ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል

ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል, Lawyer & Law Firm, Addis Ababa.

✳️ወክሎ መከራከር
✳️የማማከር አገልግሎት
✳️ክስና መልስ ማዘጋጀት
✳️ይግባኝ እና ይግባኝ መልስ ማዘጋጀት
✳️+251910214108
✳️በስልክ ወይም በአካል ማገኘት ይችላሉ
አድራሻ :-
➡️አድስ አበባ
➡️ደሴ
➡️ኮንቦልቻ
➡️ወልዲያ .........

የፍታብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መጥሪያ አሰጣጥ እና የምስክርነት ግዴታዎች አጠቃላይ  የኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፍበጠበቃ አደም ሰይድ ከማል👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛የፍትሐ ብሔር ፍርድ ቤት ሂደቶች ፍት...
31/08/2026

የፍታብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መጥሪያ አሰጣጥ እና የምስክርነት ግዴታዎች አጠቃላይ የኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፍ
በጠበቃ አደም ሰይድ ከማል
👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛👛
የፍትሐ ብሔር ፍርድ ቤት ሂደቶች ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋ እና ተዓማኒ እንዲሆኑ ከተነደፉት መሠረታዊ ሕጋዊ ሥርዓቶች መካከል የመጥሪያ አሰጣጥ እና የምስክርነት ግዴታ አፈጻጸም ዋነኞቹ ናቸው። በሂደት ላይ ያሉ አካላት ሆን ብለው መጥሪያን ከመቀበል ሲሸሹ፣ መጥሪያ ሳይደርስ ሲቀር ወይም ምስክሮች ሕጋዊ ጥሪን ችላ ሲሉ ፍርድ ቤቶች የሚወስዷቸው እርምጃዎች በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ በግልጽ ተደንግገዋል።
በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ከፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 103 እስከ 105፣ 116፣ እና 118 የተደነገጉትን ቁልፍ የህግ ማዕቀፎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 153610 (ቅጽ 23) የሰጠውን አጠቃላይ የህግ ትርጉም መሠረት በማድረግ፤ ተከሳሾች መጥሪያን ለመቀበል ሲያመነቱ የሚወሰድ እርምጃ፣ የመጥሪያ አሰጣጥ ማረጋገጫ ሥርዓት፣ በምትክ የሚሰጥ መጥሪያ (Substituted Service) አሠራር፣ እንዲሁም የምስክሮች ሕጋዊ የመመስከር ግዴታና የፍርድ ቤቶች የማስገደድ ኃላፊነት በዝርዝር በጠበቃ አደም ሰይድ ከማል በሚከተለው መልኩ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፦
1. መጥሪያን ለመቀበል እምቢተኛ ስለመሆንና ባለመገኘት የሚወሰድ ሕጋዊ እርምጃ ተከሳሹ፣ ወኪሉ፣ እንደራሴው ወይም መጥሪያው ሊደርሰው የሚገባው ማንኛውም አካል መጥሪያውን በባለቤትነት ተረክቦ የደረሰኝ ማረጋገጫ ለመፈረም ፈቃደኛ ሳይሆን ሲቀር፣ ወይም መጥሪያ ሰጪው ተገቢውን ፍለጋ አድርጎ ተቀባይን ማግኘት ሳይችል ሲቀር፣ እንዲሁም ተቀባይ ወኪል የሌለው መሆኑ ሲታወቅ ጥብቅ ሕጋዊ ሥርዓት ይከተላል። በዚህ ጊዜ መጥሪያ ሰጪው ወይም ባለጉዳዩ መጥሪያውን ለመስጠት ያልቻሉበትን ምክንያት በግልጽ በመሐላ ቃላቸው አረጋግጠው መጥሪያውን ለፍርድ ቤቱ ይመልሳሉ።
• የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 115 ድንጋጌዎች በዚህ መልኩ ሲያጋጥሙ ተፈጻሚ ይሆናሉ።
• መጥሪያ ተልኮለት ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆኑ ወይም ደረሰኝ ለመስጠት ያሳየው እምቢተኝነት በመሐላ በተሰጠ ቃል ከተረጋገጠ፣ መጥሪያው እንደደረሰው ተቆጥሮ ተከሳሹ በሌለበት ክርክሩ እንዲቀጥል ይደረጋል።
2. የመጥሪያ አሰጣጥ ሁኔታዎችንና ጊዜን በዝርዝር የማረጋገጥ ግዴታ በቁጥር 102 መሠረት ስለማንኛውም ጉዳይ መጥሪያ በሚሰጥበት ወቅት መጥሪያ ሰጪው ጥብቅ የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።
• መጥሪያ ሰጪው በዋናው መጥሪያ ላይ ወይም ከዚሁ ጋር በሚያያዝ ሌላ ወረቀት ላይ መጥሪያውን የሰጠበትን ትክክለኛ ጊዜና ሁኔታ መመዝገብ አለበት።
• የተቀባዩን ሙሉ ስም፣ መጥሪያው በሚሰጥበት ጊዜ በቦታው የነበሩ ምስክሮችን ስም በዝርዝር መጻፍ ይኖርበታል።
• ተቀባይ ከፈረመበት ዋና ኮፒ ጋር በማያያዝ መጥሪያውን ለፍርድ ቤቱ በይፋ መልስ አድርጎ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
3. በምትክ የሚሰጥ መጥሪያ (Substituted Service) እና የቸልተኝነት ሕጋዊ ውጤት ተከሳሹ መጥሪያ እንዳይደርሰው ሆነ ብሎ ራሱን የሸሸገ ወይም በፍርድ ቤቱ ደንበኛ ሥነ ሥርዓት መሠረት እንዳይደርስ መሰናክል የፈጠረ መሆኑ በሕግ ሲረጋገጥ ልዩ አሰራር ይተገበራል፦
• ፍርድ ቤቱ መጥሪያው በፍርድ ቤቱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ግልጽ በሆነ ሥፍራ ላይ እንዲለጠፍ ያደርጋል።
• ተከሳሹ የታወቀ መኖሪያ ቤት ያለው፣ በመጨረሻው ጊዜ ይኖርበት የነበረው ሥፍራ፣ የሚሠራበት ወይም የንግድ ሥራውን የሚያካሂድበት ቦታ የታወቀ ከሆነ በዚያው ግልጽ በሆነ ሥፍራ ላይ እንዲለጠፍ ይደረጋል።
• በቁጥር 107 እና 108 መሠረት ወይም በጋዜጣ ማስታወቂያ አማካይነት፣ እንዲሁም ፍርድ ቤቱ ተገቢ ሆኖ ያገኘው ሌላ ዘዴ ተከሳሹ መጠራቱን እንዲያውቅ ይደረጋል።
• መጥሪያው ሳይሰጥ በተመለሰ ጊዜ በከሳሽ አመልካችነት አዲስ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም በምትክ እንዲፈጸም ሊታዘዝ ይችላል። ሆኖም መጥሪያው ሳይሰጥ በተመለሰ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ ከሳሹ ሳያመልክት የቀረ እንደሆነ በቁጥር 70 መሠረት ቸልተኝነት የተረጋገጠ ይሆናል።
• ለተከሳሹ ሳይሆን በፍርድ ቤቱ ትእዛዝ መሠረት ለተከሳሹ ምትክ የተሰጠ መጥሪያ ለራሱ እንደተሰጠ ይቆጠራል፤ ፍርድ ቤቱም ተከሳሹ የሚቀርብበትን ጊዜ እንደ ነገሩ ሁኔታ ወስኖ ያስታውቃል ።
4. ለምስክሮች የሚሰጥ መጥሪያ አሰጣጥ ሥርዓት ለምስክሮች የሚሰጥ መጥሪያ ሁሉ ከቁጥር 103 እስከ 105 ከተመለከቱት ልዩ ሁኔታዎች በስተቀር፣ በዚህ ምዕራፍ የመጀመሪያ ክፍል ለተከሳሾች መጥሪያ ስለ መስጠት በተመለከተው ድንጋጌ መሠረት ሙሉ ተፈጻሚነት ይኖረዋል።
• በቁጥር 118 የተደነገጉት ጥሪን የማያከብሩ ምስክሮች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣ የምስክር መጥሪያዎች በዚሁ መርህ ይመራሉ።
5. የጥሪ ትእዛዝን በማያከብሩ ምስክሮች ላይ የሚወሰዱ ሕጋዊ እርምጃዎች የምስክርነት ቃሉን እንዲሰጥ ወይም የጽሑፍ ማስረጃ እንዲያቀርብ ጥሪ ትእዛዝ የተላከለት ማንኛውም ሰው ትእዛዙን ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ፣ ፍርድ ቤቱ አስቀድሞ የተላከለት ጥሪ መድረሱን ማረጋገጥ አለበት።
• እንዲቀርብ የተፈለገው ምስክር ወይም የጽሑፍ ማስረጃ ለጉዳዩ አወሳሰን ጠቃሚ መሆኑ ሲረጋገጥ፦
o የተላከው መጥሪያ ለባለ አድራሻው በሚገባ ያልደረሰው መሆኑ ከተረጋገጠ፣ ባለጉዳዩ ተገቢውን ኪሳራ ከፍሎ ሌላ መጥሪያ እንዲወስድ ይታዘዛል።
o መጥሪያው ደርሶት ሳይቀርብ የቀረው በሕግ በማይደገፍ ወይም በቂ ባልሆነ ምክንያት ሲሆን፣ ወይም እንዳይደርሰው ሆነ ብሎ መሰወሩ ሲረጋገጥ ፍርድ ቤቱ ተገቢውን ትእዛዝ በመስጠት ተጠሪው ተይዞ ወይም ታስሮ እንዲቀርብ ያደርጋል።
6. የምስክሮች ሕጋዊ የመመስከር ግዴታና የፍርድ ቤት የማስገደድ ኃላፊነት ለአንድ ጉዳይ ለምስክርነት የተቆጠረ ማንኛውም ግለሰብ በፍርድ ቤቱ ጥሪ መሠረት በሰዓቱ ቀርቦ የመመስከር ግዴታ አለበት።
• ምስክሩ ሊቀርብ ካልቻለ ወይም ምክንያቱ በቂ ካልሆነ፣ ፍርድ ቤቱ ተገቢ መስሎ የታየውን የትእዛዝ መንገድ በመከተል ምስክሩ በሕግ አግባብ ተገዶ ወይም ታስሮ እንዲቀርብ ማዘዝ አለበት።
• ፍርድ ቤቱ ይህንን እርምጃ በመውሰድ የምስክርነቱን ቃል መስማትና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም በሌላ ማስረጃ ጭምር በማጣራት በቀረበው ጉዳይ ላይ ፍትሐዊ ዳኝነት ሊሰጥ ይገባል።
7. የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በመዝገብ ቁጥር 153610 (ቅጽ 23) የህግ ትርጉም አተገባበር በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው የህግ ትርጉም መሠረት የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 116 እና 118(2)(ለ) ድንጋጌዎች ትርጉም ሰፊ ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል።
• ፍርድ ቤቶች የምስክሮችን ቀርቦ የመመስከር ግዴታ በማክበር ረገድ ክፍተት ሊኖራቸው እንደማይገባ፣
• ምስክሮች ቃላቸውን ሳይሰጡ እንዲቀሩ ክፍተት የሚፈጥሩ አሠራሮችን በማረም በፍርድ ሂደት ውስጥ መረጃዎችንና ማስረጃዎችን የማጣራት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው፣
• የፍትሕ አሰጣጡ ፍጹም የተሟላ እንዲሆን በሕግ የተሰጣቸውን አስገዳጅ የፍርድ ቤት ሥልጣን በአግባቡ በመጠቀም ጉዳዮችን በአስተማማኝ ማስረጃ መደምደም እንዳለባቸው ሕጋዊ ትርጉም ተሰጥቶበታል።
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል
📍 አድራሻ፦ አዲስ አበባ | ደሴ (ወሎ) | ኮምቦልቻ
📞 ስልክ፦ +251910214108
📧 ኢሜይል፦ [email protected]
📱 ቴሌግራም፦ https://t.me/adem2141

