25/06/2026
/ቤት_ሰበር_ሰሚ_ችሎት የሰጣቸው_አስገዳጅ_የሕግ_ትርጉሞች_በቅደም _ተከተል! #(ክፍል_4)
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
11,ቅጽ/20 የሰ/መ/ቁ 80241፡- የአንድ ንብረት ባለይዞታ የሆነ ሰው ይዞታውን ለመንጠቅ ወይም በይዞታው ላይ ሁከት ለመፍጠር የሚፈፀምን ማንኛውንም ድርጊት እንዲቆም ወይም ንብረቱ እንዲመለስለት ህግ ከጠበቃቸው መንገዶች አንዱ አማራጭ የይዞታ ክስ ማቅረብ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1149(1) ድንጋጌ ያሳያል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የሁከት ይወገድልኝ ክስ መቅረብ የሚችለው አቤቱታ አቅራቢው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ነገር በቀጥታ ወይም በጠባቂ ይዞታ ሲኖረው ነው፡፡ እንዲሁም የይዞታ ክስ የሚቀርበው ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ንብረት በወቅቱ ለመያዝ ምንም አይነት መብት በሌለው ሰው ላይ ስለመሆኑም የድንጋጌው መንፈስ ያስረዳል፡፡ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢ በማስረጃ ማረጋገጥ ያለበት ንብረቱ በይዞታው ስር የነበረና የሁከት ድርጊት ፈጻሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጥር ንብረቱን የወሰደበት መሆኑን ነው፡፡ ሁከት መፍጠር የሚኖረው ባለይዞታ የሆነው ሰው በይዞታው ስር የሚገኘውን ንብረት እንዳይገለገልበት ሌላ ሰው ጣልቃ ገብቶበት መሰናክል ሲፈጠርበት ወይም ረብሻ ሲፈጠርበት ነው፡፡
#11ኛ,የሰበር መ/ቁ.158527 (ቅፅ 24)
🛑የሊዝ ውል እንዲቋረጥ የተሰጠ አስተዳደራዊ ውሳኔ ባልተሻረበት ሁኔታ በሊዝ ውል የተያዘ መሬት ለማስለቀቅ የመሬት አስተዳደር አካል መሬቱን ለመረከብ እንዲያስችለው የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ የሁከት ተግባር ነው ሊባል የማይችል ስለመሆኑ፤
በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1149/3/፤ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ አዋጅ ቁጥር 721/04 አንቀጽ 25 ።
#12ኛ,የሰ/መ/ቁ 186946(ቅጽ 25)
🛑በፍ/ብ/ህግ ቁጥር 1179 ስር የተመለከተው በሌላ ሰው ይዞታ ላይ የሚደረግ ግንባታን የመቃወም ጉዳይ አግባብ ባለው የአስተዳደር አካል በተሰጠ ይዞታ ላይ በሚደረግ ግንባታ ላይ ተፈጻሚነት የለውም ::
#13ኛ,የሰ/መ/ቁ 186348(ቅጽ 25)
🛑የሁከት ይወገድልኝ ክስ የቀረበለት ፍርድ ቤት ሁከት የተፈጠረ መሆን አለመሆኑን አጣርቶ በመወሰን ረገድ ሁከት ተፈጠረ በተባለበት ወቅት ንብረቱ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ በከሳሽ ይዞታ ስር የነበረ መሆን አለመሆኑን ፤
🛑 ተከሳሽ በክሱ የተጠቀሰውን ተግባር ለመፈጸም የሚያስችል መብት ያለው መሆኑን አለመሆኑን እንጂ፣ ከዚህ በላይ በመሄድ በውርስ እና በይዞታ ባለቤትነት መሰረት ተደርጎ የሚሰጥ ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስሕት ነው
#14ኛ,የሰ/መ/ቁ 186461(ቅጽ 25)
🛑ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚፈጠሩ መብቶች እና ግዴታዎች የሚመሩት በንብረት ህግ አጠቃላይ መርሆዎች በመሆኑ የከተማም ሆነ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀምን አስመልክቶ የሚወጡ ህጎች/አዋጆች በንብረት ህግ ማዕቀፍ ውስጥ የሚመደቡ በመሆኑ ከንብረት ጋር የተገናኙ ያሉ ጽንሰ ሃሳቦች፣ ህጎች እና መርሆዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ለሚቀርብ ክርክር እንደአግባብነታቸው ተፈጻሚነት ያላቸው ናቼው::
🛑አንድን ንብረት አስመልክቶ የሚቀርበውን ክስ ተከትሎ ንብረቱን የሚመለከት የህግ ክፍል ተፈጻሚ የሚሆነው ከሳሽ ክሱን ያቀረበው ንብረቱን በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ በእጁ ካደረገ በኋላ በንብረቱ ላይ ያለው መብት እንዲከበርለት የተረጋገጠ ሲሆን, የታዘዘው ዳኝነት ንብረቱን የሚመለከት መሆኑ ብቻውን ጉዳዩን የንብረት ክርክር የማያደርገው ስለመሆኑ።