Access to Justice Initiative - Ethiopia

Access to Justice Initiative - Ethiopia Promoting the Rule of Law & Access to Justice in Ethiopia.
(2)

We empower citizens through expert legal education and awareness.
⚖️ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍንና ዜጎች በሕግ እውቀት እንዲበቁ የሚሰራ ሙያዊ መድረክ።

የዘመን አቆጣጠር ተቀየረ ወይ?Lakkoofsi Baraa Jijjiirameeraa?🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁የዘመን አቆጣጠር ተቀየረ ወይ? ብላችሁ በተለያየ መንገድ ለጠየቃችሁኝ። አቆጣጠሩ አልተቀየረም...
24/08/2026

የዘመን አቆጣጠር ተቀየረ ወይ?
Lakkoofsi Baraa Jijjiirameeraa?
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁

የዘመን አቆጣጠር ተቀየረ ወይ? ብላችሁ በተለያየ መንገድ ለጠየቃችሁኝ። አቆጣጠሩ አልተቀየረም። የተወሰነው ከነባሩ አቆጣጠር ጎን ለጎን የሂጅራ አቆጣጠር "ዓመተ ሂጅራ"(ዓ. ሂ) በሀገሪቱ እውቅና ኖሮት እንዲሰራበት ።

በተጨማሪም በነበረው የዘመን አቆጣጠር ጋር በተያያዘ "ዓ.ም" (ዓመተ ምህረት፣በክርስቶስ ስቅለት ምህረት አገኘን) ፥ "ዓ.ል" (ዓመተ ልደት፣ ከክርስቶስ ልደት ጀምሮ) እና "እ.ኢ.አ" እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር የሚሉት አጠራሮች ሦስቱም እኩል ተቀባይነት ኖሯቸው እንዲሠራባቸው ነው የተወሰነው።

Lakkoofsi Baraa Jijjiirameeraa?
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁

Karaa garaa garaatiin "Lakkoofsi baraa jijjiirameeraa?" jettanii kanneen na gaafattaniif: Lakkoofsi baraa hin jijjiiramne. Murtiin dabarfame lakkoofsa baraa isa duraan ture cinaatti, lakkoofsi Hijraas biyyaalessatti beekamtii argatee akka itti hojjetamuudha.

Dabalataanis, lakkoofsa baraa isa duraan ture wajjin walqabatee moggaasonni "ዓ.ም" (A.M - Waggaa Araaraa / fannoo Kiristoosiin araara arganne), "ዓ.ል" (A.L - Waggaa Dhalootaa / dhaloota Kiristoos irraa eegalee) fi "እ.ኢ.አ" (A.L.I - Akka Lakkoofsa Itoophiyaatti) jedhaman sadanuu qixa fudhatama argatanii akka ittiin hojjetaman murtaa'eera.

ቀዝቃዛው ወላፈን!!!!የእሱ አቋምና እሳቤ ሲወጋ እንጅ ሲወረወር አይታይም።ድምፅ አልባው ሚሳኤል። አሳምሬ አውቀዋለሁ። የወልዲያ ሃይስኩል የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሳለሁ እሱ የ10 ኛ ክፍል ተማሪ...
24/08/2026

ቀዝቃዛው ወላፈን!!!!

የእሱ አቋምና እሳቤ ሲወጋ እንጅ ሲወረወር አይታይም።ድምፅ አልባው ሚሳኤል። አሳምሬ አውቀዋለሁ። የወልዲያ ሃይስኩል የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሳለሁ እሱ የ10 ኛ ክፍል ተማሪ ነበር። ጩኸት አይወድም። ከተግባር ፊት ይቀድማል። የአዘቦት ቀን ሳይሆን የቁርጥ ቀን ደራሽ ነው። ስራው ይከናወንለት እንጅ credit ለመሰብሰብ አይስገበገብም፤እሱ በሰራው ጓዶቹ ናቸው የሰሩት ቢባል አይከፋውም። ልቡ ሙልት ያለ ነኽ። ላመነበት አቋም ነፍሱን ይሰጣል። የመንጋ ድለቃና የቲፎዞ ድቤ አይመስጠውም። በሃገራዊ ምክክሩ ወቅት ከጎዶቹ ጋር በጥቅሻም በግንባሩም እየተናበበ የስግብግቦቹን አጀንዳ ከእጃቸው ያስጣላቸው ይህ ሰው ነው። በአንድ ወቅት ወሎ ሕብረት የልማት ማህበርን መስርተን ሰበር ሰካ ስንል ወንድሞቼ አማራነትን ጅብ የሚያስበላ ወሎየነት ከሆነ ይቅርባችሁ ሲል ጎሰም አደረገን።አማራ አንገቱ አንድ ነው። አማራነታችን ከወሎየነታችን ጋር የማይጣላብን የሸህ ሰይድ መሀመድ ሷዲቅ ደረሶ፤ የአባ ጊወርጊስ ዘጋስጫ የቆሎ ተማሪዎች መሆናችንን አስረግጠን ነገርነው። በረካ ሁኑ ብሎ መረቀን ። የእሱ ህልም ያሳደገውን ህዝብ ከረሃብ ከቸነፈር ከስደትና ከመከራ ተላቆቆ ማየት ነው።በብሔራዊ ምክክሩ ጠባቦቹ የእና እኔ ባዩቹ ሲንቦጃቦጁ የማእዘኑን ውሃ ልክ ከጓዶቹ ጋር ያደላደለው አብዱ ሁሴን ነው። ያለ ስራው ስራ ያለ ስሙ ስም የሚሰጡትን መሸጦዎች አውቃቸዋለሁ። ጉርሻ የራቃቸው ጉ-ር-ሳ-ዎ-ች ናቸው። አብዱ ሁሴን!!!! ቀዝቃዛው ወላፈን!!!
#ጠበቃ መንግስቱ ዘገየ አባተ

24/08/2026

#ባህዳር
የነዋሪዎቿና የሁሉም ኢትዮጲያዊ ከተማ እንጂ የአንድ ብሄር ከተማ አይደለችም። ይህ ማለት ማንኛውም ኢትዮጲያዊ በከተማዋ የማይንቀሳቀስ ሀብት እስካፈራና መኖር እስከፈለገ ድረስ የከተማዋ ባለቤት ነው ። ለዚህ መከራከሪያ መነሻ የሚሆነው በአማራ ክልል ህገ-መንግስት በአንቀጽ 40(3) "የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትና የተፈጥሮ ሀብት ባለቤትነት መብት የክልሉ መንግሥትና የሕዝብ ብቻ ነው በሚል የተደነገገ ሲሆን በዚህ ህገ-መንግስት ላይ “ህዝብ “የሚለው ቃል መሬትን ለአንድ ብሄር ያልሰጠ መሆኑን ያሳያል። ስለዚህ ማንኛውም ኢትዮጲያዊ ህዝብ የባህርዳር ከተማ ባለቤት ነው!!
#ጠበቃ ዮርዳኖስ አበበ

24/08/2026

በሥልጣን ላይ ያለ ሰው ትህትናን ካጣ፣ ሹመቱ ክብር ሳይሆን ፈተና ይሆናል።

የሹመትና የሥልጣን እውነተኛ ትርጉም ከክርስትና እና ከኢስላም መለኮታዊ አስተምህሮዎች አንጻርበሁለቱም ታላላቅ ሃይማኖቶች (በክርስትና እና በኢስላም) አስተምህሮ መሠረት ሹመትና ሥልጣን የክብር...
24/08/2026

የሹመትና የሥልጣን እውነተኛ ትርጉም ከክርስትና እና ከኢስላም መለኮታዊ አስተምህሮዎች አንጻር

በሁለቱም ታላላቅ ሃይማኖቶች (በክርስትና እና በኢስላም) አስተምህሮ መሠረት ሹመትና ሥልጣን የክብር፣ የትዕቢት ወይም ሰውን ከሌሎች በላይ የማድረጊያ መድረክ ሳይሆን፣ ከባድ መደራሪያ አደራ (አማናህ) እና የሕዝብ አገልጋይነት ኃላፊነት ነው።

ይህንን መሠረታዊ እውነት ከሁለቱም ሃይማኖቶች መለኮታዊ መመሪያዎች አንጻር እንደሚከተለው እንመለከተዋለን፦

1️⃣ በክርስትና አስተምህሮ፦ ሹመት የአገልጋይነት አደራ ነው ✝️

የክርስቶስ መመሪያ፦

"በእናንተ ዘንድ ታላቅ ሊሆን የሚወድ አገልጋያችሁ ይሁን።" (ማቴዎስ 20፥26)

የኃላፊነት ሚዛን፦ ሹመት ሰውን ከሌሎች በላይ ለማድረግ የሚሰጥ መድረክ ሳይሆን፣ ለሌሎች የበለጠ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚሰጥ አደራ ነው። ሥልጣን የሰውን ባህሪ ከመቀየር ይልቅ የውስጡን ማንነት የሚገልጥ ፈተና ነው። በሥልጣን ላይ ያለ ሰው ትህትናን ካጣ፣ ሹመቱ ክብር ሳይሆን ፈተና ይሆናል።

የመሪነት መስፈርት፦ እውነተኛ መሪ ሲሾም ራሱን ከፍ አያደርግም፤ ለሕዝብ ያለውን አገልግሎት ከፍ ያደርጋል። ሥልጣኑን ለግል ጥቅም ሳይሆን ለሕዝብ ጥቅም ያውላል። ሹመት የሚለካው በወንበሩ ከፍታ ሳይሆን፣ በሚያመጣው የአገልግሎት ውጤት ነው።

2️⃣ በኢስላም አስተምህሮ፦ ሹመት ከባድ አደራና የቁስል ምንጭ ነው ☪️

ሥልጣን አደራ (አማናህ) ነው፦ ነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ለሶሓቢያቸው ለአቡ ዘር (ረ.ዐ) የሰጡት ማስጠንቀቂያ፦

"አቡ ዘር ሆይ! አንተ ደካማ ነህ፤ ሹመት ደግሞ አደራ (አማናህ) ነው። በቂያማ (በመጨረሻው) ቀንም (በሕግ አግባብ እና በፍትሕ የወሰደውና ግዴታውን የተወው ካልሆነ በስተቀር) ውርደትና ጸጸት ነው።" (ሶሒሕ ሙስሊም)

መሪ ማለት የሕዝብ አገልጋይ ነው፦ በታወቀው ኢስላማዊ የመሪነት መርህ መሠረት፦

"የሕዝብ አለቃ ማለት የዚያ ሕዝብ አገልጋይ ነው" (ሰይዱል ቀውሚ ኻዲሙሁም)።

ሕዝብን ማታለል ጥብቅ ክልክል ነው፦ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦

"አላህ በሕዝብ ላይ ሾሞት እያለ ሕዝቡን በማታለልና በመበደል ላይ እያለ የሚሞት ማንኛውም አገልጋይ (መሪ)፣ አላህ በእርሱ ላይ ጀነትን እርም ያደርግበታል።" (ሶሒሕ ቡኻሪ)

3️⃣ የሁለቱ አስተምህሮዎች የጋራ መደምደሚያ

ትህትናና ፍትሕ፦ በሁለቱም እምነቶች ሥልጣን ላይ የሚቀመጥ ሰው ከትዕቢት የራቀ፣ ፍትሐዊ እና የሕዝብን አደራ ጠባቂ መሆን አለበት።

ተጠያቂነት፦ ሥልጣን በሰውም ሆነ በፍጣሪ ፊት የሚያስጠይቅ ከባድ አደራ እንጂ የሽልማት መድረክ አይደለም።

በየትኛውም ሃይማኖታዊና ምሁራዊ መነጽር "ሹመት የሽልማት መድረክ ሳይሆን የከባድ ኃላፊነትና የአደራ ሚዛን" ነው። ሥልጣን ላይ ያለ ሰው ትህትናን ካጣ፣ ሕዝብን እንደ ጌታ ሳይሆን እንደ አገልጋይ ካላየ ሹመቱ ክብር ሳይሆን የመጨረሻ ውርደት ይሆናል።

24/08/2026

መንግሥት በሥሩ ያሉትን ግጭት አፋጣኞች/ጠማቂዎች/ የመግታትና የዜጎችን እኩልነትና ደህንነት የማረጋገጥ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ አለበት።

የጅምላ ፈረጃ አደጋ ከሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ትምህርት እስከ አሁናዊ የኢትዮጵያ ስጋትማህበረሰብን በጅምላ መፈረጅና መወንጀል በመጨረሻው ደረጃ ወደ ጅምላ ጥቃት፣ መገለልና አሰቃቂ እልቂት ያመራ...
24/08/2026

የጅምላ ፈረጃ አደጋ ከሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ትምህርት እስከ አሁናዊ የኢትዮጵያ ስጋት

ማህበረሰብን በጅምላ መፈረጅና መወንጀል በመጨረሻው ደረጃ ወደ ጅምላ ጥቃት፣ መገለልና አሰቃቂ እልቂት ያመራል። በሀገር ውስጥና በመንግሥት መዋቅር አቅራቢያ የሚገኙ ጥቂት ግጭት ጠማቂዎች (War Entrepreneurs) ማህበረሰብን በጅምላ የመፈረጅ ንግግርን ለፖለቲካ ትርፍ ሲጠቀሙበት፣ ውጤቱ ለሀገር መፍረስና ለአሰቃቂ የሰው ልጅ እልቂት መንገድ መክፈት ነው።

ይህን አደገኛ አካሄድ ከሩዋንዳ ታሪካዊ እልቂት እና ከአሁናዊ የሀገራችን ሁኔታ ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው እንተነተነዋለን።

1️⃣ የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ፈጣን መንስኤ (Immediate Cause) እና የጅምላ ፈረጃ ውጤት

የድምፅና የንግግር መርዝ፦ በ1984 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 1994) በሩዋንዳ የተከሰተው የዘር ጭፍጨፋ ከመጀመሩ በፊት፣ ሚዲያዎችና የመንግሥት ባለሥልጣናት የቱትሲን ማህበረሰብ በጅምላ "እባቦች" እና "ጠላቶች" በማለት ይፈርጁ ነበር።

የጭፍጨፋው መነሻ፦ የፕሬዝዳንት ጁቨናል ሀብያሪማና አውሮፕላን ተመቶ መውደቅ ለጭፍጨፋው ፈጣን መነሻ (Immediate Cause) ይሁን እንጂ፣ ቀድሞ የተዘራው የጅምላ ፈረጃና የጥል ንግግር ማህበረሰቡን ለጭፍጨፋ ዝግጁ አድርጎት ነበር።

የደረሰው እልቂት፦ በዚሁ የጅምላ ፈረጃ ምክንያት በ100 ቀናት ውስጥ ብቻ ከ800,000 በላይ ንጹሃን ቱትሲዎችና ምክንያታዊ ሁቱዎች በጅምላ ተጨፍጭፈዋል።

2️⃣ በኢትዮጵያ፡ የአማራን ሕዝብ በጅምላ የመፈረጅ አደገኛ አካሄድ

የጅምላ ፈረጃ አደጋ፦ አሁን ላይ በስልጣንና በፕሬዝዳንት አማካሪነት ደረጃ የሚገኙ አካላት፣ ሙሉውን የአማራ ሕዝብ በጅምላ በመፈረጅ እና በግጭት ጠማቂነት በመወንጀል ላይ ይገኛሉ።

የጥቃትና የመገለል ስጋት፦ አንድን ማህበረሰብ እንደ ማህበረሰብ በጅምላ መፈረጅ፣ ንጹሃን ዜጎች በየቦታው ለጅምላ ጥቃት፣ መፈናቀልና መገለል እንዲዳረጉ መንገድ ይከፍታል።

የታሪክ ድግግሞሽ ስጋት፦ በሩዋንዳ የተከሰተው አይነት የቃላት መርዝ እና የጅምላ ፈረጃ በአሁኑ ወቅት በሕዝባችን ላይ እንዲንጸባረቅ ማድረግ ሀገሪቱን ወደ አደገኛ ቀውስ የሚከት ነው።

3️⃣ ግጭት ጠማቂዎች (War Entrepreneurs) እና የሕግ ተጠያቂነት

የፖለቲካ ንግድ፦ ግጭት ጠማቂዎች የሕዝብን ደም እና የዜጎችን ስቃይ ለራሳቸው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅም ማካበቻ ያደርጉታል።

በሕግ መጠየቅ፦ በመንግሥት ጉያ ስር ሆነው የጅምላ ፈረጃና የጥላቻ ንግግር የሚያስፋፉ አካላት በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ሕግ ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል።

የመንግሥት ኃላፊነት፦ መንግሥት በሥሩ ያሉትን ግጭት አፋጣኞች የመግታትና የዜጎችን እኩልነትና ደህንነት የማረጋገጥ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ አለበት።

4️⃣ የመፍትሔ እና የንቅናቄ አቅጣጫ

ጅምላ ፈረጃን ማቆም፦ የትኛውንም ማህበረሰብ በቡድንና በጅምላ ከመፈረጅ መቆጠብ እና ጥፋት ያጠፉ ግለሰቦችን ብቻ በሕግ መጠየቅ።

የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ፦ የጥላቻ ንግግርና የጅምላ ፈረጃ የሚያስፋፉ ሰዎችን ለፍርድ ማቅረብ።

ሕዝባዊ አንድነት፦ ማህበረሰቡ በግጭት ጠማቂዎች አጀንዳ ሳይወሰድ፣ የጋራ ሰላሙንና አብሮነቱን ማስከበር አለበት።

24/08/2026

ማህበረሰብ እንደ ማህበረሰብ በጅምላ አይፈረጅም ፣ ይህ ፍረጃ አድጎ የጅምላ ጥቃት ፣ የጅምላ መገለል እና የጅምላ እልቂትን የሚፈጥር በመሆኑ በመንግስት ጉያ ስር ሆነው ግጭት ጠማቂወችን (War Entrepreneurs ) በህግ ሊጠየቁ ይገባል።

24/08/2026

አብሮ ለመኖር ወርቃማው ዘዴ ለእኩልነት ቦታ መስጠት ነው።

24/08/2026

የፓለቲካ መሠረቱ ህግ ነው ፓለቲከኛ ህግ አዋቂ ከሆነ ድሞክራሲና ሰብአዊ መብት ያበቡባት የበለፀገች ኢትዮጵያ ትፈጠራለች።

Address

Adis

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Access to Justice Initiative - Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category