29/08/2026
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ነሀሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ ውሳኔ የሰጠባቸው መዝገቦች ዝርዝርተ.ቁ መ, ቁ. የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልገውም1. 6416/...
28/08/2026

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ነሀሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ ውሳኔ የሰጠባቸው መዝገቦች ዝርዝር
ተ.ቁ መ, ቁ. የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልገውም
1. 6416/14 "
2. 7151/14 "
3. 7627/15 "
4. 7813/15 "
5. 7814/15 "
6. 7920/15 "
7. 8166/16 "
8. 8271/16 "
9. 8287/16 "
10. 8370/16 "
11. 8390/16 "
12. 8585/16 "
13. 8761/16 "
14. 8771/16 "
15. 8782/16 "
16. 8804/16 "
17. 8859/16 "
18. 8876/16 "
19. 8880/16 "
20. 8881/16 "
21. 8890/16 "
22. 8891/16 "
23. 9033/16 "
24. 9088/17 "
25. 9247/17 "
26. 9286/17 "
27. 9454/17 "
28. 9615/17 "
29. 9627/17 "
30. 9653/17 "
31. 9721/17 "
32. 9741/17 "
33. 9787/17 "
34. 9877/17 "
35. 9881/17 "
36. 9885/17 "
37. 9904/17 "
38. 9919/17 "
39. 9995/17 "
40. 10092/17 "
41. 10167/17 "
42. 10329/18 "
43. 10330/18 "
44. 10513/18 "
45. 10532/18 "
46. 10545/18 "
47. 10724/18 "
48. 10733/18 "
49. 10872/18 "
50. 10993/18 "
51. 11024/18 "
52. 11048/18 "
53. 11051/18 "
54. 11055/18 "
55. 11066/18 "
56. 11087/18 "
57. 11155/18 "
58. 11161/18 "
59. 11186/18 "
60. 11204/18 "
61. 11223/18 "
62. 11310/18 "
63. 11345/18 "
64. 11415/18 "
65. 11429/18 "
66. 11445/18 "
67. 11465/18 "
68. 11564/18 "
69. 11566/18 "
70. 5920/13 የተቋረጠ
71. 9324/17 ማሻሻያ የተፈቀደ
ማስፈቀጃ
72. 10830/18 ተቀባይነት ያላገኘ
73. 11009/18 ተቀባይነት ያላገኘ
74. 11038/18 የተፈቀደ
75. 11085/18 ተቀባይነት ያላገኘ
76. 11088/18 ተቀባይነት ያላገኘ
77. 11092/18 ተቀባይነት ያላገኘ
78. 11097/18 ተቀባይነት ያላገኘ
79. 11098/18 የተፈቀደ
80. 11115/18 ተቀባይነት ያላገኘ
81. 11116/18 ተቀባይነት ያላገኘ
82. 11148/18 ተቀባይነት ያላገኘ
83. 11170/18 የተፈቀደ
84. 11171/18 ተቀባይነት ያላገኘ
85. 11174/18 ተቀባይነት ያላገኘ
86. 11183/18 ተቀባይነት ያላገኘ
87. 11201/18 ተቀባይነት ያላገኘ
88. 11211/18 ተቀባይነት ያላገኘ
89. 11222/18 ተቀባይነት ያላገኘ
90. 11224/18 የተፈቀደ
91. 11266/18 ተቀባይነት ያላገኘ
92. 11311/18 ተቀባይነት ያላገኘ
93. 11328/18 የተፈቀደ
94. 11333/18 የተፈቀደ
95. 11335/18 ተቀባይነት ያላገኘ
96. 11346/18 ተቀባይነት ያላገኘ
97. 11349/18 ተቀባይነት ያላገኘ
98. 11338/18 ተቀባይነት ያላገኘ
99. 11452/18 ተቀባይነት ያላገኘ
100. 11523/18 ተቀባይነት ያላገኘ
101. 11525/18 የተፈቀደ
102. 11528/18 የተፈቀደ
103. 11534/18 ተቀባይነት ያላገኘ
104. 11274/18 ተቀባይነት ያላገኘ
105. 11275/18 ተቀባይነት ያላገኘ
106. 11491/18 ተቀባይነት ያላገኘ
107. 11518/18 ተቀባይነት ያላገኘ
108. 11538/18 ተቀባይነት ያላገኘ
109. 11431/18 ተቀባይነት ያላገኘ
110. 11510/18 ተቀባይነት ያላገኘ
111. 11513/18 የተፈቀደ
112. 11521/18 ተቀባይነት ያላገኘ
113. 11508/18 ተቀባይነት ያላገኘ

*ማስታወሻ*
1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣ ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች) መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡
2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

በአደራ በተሰጠ ዕቃ ላይ የሚፈጸሙ  የሙስና ወንጀሎች እና የህግ ተጠያቂነት የኢፌዴሪ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007  አንቀጽ 14 መሰረት ተደርጎ የተዘጋጀ ጠበቃ አደም ሰይድ ከ...
27/08/2026

