31/05/2026
ክስ የማቅረብ መብት (Cause of Action) እና የማስረጃ ምዘና ደረጃ ልዩነት
የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት
መዝገብ ቁጥር =የሰ.መ.ቁ 233250
ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
መግቢያ፦
አንድ ከሳሽ ሌላውን ወገን በፍርድ ቤት ለመክሰስ የሚያስችለው መብት ወይም ጥቅም (Cause of Action) መኖሩን ማሳየት ለክሱ ተቀባይነት የመጀመሪያው መሠረት ነው። ሆኖም ግን፣ ክስ የማቅረብ መብት ወይም ጥቅምን ማሳየት እና ክሱን በውሳኔ ለማጠናቀቅ የሚደረግ የማስረጃ ምዘና ደረጃ ፍፁም የተለያዩ ሕጋዊ ሥርዓቶች ናቸው።
ብዙውን ጊዜ በሙግት ሂደት ላይ ከሳሽ ገና ተከሳሽ ሳይጠራ ፍሬነገሩን በሙሉ እንዲያስረዳ የሚገደድበት ወይም የቅድመ-ሕግ ሁኔታዎች የሚደበዝዙበት አጋጣሚ ይታያል። ይህንን አስመልክቶ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ምን ይላል? የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትስ የሰጣቸው አስገዳጅ የሕግ ትርጉሞች ምን ይመስላሉ? ሙሉውን ትንታኔ ከዚህ በታች እንመልከት፦
✅ የአንድ መብትና ግዴታ ምንጭ ሕግ ወይም ውል ሲሆን አንድ ከሳሽ ሌላውን ወገን በተከሳሽነት
ፍርድ ቤት መክሰስ የሚያስችለው ምክንያት (cause of action) እንዲኖረው የግድ የሚል መሆኑንና
ለመክሰስ የሚያስችል ጥቅም ወይም መብት በማረጋገጥ አቤቱታ ካላቀረበ በቀር በማናቸውም ሰው ላይ ክስ
ሊያቀርብ የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 33(2)እና(3) ድንጋጌ ያስገነዝባል፡፡
✅ሆኖም በአንድወገን ላይ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መብት ወይም ጥቅም መኖሩ ብቻውን ውጤት የሚያመጣ ሳይሆንከሳሹ ተጣሰብኝ ወይም ተደፈረብኝ ወይም አልተፈፀመልኝም የሚለውን ግዴታ በሌላው ወገን በሕግ ወይም
በውል የተገኘ መብቱ/ ጥቅሙ / የተጣሰበት መሆኑን፣ ተከሳሹ መብቱ የተደፈረበት ወይም ግዴታ
ያልተፈፀመበት መሆኑን፣ መብቱ በመደፈሩ ወይም ሊፈፀምለት ይገባው የነበረው ግዴታ ባለመፈፀሙ ጥቅምየቀረበት ወይም ጉዳት የደረሰበት መሆኑን፣ እንዲሰጥለት የሚጠይቀው ዳኝነት (relief) በሕግ የተፈቀደመሆኑን ካለሳዬ በቀር ያቀረበው ክስ ተቀባይነት ሊኖረው የማይገባ ስለመሆኑም ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ33(2)እና(3) ፤ 231 ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መዘንዘብ ይቻላል፡፡
✅ በመሆኑም አንድን ክስ የሚያቀርብተከራካሪ ወገን ይህንን ሊያስረዳ የሚችል ጠቋሚ ማስረጃ (Prima facie evidence) ሊያቀርብ ይገባል፡፡
✅ከሳሽ የሆነው ወገን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33(2)እና(3) ድንጋጌ አኳያ የሚጠበቅበት ክስ በመሰረተበት ነገር / ሐብት / ላይ ከሕግ ወይም ከውል የመነጨ መብት ወይም ጥቅም እንዳለው እና ይሄው ጥቅሙ ወይም መብቱ በተከሳሹ የተነካበት ወይም የተጣሰበት መሆኑን እንጂ ገና ተከሳሹ ሳይጠራ በክሱ የተጠቀሰውንፍሬነገር በማስረጃ እንዲያረጋግጥ አይደለም፡፡
✅ይህም ከሳሽ የሆነው ተከራካሪ ወገን ከጅምሩ እንዲያረጋግጥ
የሚጠበቅበት አለኝ የሚለውን መብት በክስ አቤቱታው ላይ እንዲያሳይ እና ይህንንም የሚያረጋግጥለት
ጠቋሚ ማስረጃ ማቅረብ እንደሆነ፤ ክስ የማቅረብ መብት ወይም ጥቅም ማስረዳት መቻል እና እንደክሱ
አቀራረብ ወይም እንደተጠየቀዉ ዳኝነት ዉሳኔ ለመስጠት የሚያስችል የማስረጃ ምዘና ደረጃ ልዩነት ያላቸው
መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
✅ተከራካሪ የሆኑ ወገኖች የሚያቀርቧቸውን ክርክሮች ለመወሰን በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች ደግሞ ተከሳሽ ወገን ክሱን ለማስተባበል የሚያቀርበውን መከራከሪያ እና ማስረጃ
መሠረት በማድረግ ፍሬነገርን አጣርተው እና ማስረጃ መዝነው ዉሳኔ መስጠት የሚጠበቅባቸው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33/2 እና 231፤ 182 እና 273 ድንጋጌዎች ይዘት ያስገነዝቡናል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም በዚህ ረገድ በተለይም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 33 እና 231 አተገባበርን አስመልክቶ
በሰ.መ.ቁ 82234፤ 135639፤ 144052 እና በሌሎችም መዝገቦች ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል