደርስባቸውና ወደ መደበኛ ህይወታቸው እንዲመለሱ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ነው።

​በቀጣይም ከተለያዩ የልማት አጋሮችና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመሆን መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመላክታል

Voice of Sidaama

ይድረስ ለሲዳማ ክልል ፕሬዚዳንት ለተከበሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ፦በሲዳማ ክልል የሙስሊሙ ማህበረሰብ የፍትህ እና የእኩልነት ጥያቄ​በሲዳማ ክልል ለረጅም ዘመናት የቆየውን የሃይማኖቶች አብሮ የመኖር...
22/06/2026

ይድረስ ለሲዳማ ክልል ፕሬዚዳንት ለተከበሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ፦በሲዳማ ክልል የሙስሊሙ ማህበረሰብ የፍትህ እና የእኩልነት ጥያቄ

​በሲዳማ ክልል ለረጅም ዘመናት የቆየውን የሃይማኖቶች አብሮ የመኖር፣ የመከባበር እና የሰላም እሴት አደጋ ላይ የሚጥሉ ጥላቻ አዘል ንግግሮች ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት መሰራጨታቸው፣ በክልሉ ሙስሊም ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትና ቅሬታ ፈጥሯል።

​ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአደባባይ መድረኮችና በማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ሰባኪያን፣ የእስልምናን እምነት የሚያንኳስሱና “ሙስሊሞች ከክልሉ መጥፋት አለባቸው” እስከማለት የሚደርሱ ቀስቃሽና አደገኛ መልእክቶችን እያስተላለፉ ይገኛሉ።

​የማህበረሰቡን ቅሬታና ቁጣ ይበልጥ ያባባሰው፣ አቶ አየለ ፈጎ የተባለ ግለሰብ በየመድረኩ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሲሳደብና ሲያጥላላ ከቆየ በኋላ፣ በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ ያስተላለፈውና ግልጽ ንቀት የተሞላበት መልዕክት ነው። ግለሰቡ በንግግሩ እንዲህ ብሏል፦

​"በሲዳማ ክልል የመንግሥት መሥሪያ ቤትና ፍርድ ቤት ሁሉ በክርስቲያኖች እንደሚመራ አታውቁም? የምትከሱኝ እናንተ ናችሁ፤ እንደፈለግኩ መናገርና እስልምናን መሳደብ እችላለሁ፤ መሳደቤንም እቀጥላለሁ፤ ማንም የሚከለክለኝ አካል የለም"

​ይህ የሕግ የበላይነትን፣ የሕገ-መንግሥቱን ድንጋጌዎች እና የፍትህ ተቋማትን ገለልተኝነት የናቀ ንግግር፣ የክልሉ ሙስሊሞች ከክልሉ መንግሥት ፍትህ የማግኘት ተስፋቸው እንዲመናመን እያደረገው ይገኛል። ማህበረሰቡ እንደሚያምነው፣ ይህ ዓይነቱ ድፍረት ሊመጣ የቻለው ከክልሉ ፕሬዚዳንት ጀምሮ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ የመንግሥት ተሿሚዎች የአንድ እምነት ተከታዮች መሆናቸውን እነዚህ ግለሰቦች እንደ ከለላና እንደ ዋስትና በመቁጠራቸው ነው።

​ስለሆነም የክልሉ ሙስሊም ማህበረሰብ ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለአቶ ደስታ ሌዳሞ የሚከተሉትን 3 ቁልፍ እና መሰረታዊ ጥያቄዎች በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥባቸው አጥብቆ ይጠይቃል፦

​1. የመንግሥትና የፍትህ አካላት ገለልተኝነት

​የሲዳማ ክልል መንግሥትና የፍትህ ተቋማት የአንድ ሃይማኖት የበላይነት የሚንጸባረቅባቸው ሳይሆኑ፣ ለሁሉም ዜጎች በእኩልነትና በገለልተኝነት የተመሰረቱ መሆናቸውን በተግባርና በማስረጃ እንዲያሳዩ፤

​2. ለሕግ ማስከበር ቅድሚያ መስጠት

​በማህበረሰቡ መካከል ጥላቻን፣ መገለልንና ቀስቃሽ ንግግሮችን በማሰራጨት ሕግንና ተቋማትን የናቁ፣ የሕዝብን ሰላም የሚያውኩ ግለሰቦች (በተለይም አቶ አየለ ፈጎ) በአስቸኳይ ተፈልገው በሕግ ፊት እንዲቆሙ፤

​3. የአብሮነት እሴትን ማስጠበቅ

​በክልሉ ለዘመናት የኖረውን የሃይማኖቶች የጋራ መከባበር፣ እኩልነት እና ሰላማዊ አብሮ መኖርን ለመጠበቅ የክልሉ መንግሥት ያለበትን ታሪካዊና ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ።

​ማጠቃለያ፦

የክልሉ ሙስሊም ማህበረሰብ የሕግ የበላይነት እንዲከበር፣ ፍትህ እንዲሰፍን እና የዜግነት መብቱ ሙሉ በሙሉ እንዲጠበቅ ጽኑ ፍላጎት አለው። ለዚህም ከክልሉ ፕሬዚዳንት እና ከሚመለከታቸው የፍትህ አካላት አፋጣኝ፣ ግልጽ እና ተጨባጭ የሆነ ማረጋገጫና ምላሽ ይጠበቃል።

​ሰላምና ፍትህ ለሁሉም!

Voice of Sidaama

በሲዳማ ክልል ምስራቅ ሲዳማ ዞን ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሱ ሰድቦችንና የጥላቻ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፎችና የተቃውሞ መፈክሮች ተሰሙ!​በዛሬው ዕለት በሲዳማ ክልል ምስራቅ...
21/06/2026

በሲዳማ ክልል ምስራቅ ሲዳማ ዞን ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሱ ሰድቦችንና የጥላቻ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፎችና የተቃውሞ መፈክሮች ተሰሙ!

​በዛሬው ዕለት በሲዳማ ክልል ምስራቅ ሲዳማ ዞን በበዳዬ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ በበዳዬ ከተማ፣ በሻንታ ዌኔ ቀበሌ እንዲሁም በተለያዩ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ከተሞችና ቀበሌዎች የሚኖሩ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት ሰላማዊ የተቃውሞ መፈክሮችን አሰምተዋል።

​ይህ ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተነሳው ሰሞኑን በሲዳማ ክልል በሚገኙ ሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ያለውን ስድብ፣ ማግለልና የጥላቻ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም እና ፍትህ እንዲሰፍን ለመጠየቅ መሆኑ ታውቋል።

ሰላማዊ የሆነው ተቋውሞ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ይቀጥላል ..


Voice of Sidaama

Address

Awassa

Telephone

+251938651798

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Voice of Sidaama posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Voice of Sidaama:

Share