በአደራ በተሰጠ ዕቃ ላይ የሚፈጸሙ የሙስና ወንጀሎች እና የህግ ተጠያቂነት የኢፌዴሪ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 14 መሰረት ተደርጎ የተዘጋጀ
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
🛑የኢፌዴሪ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2014 አንቀጽ 14 በዋነኝነት ትኩረት የሚያደርገው በመንግሥት መስሪያ ቤት ውስጥ አደራ በተጣለበት ንብረት፣ ሰነድ ወይም ታሸገ ዕቃ ላይ ያለአግባብ ማዘዝን ለመግታት ነው። የመንግሥት አሰራር በታማኝነት፣ በምስጢር ጥበቃ እና በኃላፊነት ስሜት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ፣ አደራ የተሰጠውን ማናቸውንም ዕቃ ያለህግ አግባብ መክፈት፣ ማዘገየት፣ መጠቀም ወይም ለሌላ ወገን አሳልፎ መስጠት አጥፊውን ለወንጀል ተጠያቂነት ይዳርጋል። የዚህ አንቀጽ ዋና ዓላማ የመንግሥትና የሕዝብ ንብረት እንዳይባክን፣ የሰነዶች ምስጢራዊነት እንዳይጣስ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ግልጽነትና ታማኝነት እንዲጠበቅ ማድረግ ነው
🛑በንኡስ አንቀጽ 1 መሠረት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የግል ንብረት ለማድረግ ሳያስብ ነገር ግን በሕግ ሳይፈቀድለት አደራ የተቀበለውን ወይም እንዲታሸግ የተሰጠውን ኢንቨሎፕ፣ ፓኬጅ ወይም ሰነድ የከፈተ፣ ያዘገየ፣ የወሰደ፣ ያነሳ ወይም ለሌላ ሰው አሳልፎ የሰጠ እንዲሁም የተጠቀመበት እንደሆነ በዚሕ አንቀጽ ይቀጣል።
▶️​ምሳሌ 1፡ አህመድ በፖስታ አገልግሎት ድርጅት ውስጥ ታሽገው የሚላኩ ሰነዶችን የሚቀበል ሠራተኛ ነው። አህመድ ታሽጎ የመጣውን የፈተና ሰነድ ይዘት ለማወቅ ፈልጎ ያለአግባብ እሽጉን ቢከፍተው ወይም ቢያዘገየው፣ ምንም እንኳ ለራሱ የግል ጥቅም ባያውለውም በዚሁ ንኡስ አንቀጽ መሠረት ከ7,000 ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል።
🛑​ ለራሱ ጥቅም ለማግኘት የተፈጸመ ወንጀል፡-በንኡስ አንቀጽ 2 ሥር የተጠቀሰው ደግሞ ወንጀሉ የተፈጸመው ሠራተኛው "ለራሱ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ" ሲሆን የሚጣልበትን የቅጣት ደረጃ ያከብደዋል። እዚህ ላይ የግል ጥቅም የማግኘት እቅድ ወይም ፍላጎት መኖሩ ቅጣቱን ከቀላል እስራት ወደ ፅኑ እስራት ያሸጋግረዋል።
▶️​ምሳሌ 2፡ ፋጡማ በጉምሩክ ባለሥልጣን ታሽገው የተቀመጡ ዕቃዎችን የምትጠብቅ ሠራተኛ ብትሆን እና ታሽጎ የተቀመጠውን ውድ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃ እሽግ ከፍታ ለራሷ ጥቅም ብታውለው ወይም ለሌላ ሰው አሳልፋ ብትሸጠው፣ ወንጀሉን ለግል ጥቅሟ ስላከናወነችው ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት እና ከ3,000 ብር በማይበልጥ መቀጮ፤ ወይም ከ7 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና እስከ 20,000 ብር በሚደርስ መቀጮ ትቀጣለች።
​🛑በንኡስ አንቀጽ 3 ወንጀሉን የበለጠ ከባድ የሚያደርጉ ሁለት ዋና ዋና ሁኔታዎችን ያስቀምጣል፤ እነሱም የተገኘው ጥቅም "ከፍተኛ" መሆን ወይም የጥፋተኛው "የኃላፊነትና የሥልጣን ደረጃ" ከፍተኛ መሆን ናቸው። ከፍተኛ ኃላፊነት ያለው ሰው አደራን ሲያጉድል በሕዝብና በመንግሥት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት የጎላ በመሆኑ ቅጣቱ በጽኑ እስራት እንዲጠናከር ተደርጓል።
▶️​ምሳሌ፡ ኡመር የአንድ የመንግሥት ልማት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር (ከፍተኛ ባለሥልጣን) ሲሆን፣ በቢሮው አደራ ተጠብቆ እንዲቆይ የተደረገን ሚሊዮን ብሮች የሚያወጣ የጨረታ ሰነድ እሽግ በማፍረስ ለራሱ ወዳጅ ኩባንያ አሳልፎ ቢሰጥ እና ከፍተኛ ጥቅም ቢያገኝ፣ በሥልጣኑ ደረጃ እና በጠየቀው ጥቅም መጠን ምክንያት ቅጣቱ ከ5 ዓመት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና ከ5,000 እስከ 30,000 ብር በሚደርስ መቀጮ ይወሰንበታል።
​🛑 በቸልተኝነት የሚፈጸም ጥፋት
የመጨረሻው ንኡስ አንቀጽ 4 የሚያተኩረው ወንጀሉ ሆነ ተብሎ (በሐሳብ) ሳይሆን "በቸልተኝነት" (በጥንቃቄ ጉድለት) በሚፈጸምበት ጊዜ ባለው ተጠያቂነት ላይ ነው። ሠራተኛው አደራ የተቀበለውን ዕቃ በጥንቃቄ ባለመጠበቁ ወይም በቸልተኝነቱ ምክንያት አደጋ ላይ እንዲወድቅ ካደረገ የወንጀል ሐሳብ ባይኖረውም ቅጣት ይጥልበታል።
▶️​ምሳሌ፡ ዘይነብ በመንግሥት መሥሪያ ቤት የካዝና ቁልፍ እና የታሸጉ ሰነዶች ያዥ የሚል ሠራተኛ ነው። ዘይነብ ቢሮውን ሳታስብ ክፍት አድርጎ በመሄዱ ወይም አደራ የተሰጠውን ፓኬጅ በቸልተኝነት ጠረጴዛ ላይ ትቶ በመውጣቱ ምክንያት እሽጉ ቢጎዳ ወይም ቢጠፋ፣ ድርጊቱ በቸልተኝነት የተፈጸመ በመሆኑ እስከ 2,000 ብር በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል።
ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል

📍 አድራሻ፦ አዲስ አበባ | ደሴ (ወሎ) | ኮምቦልቻ
📞 ስልክ፦ +251910214108
📧 ኢሜይል፦ [email protected]
📱 ቴሌግራም፦ https://t.me/adem2141

በውርስ ሕግ አተረጓጎም ዙሪያ በተሰጡ አንዳንድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጎሞች ላይ የቀረበ ትችት(አስተማሪ ጽሑፍ ነው ያነቡ  ዘንድ ተጋበዙ)✅✅✅✅✅✅...
27/08/2026

በውርስ ሕግ አተረጓጎም ዙሪያ በተሰጡ አንዳንድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጎሞች ላይ የቀረበ ትችት
(አስተማሪ ጽሑፍ ነው ያነቡ ዘንድ ተጋበዙ)
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
1) ስጦታ (donation) እና የኑዛዜ ስጦታዎች (legacy)

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ግንቦት 21/2000 ዓ.ም በሰጠዉ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም፡-

"የቁም ስጦታ /donation intervivous/ እና የኑዛዜ ስጦታ(donation mortis causa/ የተለያዩ ናቸው። ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም የኑዛዜ የቁም ስጦታን የኢትዮጵያ ሕግ ስጦታ ነው ብሎ እውቅናና ጥበቃ አይሰጠውም። የኑዛዜ የቁም ስጦታዎች የሚገዙት ስለ ኑዛዜ በተደነገገው የሕግ ክፍል ነው። የኢትዮጵያ ሕግ ስጦታ ነው በማለት እውቅና እና ጥበቃ የሚያደርግለት የቁም ስጦታን ነው። አንድ ሰው ቤቱን በቁም ኑዛዜ ስጦታ ለወራሹ ቢሰጥ በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 መሠረት ቤቱ የቁም ኑዛዜ ስጦታ ላደረገላቸው በክፍፍል ወቅት እንዲደርሳቸው ያለውን ፍላጎት የሚያሳይ እንጂ የተለየ ስጦታ መስጠቱን አያመለክትም።"

በሚል ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ከውርስ ሕጉ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 912 እንደምንገነዘበው በውርስ ሕግ ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ (universal title legacy) እና ልዩ የኑዛዜ ስጦታዎች (singular title legacy) መኖራቸው ተገልጧል፡፡ እዚህ ላይ መገንዘብ ያለብን በእግሊዘኛው (legacy) በሚል የተጠቀሰው ቃል በአማርኛ ስጦታ ተብሎ ስለተተረጎመ በእንግሊዘኛ (legacy) በሚል ተገልጾ በአማርኛ የኑዛዜ ስጦታ በሚል የተተረጎመው ቃል ከመደበኛው ስጦታ (donation) የተለየ ሃሳብ መሆኑን ነው፡፡ ምንም እንኳን ሌጋሲ በአማርኛ ስጦታ በሚል ትርጉም የተሰጠው ቢሆንም legacy (የኑዛዜ ስጦታ) እና donation (ስጦታ) የተለያዩ ሃሳቦች ናቸው፡፡

Legacy (የኑዛዜ ስጦታ) በኑዛዜ ንብረት መስጠትን የሚያመላክት ሲሆን ኑዛዜ በመሆኑም ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ donation (ስጦታ) ግን በጠቅላለው የሚፈጸምበት ሟች ከመሞቱ በኋላ ይሁን በፊት አንድን ንብረት በችሮታ ለሌላ መልቀቅን የሚመለከት ሰፊ ሃሳብ የያዘ ነው ፡፡ Legacy (የኑዛዜ ስጦታ) በ donation (ስጦታ) ስር የሚገኝ ንዑስ ሃሳብ ነው፡፡

ስለሆነም Legacy (የኑዛዜ ስጦታ) እና donation (ስጦታ) የሚሉ ቃሎችን ስጦታ ከሚል እኩል መልክት እንዳላቸዉ አድርጎ ማየት የለብንም፡፡

ታዋቂዉ የሕግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ legacy is a gift by will በሚል ተርጉሞ donate to give property without receiving consedration for the transfere በሚል ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ ብላክስ ሎዉ እንደተረጎመዉ ሌጋሲ ማለት በኑዛዜ የሚሰጥ የስጦታ አይነት ሲሆን ስጦታ ደግሞ በምላሹ ዋጋ ሳይቀበሉ ንብረትን ማስተላለፍ የሚመለከት ሰፊ ጥቅል ሃሳብ ነዉ፡፡
በተጨማሪም Legacy እና donation ስጦታ የሚል እኩል መልክት የማያስተላልፉ እና የሕጉም እሳቤ ይህ አለመሆኑን ከውርስ ሕጉ ከራሱ ድንጋጌዎች ጋር ማየት ተገቢነት አለው፡፡

በፍ/ብ/ህ/ቁ 1117 ወላጆች በህይወት እያሉ ንብረታቸውን ለተወላጆቻቸው ማካፈል እንደሚችሉ እና ይህም ስጦታ በቁም ስለሚደረጉ ስጦታዎች አፈጻጸም እንደሚገዛ ተመላክቷል ፡፡ ይህን የመሰለው ስጦታ በውርስ ሕጉ የተገለጸው legacy በሚል ሳይሆን donation በሚል ቃል ነው፡፡ ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ስጦታ legacy ሲሆን ሰጪው በህይወት እያለ የሚፈጸም ሲሆን ደግሞ (donation) ይሆናል፡፡ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1067 (2) እና (3) የሁለቱን ስጦታዎች አይነት ልዩነት ይበልጥ እንገነዘባለን፡፡ ከእነዚህ ድንጋጌዎች legacy የሚለው ቃል ምንም እንኳ የኑዛዜ ስጦታ በሚል ቢገለጽም donation ከሚለው የጠበበ መሆኑን የሚያስመዘግበን ነው፡፡ ስለሆነም በውርስ ሕጉ (legacy) በሚል የተገጹ ቃሎችን ስጦታ donation ከሚለው ጋር አንድ እና ተመሳሳይ አድርጎ ማየት ስህተት ነው፡፡

2) የቁም ስጦታ/ስጦታ ሰጪዉ በህይወት እያለ የሚፈጸም ስጦታ /donation intervivous/ እና የኑዛዜ ስጦታ/ስጦታ ሰጪዉ ከሞተ በኋላ የሚፈጸም/ (donation mortis causa/

በዉርስ እና በስጦታ ክርክሮች ላይ አብዛኛዉን ጊዜ ሰነዱ የቁም ስጦታ ነዉ ወይስ የኑዛዜ ስጦታ ነዉ? አንድ ሰነድ የኑዛዜ ስጦታ መሆኑ እና የቁም ስጦታ መሆኑ የሚለየዉ እንዴት ነዉ? የሚለዉን መመርመር የዉርስ ሕጉን የበለጠ ለመረዳት እና በተግባር የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ጠቃሚ በመሆኑ ልንመረምረዉ የሚገባ ጉዳይ ነዉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ች ሁለት የተለያዩ ዉሳኔዎችን የሰጠ መሆኑ ነገሩን ይበልጥ ያወሳስበዋል፡፡ በመሆኑም ሁለቱንም የሰበር የሕግ ትርጉሞች አንስተን ተገቢነታቸዉን እንዳስሳለን፡፡

የሰ/መ/ቁ.189118፡- ሟች መስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም በተደረገ የስጦታ ውል ለክርክር መነሻ የሆነውን ቤት ለአንደኛው ወራሽ ሰጥተው እሳቸው ከ28 ቀን በኋላ ጥቅምት 26 ቀን 2006 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ የስጦታ ውሉ እንዲፈጸም እየተጠየቀ ያለው ከሟቹ ሞት በኋላ ከሆነ ሟች አድርገዋል የተባለው የስጦታ ውል የሚፈጸመው ከሟች ሞት በኋላ ስለሆነ በሞት ምክንያት የተደረገ ስጦታ እንደሆነ የሚያስገነዝብ ነው፡፡ በሞት ምክንያት የተደረገ ስጦታ ደግሞ ስለኑዛዜ የተነገሩት ድንጋጌዎች ተፈጻሚዎች እንደሚሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ.2428 ድንጋጌ ያመለክታል፡፡ በመሆኑም የግራ ቀኛቸውን ክርክር መነሻ በማድረግ አግባብነት ያላቸውን ስለኑዛዜ የተነገሩትን ድንጋጌዎች ማየቱ ተገቢ ነው፡፡

ሟች ካላቸው የውርስ ሀብት ውስጥ የመኖሪያ ቤታቸውን በስጦታ ውል ሰጥተው የቀራቸው የውርስ ንብረት እጅግ አነስተኛ ሆኖ ለሌሎች ወራሾች ከቀረው የውርስ ሀብት አንጻር ሲታይ የሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ እጅግ አነስተኛ ከሆነ ጉዳዩ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ.1123 ድንጋጌ አንጻር የሚታይ ይሆናል፡፡ የዚህ ድንጋጌ ተፈጻሚነት ሲታይ አባት እና እናት ያላቸውን ሀብቶች ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ለልጆቻቸው እና ወደ ታች ለሚቆጠሩ ተወላጆቻቸው ለመስጠት እና ለማከፋፈል መብት ያላቸው ቢሆንም ይህ የስጦታ አከፋፈል ወደ ታች ከሚቆጠሩ ተወላጆች አንዱ ከሚደርሰው ከሩብ የበለጠ ጉዳት ደርሶበት እንደሆነ የስጦታ ክፍፍሉ ቀሪ ሊደረግ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡

ሌሎች ወራሾች ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ያልደረሳቸው ሳይሆን የደረሳቸው ድርሻ ግን አነስተኛ ከሆነ እነዚህ የሟች ወራሾች ከሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ አነስተኛ ደርሷቸዋል ከሚባል በስተቀር ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ድርሻ እንዳላገኙ ተነቅለዋል የሚያስብል አይደለም በሚል የካቲት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል። ነገር ግን በሚቀጥለው የሰበር መዝገብ ከዚሁ ጋር የማይስማማ ትርጉም እንደሚከተለው ተሰጥቷል፡፡

ሰ/መ/ቁ/196783፡- የስጦታ ውል አደራረግ በባህሪው ሁለት ዓይነት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2428 ድንጋጌ ያሣያል። አንደኛው ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ወይም የሚተላለፍ መብት/donation mortis causa/ የሚመለከት ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ የሥጦታ ውል የኑዛዜ ዓይነት ሆኖ ስለኑዛዜ የተደነገው ደንብ ተፈጻሚነት የሚኖረው ሲሆን ሌላኛው የሥጦታ ዓይነት የቁም ስጦታ ወይም ሰጪው በህይወት እያለ የሚፈጸም/donation inter vivos/ የሚባለው ዓይነት ነው። በሁለቱ መካከል የሚኖረው መሠረታዊ ልዩነት የመጀመሪያው ተፈጻሚነቱ ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ እንደመሆኑ ውሉ የሚታየው በኑዛዜ ዓይነት ሆኖ ጉዳዩም ስለኑዛዜ በተደነገገው ሕግ መሠረት የሚታይ ሲሆን ሁለተኛው ግን ስጦታ ሰጪው በሕይወት እያለ የሚፈጸም በመሆኑ በስጦታ ሰጪው እና በስጦታ ተቀባዩ መካከል የሚኖረው መብትና ግዴታ ስለሥጦታ ውል በተደነገገው ደንብ የሚገዛ መሆኑ ነው። አንድ የሥጦታ ውል ከሁለቱ በየትኛው ዓይነት ይፈረጃል የሚለውን ለመለየት የሚቻለው እንዴት ነው ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጠን የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2428 ነው። ከዚህ ድንጋጌ ይዘት መገንዘብ እንደሚቻለው ስጦታ ውሉ ላይ ስጦታው ተፈጻሚ የሚሆነው ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ መሆኑን የሚያመላከት ቃል መኖሩ ከተረጋገጠ የስጦታው ዓይነት ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ወይም የሚተላለፍ በመሆኑ ልክ እንደኑዛዜ የሚታይ ይሆናል ማለት ነው።

የቤቱ ስመ-ሀብት ወደ ስጦታ ተቀባይ አለመተላላፉ ብቻውን የስጦታውን ዓይነት ስጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም የሥጦታ ዓይነት ነው ሊያሠኝ የሚችል አይደለም። የስጦታ ውሉ የኑዛዜ ዓይነት ነው ለማለት የሚያሥችል ምክንያት ከሌለ ከውርስ መነቀል አለመነቀል ጉዳይ የሚመረመርበት አግባብ አይኖርም። ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም

ከእነዚህ ሁለት የሕግ ትርጉሞች መገንዘብ የሚቻለው በመጀመሪያው ውሳኔ ላይ ስጦታው የሚፈጸመው ሟች ከሞተ በኋላ ስለመሆኑ የሚያመላክት ቃል ከስጦታ ውሉ ላይ የለም፡፡ችሎቱ የገለጸው ስጦታው እንዲፈጸም የተጠየቀው ሟች ከሞተ በኃላ ከሆነ ስጦታው ሟች ከሞተ በኋላ እንደሚፈጸም (donation mortis causa / እንደሆነ ተደርጎ እንደሚወሰድ ሲሆን በሁለተኛው የችሎቱ ውሳኔ ላይ ግን የስጦታ ውሉ የእንዲፈጸም የተጠየቀበት ጊዜ ሳይሆን ስጦታ ሰጪው በህይወት እያለ የሚፈጸም /donation intervivous/ እና ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም (donation mortis causa/ የሚለውን ለመወሰን መታየት ያለበት ስጦታው እንዲፈጸም በተጠየቀበት ቀን ሰጪው ሞቶ ነበር ወይስ በህይዎት ነበር የሚለው ሳይሆን በስጦታ ውሉ ላይ ስጦታው ተፈጻሚ የሚሆነው መቸ እንደሆነ የሚያመላክት ቃል እና ይዘቱን በመመርመር ነው፡፡ የስጦታ ውሉ ስጦታ ሰጪው ከሞተ በኋላ ሚፈጸም መሆኑን የሚያመላከት ቃል መኖሩ ከተረጋገጠ የስጦታው ዓይነት ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ወይም የሚተላለፍ በመሆኑ ልክ እንደኑዛዜ የሚታይ ይሆናል፡፡ የስጦታ ውሉ ተፈጻሚነቱ እንደተደረገ ወይም ሟች በህይዎት እያለ መሆኑን ካላሳየ የስጦታ ውሉ ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም (donation mortis causa / ይሆናል የሚል ነው።

ስለሆነም የመጀመሪያው የሕግ ትርጉም ሟች ከሞተ በኋላ እንዲፈጸም የተጠየቀ ስጦታ ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም (donation mortis causa / የስጦታ አይነት አድርጎ የተረጎመ ሲሆን ሁለተኛው የሕግ ትርጉም ግን የስጦታውን አይነት የሚወሰነው መቼ እንዲፈጸም ተጠየቀ በሚለው ሳይሆን የስጦታ ውሉ መቸ እንደሚፈጸም እንደሚያዝዝ የስጦታ ውሉ ይዘት ታይቶ ነው የሚሉ ስለሆኑ ሁለቱም የሚቃረኑ ወይም አብረው የሚሄዱ የሕግ ትርጉሞች አይደሉም፡፡

የፍ/ብ/ህ/ቁ 2428 ሰጪው ሲሞት ይፈጸማሉ ተብለው በተወሰኑት ስጦታዎች ላይ ስለ ኑዛዜ የተነገሩት ድንጋጌዎች ተፈጻሚዎች ይሆናሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጊ በግልጽ መገንዘብ እንደሚቻለው አንድ ስጦታ ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም (donation mortis causa) መሆኑ የሚለየው ስጦታው ሰጪው ሲሞት ይፈጸማል የሚል ከሆነ እንጂ ሰጪው ከሞተ በኋላ ስጦታው እንዲፈጸም ስለተጠየቀ ወይም ክስ የቀረበዉ ስጦታ ሰጪዉ ከሞተ በኋላ ስለሆነ አይደለም፡፡

የፍ/ብ/ህ/ቁ 2428 በሞት ምክንያት የተደረገ ስጦታ የሚል እርስ የተሰጠው ቢሆንም በእንደሊዘኛው donation mortis causa በሚል ስለተገለጸ ሰጪው ሊሞት ሲል ወይም ስጦታው ከተደረገ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰጪዉ ስለሞተ ብቻ ከሞት በኋላ የሚፈጸም ነው አያስብልም ፡፡በሞት ምክንያት የተደረገ ስጦታም ሌላ አይነት የስጦታ አይነት አለመሆኑን ከእንግሊዘኛው ትርጉም እንረዳለን፡፡

ስለሆነም አንድ ስጦታ ከሁለቱ የስጦታ አይነቶች የትኛው አይነት ስጦታ ነው ብሎ ለመለየት እንዲፈጸም የተጠየቀበት ጊዜ ሳይሆን መቸ እንደሚፈጸም የውሉ ይዘት ታይቶ የሚለይ በመሆኑ እና ሟች በህይወት እያለ ሊፈጸም የሚችል ስጦታ ሆኖ ነገር ግን ሟች ከሞተ በኋላ እንዲፈጸም መጠየቁ የስጦታውን አይነት ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ስጦታ (donation mortis causa) ስለማያደርገው የመጀመሪያው የሰበር ትርጉም ቀሪ ሊሆን የሚገባው ነው፡፡

በአጠቃላይ የስጦታ ውል አደራረግ በባህሪው ሰጪው በህይወት እያለ የሚፈጸም /donation intervivous/ እና ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚፈጸም (donation mortis causa / በሚል በሁለት ተከፍሎ የሚታይ መሆኑን ከፍ/ብ/ህ/ቁ 2428 የምንገነዘበው ነው፡፡ሁለቱ አይነት ስጦታዎች ህጋዊ ተቀባይነትን ለማግኘት የሚገዙባቸው ስርዓቶች የተለያየ ነው፡፡የመጀመሪያው የስጦታ አይነት ስጦታው የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን በግልጽ ኑዛዜ ፎርም መሠረት የሚገዛ ሲሆን ሁለተኛው አይነት ስጦታ የስጦታው ንብረት የሚንቀሳቀስም ይሁን የማይንቀሳቀስ ከኑዛዜ ሕግ አንጻር የሚታይ ነው ፡፡ በእርግጥ እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባው ሰጪው ሲሞት ይፈጸማሉ ተብለው የሚደረጉ ስጦታዎች በፍታብሄር ሕጉ ስለ ስጦታ በተደነገገው ምዕራፍ ስር ጉዳዩ የሚገዛበት የሕግ ክፍል ከመመላከቱ ውጪ እንደ ስጦታ የሚታይ ነው ወይ የሚለው ሊታይ ይገባዋል፡፡ ይህንን ሃሳብ በሚቀጥለው ክፍል እንመረምራለን፡፡

3) በውርስ ሊደርሰው ከሚገባው ከሩብ በላይ ማጣት ከውርስ መነቀል ስላለመሆኑ

ከፍ ብሎ በተራ ቁጥር 1 ባለው እርዕስ ስለ legacy (የኑዛዜ ስጦታ) እና donation (ስጦታ) ልዩነት እና አንድነት ያነሳሁት ከፍ ብሎ በመጀመሪያ በተጠቀሰው የሰበር ችሎቱ የሕግ ትርጉም ላይ ስጦታዉ የኑዛዜ ስጦታ መሆኑን ተቀብሎ እያለ፡-

"ስለሆነም ሟች ካላቸው የውርስ ሀብት ውስጥ የመኖሪያ ቤታቸውን በስጦታ ውል ሰጥተው ( በሞት ምክንየት በተደረገ ስጦታ) የቀራቸው የውርስ ንብረት እጅግ አነስተኛ ሆኖ ለሌሎች ወራሾች ከቀረው የውርስ ሀብት አንጻር ሲታይ የሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ እጅግ አነስተኛ ከሆነ ጉዳዩ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ.1123 ድንጋጌ አንጻር የሚታይ ይሆናል፡፡ የዚህ ድንጋጌ ተፈጻሚነት ሲታይ አባት እና እናት ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ለልጆቻቸው እና ወደ ታች ለሚቆጠሩ ተወላጆቻቸው ያላቸውን ሀብቶች ለመስጠት እና ለማከፋፈል መብት ያላቸው ቢሆንም ይህ የስጦታ አከፋፈል ወደ ታች ከሚቆጠሩ ተወላጆች አንዱ ከሚደርሰው ከሩብ የበለጠ ጉዳት ደርሶበት እንደሆነ የስጦታ ክፍፍሉ ቀሪ ሊደረግ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡---"

በሚል የሰጠው የሕግ ትንታኔ የኑዛዜ ስጦታን legacy እና ስጦታን (donation) ሃሳብን በመቀላቀል የተሰጠ ስለሆነ ነው፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 የሚገኘው የተከፋፈሉ ስጦታዎች (partition made by donations) በሚለው ክፍል ስር ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ የሚያወራው ስለ ኑዛዜ ስጦታ (legacy) ሳይሆን ስለ ስጦታ (donation) ነው፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 መጎዳት ተግባራዊ የሚሆነው እና ተፈጻሚነቱ በኑዛዜ ስጦታ (legacy) ሳይሆን በስጦታ (donation) ላይ ነው፡፡ ስለሆነም በኑዛዜ ስጦታ (legacy) ላይ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (1) መሠረት ከሩብ በላይ ጉዳት ደርሶብኛል የስጦታ አከፋፈሉ ይቅር ብሎ ሊጠይቅ አይችልም፡፡ በኑዛዜ ስጦታ (legacy) ላይ ከሩብ በላይ ድርሻ አጥቻለሁ፤ ኑዛዜው ይሻርልኝ ወይም ክፍያው ቀሪ ይሁንልኝ የሚሉ ክርክሮች በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 መሠረት ተቀባይነት አግኝተው በርካታ የሰበር ውሳኔዎች አሉ፡፡ ነገር ግን ከሕጉ አቀራረጽ በኑዛዜ ስጦታ (legacy) ከሩብ በላይ ጉዳት በሚያደርስ ሁኔታ ለተወላጅ ኑዛዜ ማድረግ ከፍታብሄር ሕግ ቁጥር 1123 እንደማይገናኝ የምንገነዘበዉ ሲሆን ተናዛዡም ተወላጁን እስካልነቀለው ድረስ ከሩብ በላይ ያለምክንየት ማሳጣት ሕጉ አይከለክለውም፡፡

በዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ እምነት በፍታሃብሄር ሕጉ መንቀል (disherison) ከኑዛዜ ስጦታ ጋር እንጂ ከድርሻ ማነስ (lesion) ጋር በምንም አይገናኝም፡፡ እንዲሁም ድርሻ ማነስ (lession) ከ(donation) ጋር እንጂ ከኑዛዜ ስጦታ (legacy) ጋር አይገናኝም፡፡ አንደኛው የሌላኛውን ውጤትም አይወስድም፡፡

ስለመነቀል የሚያደነግጉት የፍ/ብ/ህ/ቁ 937፤938፤939 እና ሌሎችም የመነቀል ሃሳቦች ተናዛዥ ንብረቱን ከሞተ በኋላ በኑዛዜ ስጦታ (legacy) የሚያስተላለፍበትን አግባብ የሚመለከቱ እንጂ ሟች በህይወት እያለ ስለሚፈጸም ስጦታ (donation) ወይም የስጦታ ክፍፍል (partition made by donation) የሚመለከቱ አይደሉም፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 መነሻ እና መሠረቱ ከዚሁ ድንጋጌ ከፍ ብሎ የተቀመጠዉ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1117 የተከፋፈሉ ስጦታዎች (partition made by donations) የሚለው የሕጉ ክፍል ነው፡፡ ይህ የሕግ ክፍልም ወላጆች በህይወት እያሉ ከመሞታቸው በፊት ንብረታቸውን ለተወላጆቻቸው በስጦታ (donation) ባከፋፈሉ ጊዜ በሚነሳ ክርክር ተፈጻሚ የሚሆን የሕግ ክፍል ነው፡፡ በዚህ የሕግ ክፍል የሚገዛው ስለ የስጦታ ውል (donation) ብቻ ነው፡፡ በዚህ የሕግ ክፍል እና በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 የተጠቀመው ቃል (legacy) በሚል ሳይሆን (donation) በሚል ነው፡፡

ወላጆች በህይወት እያሉ የሚፈጸም የስጦታ አከፋፈል በቁም ስለሚደረጉ ስጦታዎች (በመደበኛዉ የስጦታ የሕግ ክፍል ) በተደነገጉት ደንቦች መሠረት መፈጸም አለበት በሚል በፍ/ብ/ህ/ቁ 1119 የተደነገገዉም የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 የስጦታ ዉልን እንጅ የኑዛዜ ስጦታን የማያሳይ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነዉ፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 ወላጆች በህይወት እያሉ ንብረታቸውን በስጦታ ባከፋፈሉ ጊዜ ተወላጆች ይህ የስጦታ ክፍፍል ባይደረግ ኖሮ ሊደረሰው ከሚገባው የውርስ ድርሻው ከ1/4ኛ በላይ እንዳያሳጡት ገደብ የሚጥል እንጅ ወላጅ የኑዛዜ ስጦታ (legacy) ሲያደርግ ተወላጁን ሊደርሰው ከሚገባው ከ1/4ኛ በላይ እንዳያሳጣው የሚከለክል ድንጋጌ አይደለም፡፡ ድንጋጌው የስጦታ ክፍፍል ባይኖር ኖሮ ይላል እንጂ ኑዛዜ ባይኖር ኖሮ አይልም፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ድንጋጌ አንድ አይነት ሃሳብ በሌለው በኑዛዜ ስጦታ (legacy) ላይ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይችልም፡፡ የዚህ የሕግ ክፍል ተፈጻሚነት በስጦታ ውል (partition by donation) ላይ ብቻ ነው፡፡ስለሆነም በኑዛዜ ስጦታ ጊዜ ሟች በኑዛዜዉ ተወላጅን ከሩብ በላይ እንዳያሳጣ የሕግ ገደብ የለበትም፡፡

ለትችት በተያዘው ከላይ በተገለጸው የሰ/መ/ቁ.189118 የሰበር ችሎቱ በአንድ በኩል ሟች ያደረጉት ኑዛዜ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2428 መሠረት ሟች ከሞተ በኋላ የሚፈጸም ስጦታ ነው ብሎ ወረድ ብሎ ግን የድርሻ መጠንን በሚመለከት ሲያትት

"-----በስጦታ ውል ሰጥተው የቀራቸው የውርስ ንብረት እጅግ አነስተኛ ሆኖ ለሌሎች ወራሾች ከቀረው የውርስ ሀብት አንጻር ሲታይ የሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ እጅግ አነስተኛ ከሆነ ጉዳዩ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ.1123 ድንጋጌ አንጻር የሚታይ ይሆናል፡፡"

በሚል የደረሰበት መደምደሚያ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1117-1123 ተፈጻሚነት ሟች ከሞተ በኋላ በውርስ ማጣራት ታልፎ ለሚደረግ የኑዛዜ ስጦታ ( legacy ) ሳይሆን ሟች በህይወት እያለ ለተወላጆቹ አስቀድሞ በሚያደርገው ስጦታ ለሚያደረግ ክፍፍል መሆኑን ያላገናዘበ ነው፡፡
በእርግጥ በዚሁ መዝገብ ችሎቱ

"----የዚህ ድንጋጌ ተፈጻሚነት (የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ማለት ነው) ሲታይ አባት እና እናት ያላቸውን ሀብቶች ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ለልጆቻቸው እና ወደ ታች ለሚቆጠሩ ተወላጆቻቸው ለመስጠት እና ለማከፋፈል መብት ያላቸው ቢሆንም ይህ የስጦታ አከፋፈል ወደ ታች ከሚቆጠሩ ተወላጆች አንዱ ከሚደርሰው ከሩብ የበለጠ ጉዳት ደርሶበት እንደሆነ የስጦታ ክፍፍሉ ቀሪ ሊደረግ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡"

በሚል ጠቅሷል ፡፡
የዚህ የሕግ ትርጉም የችግሩ መንስዔ የሚመነጨው ወላጆች ለተወላጆች በፍ/ብ/ህ/ቁ 1117 መሠረት ክፍፍል የሚያደርጉት በኑዛዜ ስጦታ ነው ወይስ በስጦታ ማለትም ከመሞታቸው በፊት በሚፈጸም ስጦታ ነዉ ወይስ ከሞቱ በኋላ በሚፈጸመው የሚለውን አለመለየቱ ነው፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (3) የስጦታ ክፍያ እንዲቀር የሚደረገው ወደ ላይ የሚቆጠረው ስጦታ አድራጊው ወላጅ በሞተ በሁለት አመት ውስጥ እና የስጦታው መከፋፈል ከተደረገበት ቀን አንስቶ በአስር አመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ በቀር ዋጋ የሌለው ይሆናል በሚል የይርጋ ድንጋጌ አስቀምጧል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ በግልጽ የምንገነዘበው የድንጋጌው ተፈጻሚነት ሟች በህይወት እያለ በስጦታ ባከፋፈለን መሠረት ሊደርሰኝ ከሚገባው 1/4ኛ ድርሻ በላይ ስላጣሁ በሚል የሚቀርብ ክስ ሟች ከሞተ በሁለት አመት ውስጥ ወይም በአማራጭ የስጦታ ክፍፍሉ ከተደረገ በአስር አመት ውስጥ መቅረብ እንዳለበት ነው፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሠረት የስጦታ ክፍፍሉ ከተደረገ በኋላ የስጦታ ክፍፍል ያደረገው ሰው ክፍፍሉን ከፈጸመ በኋላ አስር አመት በህይወት ከቆየ ሊደረሰኝ ከሚገባው ከሩብ በላይ አጥቻለሁ ወይም ድርሻ አንሶኛል በማለት ክስ ለማቅረብ የጊዜ ገደብ የሚያልፍባቸው መሆኑን ነው፡፡

ይህን ክፍፍል እንደ ኑዛዜ ስጦታ ማለትም ሟች ከሞተ በኋላ እንደሚደረግ ድልድል ካየነው ሟች በኑዛዜ ለተወላጆቹ የኑዛዜ ስጦታ አድረጎ ኑዛዜውን ካደረገ በኃላ አስራ ሁለት አመት ቆይቶ ቢሞት ውርሱ ሲከፈት ልጆቹን በኑዛዜው ክፍፍል የተደረገው ሟች ከመሞቱ ከአስር አመት በፊት ስለተደረገ በይርጋ ታግዳችኋል ልንል ነውን? ኑዛዜ ግላዊ እና ሚስጥራዊ ከሆነበት ተፈጥሮው አውጥተን አስቀድሞ ለተወላጆች ያልተገለጸን እና የማያውቁትን ኑዛዜ ሟች ከሞተ በኋላ የሚከፈትን ኑዛዜ እና ከሟች መሞት በኋላ የሚያውቁትን ኑዛዜ ወላጃችሁ ድልድሉን ወይም ክፍፍሉን ካደረገ አስር አመት ሆኖታል ስለዚህ የመነቀል ጥያቄያችሁ ሟች በሞተ በወር ውስጥ ብታቀርቡም በይርጋ ታግዳችኋል ማለት ፍትሃዊ ነው? ይርጋው መቆጠር የሚጀምረው በመብታቸው መስራት ከጀመሩበት ሟች ከሞተበት ቀን ጀምሮ ነው እንዳንል ሟች ከሞተ በሁለት አመት ውስጥ ተብሎ ሌላ አማራጭ መሆኑ ተገልጧል፡፡ስለሆነም በኑዛዜ ስጦታ ከውርስ መነቀልን እና በስጦታ ክፍፍል አነስተኛ ድርሻ ማግኘትን አንድ አድርጎ በመውስድ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123`ን ተግባራዊ ማድረግ ከሕጉ ውጪ ነው፡፡

በአጭሩ በቁም ስጦታ ዉል በተደረገ ክፍፍል ተጎድቻለሁ ወይም ሊደረሰኝ ከሚገባዉ 1/4ኛ በላይ አጥቻለሁ የቁም ስጦታ ክፍፍሉ ይሻርልኝ በሚል አንድ ተወላጅ ክስ ለማቅረብ የግድ የስጦታ ሰጪዉን መሞት መጠበቅ የማይኖርበት መሆኑ በስጦታ ያከፋፈለዉን ተወላጅን ቸምሮ ሊከስ የሚችል መሆኑ በሌላ በኩል በኑዛዜ ተነቅያለሁ ኑዛዜዉ ይሻርልኝ የሚል ሰዉ የግድ ጥያቄዉን የሚያቀርበዉ ተናዛዡ ከሞተ በኋላ ወራሾችን ተከሳሽ በማድረግ መሆኑን መገንዘብ የሁለቱን ልዩነት ለመለየት ይረዳል፡፡

4 ) በኑዛዜ አነስተኛ ድርሻ ስለደረሰኝ (ከ1/4ኛ በላይ ስላጣሁ) ወይም በዝምታ በኑዛዜ ተነቅያለሁ ስለሆነም ኑዛዜው ይሻርልኝ የሚል ክስ የይርጋ ጊዜው በፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 (3) የተመለከተው አስር አመት ሊሆን የማይገባ ስለመሆኑ፡-

የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በበርካታ መዝገቦች በኑዛዜ አነስተኛ ድርሻ ስለደረሰኝ በኑዛዜ ተነቅያለሁ ስለሆነም ኑዛዜው ይሻርልኝ የሚል ክስ የይርጋ ጊዜው በፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 (3) የተመለከተው አስር አመት ነው እንጂ የፍ/ብ/ህ/ቁ 994 አይደለም በሚል በተደጋጋሚ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ነገር ግን ከፍ ሲል እንደገለጽሁት የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ከመነቀል ጋር የሚያያዝ ሳይሆን ሟቾች በህይወት እያሉ ንብረታቸውን ለተወላጆቻቸው ባከፋፈሉ ጊዜ የሚፈጸምበትን ሁኔታ ስለሚመለከት ከውርስ በዝምታ ተነቅያለሁ የሚል ወይም ድርሻ ስላነሰኝ በተዘዋዋሪ መንገድ ተነቅያለሁ የሚል ክስ ወደ ፊት በምገልጸው ምክንየት እንደየሁኔታው በፍ/ብ/ህ/ቁ 993 እና 994 ወይም በፍ/ብ/ህ/ቁ 1677 እና 1845 መሠረት አስር ዓመት ይሆናል እንጂ በፍብ/ህ/ቁ 1123(3) መሠረት አይገዛም፡፡

የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (3) ያስቀመጠው አማራጭ ሁለት የይርጋ ጊዜዎችን ነው፡፡ የመጀመሪያው ሟች ከሞተ ጀምሮ እስከ ሁለት አመት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ክፍፍሉ ከተፈጸመ በአስር አመት ውስጥ ነው፡፡ይህ ድንጋጌ ስለ ስጦታ (donation) እንጂ ስለኑዛዜ ስጦታ (legacy) የማያወራ በመሆኑ የኑዛዜ ስጦታ (legacy)`ን መነሻ ለሚያደርግ ጽንሰ ሃሳብ ከውርስ መነቀልንም ይመለከታል ሊባል አይቻልም፡፡ እንዲሁም አንድ ተወላጅ የስጦታ ክፍፍሉ እንዲሰረዝ ክስ ለማቅረብ የስጦታ አድራጊዉን ሞት መጠበቅ አይጠበቅበትም፡፡ ይልቁንም በስጦታ ንብረቱን ያከፋፈለዉን ወላጁን ጭምር ሊከሰዉ ይችላል፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (3) የኑዛዜ ስጦታን ይመለከታል ካልን ከውርስ የመነቀሉ ጉዳይ የይርጋ ጊዜዉ ሟች ከሞተ በኋላ በሁለት አመት ይርጋ ነው ብለን እንደገና ደግሞ በአማራጭ ሟች ከሞተ ጀምሮ በአስር አመት የሚታገደው ክፍፍል ከተደረገ ጀምሮ ነው ሊባል ነው፡፡ ምክንየቱም ስለ ኑዛዜ መሻር የምናወራዉ ሟች ከሞተ በኋላ ብቻ ነዉ፡፡

የኑዛዜ ስጦታ ክፍፍሉ ተደርጎ እስከ አስር አመት ሟች በህይወት ቢቆይ የመነቀል ጉዳይ ለማንሳት ያለው ጊዜ ሟች ከሞተ ጀምሮ እስከ ሁለት አመት ነው የሚል አንድምታም ይኖረዋል፡፡

እንደሚታወቀው ኑዛዜ የሚከፈተው እና ይፋ የሚሆነው ሟች ከሞተ በኋላ ውርሱ ተከፍቶ ማጣራት ሲጀመር ነው፡፡ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 965 እንደምነገነዘበው ኑዛዜ የሚከፈተው ሟች ከሞተ በኃላ በ40ኛው ቀን ሲሆን ኑዛዜው ከዚህ ቀን በኃላ ከተገኘ ከዚህ ቀን ዘግይቶ ምናልባትም ሟች ከሞተ ከሁለት አመት በኋላ ሊከፈት ይችላል፡፡ ስለሆነም ተከፍቶ ባልታወቀ ኑዛዜ ላይ ሟች ከሞተ በኋላ ከ2 ዓመት በኋላ ክስ ለማቅረብ በይርጋ ታግደሃል ሊባል አይገባም፡፡ ሁለተኛ ከውርስ የመነቀል ጉዳይ ሟች ከሞተ በኋላ በሁለት አመት ካልቀረበ በቁጥር 1123 (3) መሠረት በሁለት አመት ይታገዳል ካልን ትልቅ እና ሰፊ ለሆነው በፍ/ብ/ህ/ቁ 974 (2) እንደተመለከተው በውርስ ማጣራት ጊዜ ኑዛዜን ወይም ድልድልን ለመቃወም ሟች ከሞተ እስከ አምስት አመት የይርጋ ጊዜው እንደሆነ ካስቀመጠው ዘመን ያነሰ ጊዜ ሕግ አውጭው ያስቀምጣ ተብሎ አይታሰብም፡፡ ሶስተኛ የውርስ መነቀል ጉዳይ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (3) የተቀመጠው የሁለት አመት እና የአስር አመት ጊዜ ውስጥ የቱ እንደሚመረጥ እና ተግባራዊነቱ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ከሞተ በሁለት አመት እና ክፍፍል ከተደረገ በ10 ዓመት ውስጥ የተባለው ይህን ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ አራተኛ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (3) ላይ በመጎዳት ሊደርሰው ከሚገባው ከሩብ በላይ አጥቻለሁ በሚል የሚቀርበው ክስ አይነት እና የጊዜ ገደቡ የተቀመጠለት ጥያቄ በእንግሊዘኛው rescission የሚል ሲሆን በአማርኛው አከፋፈሉ እንዲቀር በሚል የተገለጸ ስለሆነ ቃሉ አስቀድሞ የተደረገ ክፍፍል መኖሩን ታሳቢ ያደረገ እንጂ ሰጪው ከሞተ በኋላ የሚደረግን የኑዛዜ ስጦታ ወይም የኑዛዜ ስጦታ ክፍፍልን የሚመለከት አለመሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡

5) በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የተመለከተው የክፍያ ደንብ ከፍ/ብ/ህ/ቁ.1117-እስከ-1123 ከተመለከቱ ድንጋጌዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የሌለው ስለመሆኑ፡-

አንድ ተወላጅ አንድን ንብረት ለተወላጁ መስጠቱ እንደ ክፍያ ደንብ እንጂ እንደ ኑዛዜ ስጦታ እንደማይታይ በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የተገለጸው መርህ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1117 እና 1123 እንደተገለጸው ወላጆች በህይወት እያሉ ንብረታቸዉን በስጦታ ባከፍፈሉበት ጊዜ ተፈጻሚነት የለውም፡፡ በመግቢያዉ እንተገለጸዉ ለችግሩ ሌላው መንስዔ ተመሳሳይ መልክት የሌላቸውን አንድ አይነት ቃላቶት ለተለያዩ ሃሳቦች ሕጉ መጠቀሙ ነው፡፡

በፍ/ብ/ህ/ቁ.1117 በአማርኛው የተከፋፈሉ ስጦታዎች (partition made by donation) በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 ደግሞ የኑዛዜ ስጦታና የክፍያ ደንብ (legacies and rule of partition) በሚል ተቀምጧል፡፡ እንግሊዘኛው ሌሎች ገላጭ ቃላቶች እንደተጠበቁ ሆነው ለሁለቱም የተለያዩ ሃሳቦች partition በሚል አንድ ቃል ገልጧል፡፡ አማርኛው ግን የተከፋፈሉ ስጦታዎች እና የክፍያ ደንብ በሚል በተለያዩ ቃላቶች ነው የገለጻቸው፡፡ከአማርኛው ከስሙ እንደምንረዳው የተከፈፈሉ ስጦታዎች የሚለው በተለይ የተከፋፈሉ የሚለው ቃል ያለፈ ነገርን አስቀድሞ ተደረገውን የሚያመላከት በመሆኑ ሟች በህይወት እያለ ውርሱ ከመከፈቱ በፊት የተደረጉ ስጦታዎችን እንደሚመለከት የሚያሳይ ነው፡፡የክፍያ ደንብ ማለት ደግሞ ምን ማለት እንደሆነ በጥንቃቄ ከሕጉ ላይ እንፈትሽ፡፡

በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 ሟች ተቃራኒ ሃሳብ በኑዛዜው ቃል ከሌለ በቀር ለተወላጁ አንድን ንብረት ወይም ከውርስ ሃብቱ አንድን ድርሻ መስጠቱ ተራ የሆነ የክፍያ ደንብ እንጂ እንደ ኑዛዜ ስጦታ አይቆጠርም ይላል፡፡ የሰበር ችሎቱን ጉዳዩን ወደ ፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 የመሰደው የዚህ ድንጋጌ አገላለጽ ስለሆነ በዚህ አንቀጽ የክፍያ ደንብ (rule of partition) ምንድን ነው? በየትኛው የሕጉ ክፍል የሚገኝ ሀሳብ ነው? ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ጋር ተመሳሳይ ነው ወይ? የሚለውን እንመርምር፡፡

የክፍያ ደንብ (rule of partition) የሚባለው ሃሳብ የሚመጣው ውርስ ተከፍቶ፤ ውርስ ተጣርቶ፤ የውርስ እዳው እና የልዩ ኑዛዜ ተጠቃሚዎች ክፍያ ተከፍሎ፤ የውርስ ሃብቱ ተሰብስቦ እና ወራሾች ተለይተው ከተጠናቀቀ በኃላ ለወራሾች የሚተርፈው ገንዘብ ተለይቶ ተጠናቆ ይህን የተጣራ ተራፊ የውርስ ሃብት ወራሾች እንዴት እንደሚከፋፈሉት የሚያሳይ የውርስ ንብረት ክፍፍል ስርዓቶችን የሚመለከት ነው ፡፡ እነዚህ የክፍያ ደንቦች (rule of partition) በፍትሃብሄር ሕጉ ቁጥር 1060 እስከ 1096 ያሉት ያሉት ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች የውርስ ሃብቱ ተጣርቶ ተጠናቆ ውርሱ ከተዘጋ በኋላ በማጣራቱ ሂደት ለወራሾች የሚተርፉት ንብረቶች በወራሾች መካከል በስምምነት፤ በኑዛዜው መሠረት፤ ንብረቱን አስገምተው በማካካስ፤ በእጣ ድልድል፤ በአይነት፤ በስምምነት በመሸጥ፤ በሃራጅ በመሸጥ ለወራሾች ሊካፈፈሉ እና ሊደለደሉ የሚችሉ መሆኑን በማመላከት የውርስ ሃብት ክፍፍል መፈጸሚያ መንገዶችን ወይም ስርዓቶችን የሚደነግጉ የክፍያ ደንቦች (rule of partition) ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ በተለይ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1083 ክፍያው የሚፈጸመው ሟች ባደረገው ኑዛዜ መሠረት ሲሆን ኑዛዜ ከሌለ በሕጉ በተመላከቱ የክፍያ ደንቦች ይፈጸማል በማለት ይደነግጋል፡፡ እንዲሁም የፍ/ብ/ህ/ቁ 980 የክፍያ ደንብ ስለማቋቋም በሚል እርስ ስር ውርሱ እንዴት እንደሚከፋፈል የትኛው የውርስ ሃብት ለማን እንደሚሆን ድልድል እንደሆነ አስቀምጧል፡፡

እነዚህን ድንጋጌዎች ከቁጥር 913 ጋር ስናያቸዉ ተቃራኒ አገላለጽ ከሌለ በስተቀር አንድ ወላጅ ለተወላጁ አንድን ንብረት ወይም ከውርስ ሃብቱ አንድን ድርሻ መስጠቱ ተራ የሆነ የክፍያ ደንብ እንጂ እንደ ኑዛዜ ስጦታ አይቆጠርም የሚለው ወላጅ ለተወላጁ በኑዛዜ አንድን ንብረት ወይም ድርሻ መስጠቱ ውርሱ ተጣርቶ ከተዘጋ በኋላ ተራፊ የውርስ ሃብቶች ለወራሾች ሲከፋፈሉ ወይም ለጊዜውም ድልድል ሲደረግ የክፍያ ደንቦች (rule of partition) ሲተገበር እነዚህ ንብረቶች ለተባሉት ተወላጆች እንዲደርሳቸው በኑዛዜ ማዘዛቸውን ያሳያል እንጂ የኑዛዜ ተጠቃሚ የሆኑ ልጆች እነዚህ በኑዛዜ የተደለደሉላቸው ንብረቶች ከግምት ሳይገቡ ቀሪውን የውርስ ሃብት ከሌሎች ወራሾች ጋር እኩል ልካፈል ማለት አይችሉም ማለት ነው፡፡

በፍ/ብ/ህ/ቁ 1086 ላይ የድርሻዎቹ አመዳደብ የሚለው rule of partition in kind በሚል በእንግሊዘኛ ተተርጉሞ በግልጽ መገኘቱም የክፍያ ደንብ (rule of partition) በሚል በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የተገለጸው ይህን የሕግ ክፍል እንጂ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1117-1123 ያለውን እንደማይመለከት የሚያስገነዝብ ነው፡፡

ሌላው የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123`ን ከፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የምናገኛኝበት ምክንየት የውርስ ጉዳይ መነሳት የሚችለው እና የውርስ ሕጉ ተግባራዊነት ተናዛዙ ከሞተ በኋላ ብቻ ነው ብለን ስለምናስብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ አስተሳሰብ ሁል ጊዜ ትክክል አይደለም፡፡ የእኛ ሃገር የፍታብሄር ሕግ የተቀዳበት የፈረንሳይ የፍታብሄር ሕግ የቁም ስጦታን እና የኑዛዜ ስጦታን በውርስ ሕጉ ክፍል በመጽሃፍ 3 የንብረት ማግኛ መንገዶች በሚለው ስር በእርእስ 3 ደንግጓል፡፡ በዚህም የፈረንሳይ ፍታብሄር ሕግ በእኛ የፍሃብሄር ሕግ ቁጥር 1117 የተከፋፈሉ ስጦታዎች (partition made by donation) የሚለውን (Distributions made by Father, Mother, or other ancestors, among descendants ) በሚል ነው የሚያስቀምጠው፡፡

በዚህ የፈረንሳይ የፍታብሄር ሕግ (Distributions made bay Father,Mother,or other ancestors, among descendants ) ተብሎ የተቀመጠው ሃሳብ በእኛ የፍትሃብሄር ሕግ የተከፋፈሉ ስጦታዎች (partition made by donation ) የሚለው ሃሳብ ስለመሆኑ በግልጽ ድንጋጌዎቹ የሚናገሩት ነው፡፡ ለማሳያ ያህል የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123(3) በስጦታው ሊደርሰው ከሚገባው ከ1/4ኛ በላይ ሊያጣ አይገባም የሚለው ከላይ በተገለጸው የፈረንሳይ የፍታብሄር ሕግ የተወሰደ መሆኑን የፈረንሳይ የፍትሃብር ሕግ አንቀጽ ይህን አስመልክቶ

"The distribution made by ancestor may be impeached for cause of wast more than a fourth"

በሚል ከደነገገዉ የምንረዳዉ ነዉ፡፡

የእኛ የፍትሃብሄር ሕግ ከአንቀጽ 1117-1123 ያሉ ድንጋጌዎችን ከፈረንሳይ የፍትሃብሄር ሕግ ሃሳቡን ሲወስድ Distributions የሚለውን partition በሚል ቀይሮታል፡፡ ነገር ግን በሁለቱም የፍትሃብሄር ህጎች “--made by---" ስለሚሉ ያለፈ መሆኑን ስለሚያሳዩ ክፍፍሉ በስጦታ ውል አስቀድሞ የተደረገ እንጂ ገና በሚከፋፈል የውርስ ንብረት ላይ እንዳልሆነ ያስገነዝባሉ፡፡ የእኛ የፍትሃብሄር ሕግ 1085 ጀምሮ ሟች በህይወት እያለ ወራሾች በስጦታ ያገኘዉ ንብረት በሕጉ በተቀመጡት በስተቀሮች ዉጪ ሊመልሱ እንደሚገባ መደንገጉ በዉርስ ሕጉ ክፍል ስለ ስጦታ ጭምር የተካተተ ሃሳብ መኖሩን የሚያሳይ ነዉ፡፡

ሌላዉ መጎዳት የሚለው ጽንሰ ሃሳብ መሠረታዊ ምንጩ የውርስ ሳይሆን የውል ሕግ ነው፡፡ ይህ ሃሳብ በውርስ ሕጉ ቁጥር 1117 የተካተተበት ዋነኛ ምክንየት ከቁጥር1117-1123 ያሉ ጽንሰ ሃሳቦች ሟች በህይወት እያለ በስጦታ ውል መሠረት የሚያደርገውን የስጦታ ክፍፍል የሚመለከት እና ስጦታ አድራጊውም በህይወት እያለ እስከ አስር አመት በውል የተደረገውን የስጦታ ክፍፍሉን መቃወም የተፈቀደዉ ኑዛዜ ባለመሆኑ ግላዊ ባህሪ የሌለው እና ተቀባዮች ሊቃወሙት የሚችሉት፤ እንዲሻሻል ሊጠይቁበት የሚችሉት ውል ስለሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ይህም የሕጉ አስተሳሰብ ነገሩን ትኩረት ሰጥተን እንዳንረዳው አድርጎናል፡፡

የፍ/ብ/ህ/ቁ 913 ላይ የተጠቀሰው የክፍፍል ደንብ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 የተመለከተው መከፋፈል ጋር አንድ አይነት እንዳልሆነ የማያወላዳ ተጨማሪ ምክንየት አቀርባለሁ ፡-

በፍ/ብ/ህ/ቁ 904 እና 905 የኑዛዜዎች መሻር እና ውድቅ መሆን በሚለው ክፍል ኑዛዜ ከተደረገ በኋላ ልጅ ከተወለደ ኑዛዜዎች ፈራሽ ይሆናሉ፡፡ ዳኞች በልዩ ሁኔታ ኑዛዜውን ካላፈረሱት ለተወለደዉ ልጅ ቢያንስ እጅግ ቢያንስ ሶስት እሩብ ማግኜት አለበት ይላል፡፡ በሌላ በኩል የፍ/ብ/ህ/ቁ 1121 እና 1123 ስጦታው ከተደረገ በኋላ የተወለደ እንደሆነ ሰጪው በሞተ ጊዜ የተተወው ልጅ የስጦታ አከፋፈሉ እንዲፈርስ መጠየቅ ይችላሉ፡፡ ከክፍፍሉ የተወለደው ወይም የተተወው ልጅም ከ1/4ኛ በላይ ሊያጣ እንደማይገባ ይደነግጋል፡፡ ሕጉ በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የተመላከተው ክፍፍል ደንብ በፍ/ብ/ህ/ቁ ከ1117 እስከ 1123 የተመለከተው ነው ብሎ ካሰበ የስጦታውን እጣ ፈንታ አስመልክቶ ልጅ በሚወለድበት ጊዜ ለምን ሁለት ጊዜ ይደነግጋል?
የፍ/ብ/ህ/ቁ 1105 እና 1106 በክፍፍል ስርዓቱ ንብረቱ በተሳሳተ መንገድ ተገምቶ ከሶስት እሩብ በታች የሆነ አነስተኛ ድርሻ የደረሰው ወራሽ ውርሱ በተከፋፈለ በ3 ዓመት ውስጥ ክፍፍሉ እንዲቃና ለመጠየቅ እንደሚችል ይደነግጋል ፡፡ በሌላ በኩል የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ጉዳቱ ሊደርሰው ከሚገባው ከሩብ በላይ ጉዳት ከሆነ የስጦታ ክፍፍሉ እንዲቀር ሟች በሞተ በሁለት አመት ውስጥ እና የስጦታ ክፍፍሉ በተደረገ አስር አመት ውስጥ ጉዳቱን ለማስተካከል መተየቅ እንደሚችል ደንግጓል፡፡ በፍ/ብ/ህ/ቁ 913 የተመላከተው የክፍያ ደንብ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ከተመላከተው ጋር ተመሳሳይ ነው ከተባለ ሕጉ ለምን በክፍፍል ጉዳት የደረሰበት ሰው እንዲያቃና ሁለት ቦታ ላይ መግለጽ ለምን ያስፈልገዋል? ለምንስ ለአንድ አይነት ጉዳይ የተለያየ የይርጋ ጊዜ ገደብ ያስቀምጣል?
እነዚህ ድንጋጌዎች የክፍያ ደንብ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 ከተመላከተው የስጦታ ክፍፍል የተለዩ እና በተለያየ ሕግ የሚገዙ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የፍ/ብ/ህ/ቁ 913`ን በዝርዝር ያየሁት ሰበር ችሎቱ ይህን ድንጋጌ በኑዛዜ ስጦታ ወይም በክፍያ ደንብ ክርክር ጊዜ ወደ ቁጥር 1123 ለመሸጋገር ስለሚጠቀምበት እና የችግሩ ዋና ምንጭ በመሆኑ ነው፡፡

6) በተዘዋዋሪ መንገድ ከውርስ መነቀል ምንድን ነው?መነቀል ከውርስ ሃብቱ ምንም አለማግኘት ነው ወይስ ድርሻ ማነስ ነው?

ሌላው መታየት ያለበት ጉዳይ ሰበር ችሎቱ በሰ/መ/ቁ.189118

"---ሌሎች ወራሾች ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ያልደረሳቸው ሳይሆን የደረሳቸው ድርሻ ግን አነስተኛ ከሆነ እነዚህ የሟች ወራሾች ከሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ አነስተኛ ደርሷቸዋል ከሚባል በስተቀር ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ድርሻ እንዳላገኙ ተነቅሏል የሚያስብል አይደለም፡፡"

በሚል ያሰፈረው አገላለጽ ነው፡፡

ከላይ እንደገለጽሁት በፍ/ብ/ህ/ቁ.1123 በስጦታ ክፍፍል ሊደርስ ከሚገባው ከሩብ በላይ ማጣት ወይም መጎዳት ከውርስ መነቀል ጽንሰ ሃሳብ ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም፡፡ የሰበር ችሎቱ አንድ ጊዜ መነቀል ማለት ምንም ድርሻ አለማግኘት እንጂ ድርሻ ማነስ አይደለም፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ምንም አለማግኘት ብቻ ሳይሆን ድርሻ ማነስም በተዘዋዋሪ መንገድ መንቀል ነው በሚል እርስ በእርሱ የሚቃረኑ የሰበር ውሳኔዎች ስላሉ እነሱን ማየት ተገቢ ነው፡፡

ቀጥሎ በማነሳቸዉ የሰበር የሕግ ትርጉሞች ላይ በአንዳንዶቹ ላይ ኑዛዜው መነቀል አስከትሏል የሚባለው ከቀሪው የውርስ ሃብት ጋር ተነጻጽሮ አነስተኛ ድርሻ ሲደርሰው ነው፤ በኑዛዜ ሊደርሰው ከሚገባው 1/4ኛ ማጣት እና መነቀል እኩል ነዉ፤ መጎዳት ወይም ከ1/4ኛ በላይ ማጣት ከመነቀል የተለየ ነዉ፤ በኑዛዜ እጅግ አነስተኛ ገንዘብ ማግኘት የድርሻ ማነስ ሳይሆን መነቀል ነው፤ ከውርስ መነቀል ማለት ከውርስ ሃብት ምንም አይነት ድርሻ አለማግኘት እንጂ አነስተኛ ድርሻ ማግኘት ስላልሆነ ከሌሎች ወራሾች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ድርሻ ተሰጥቶኛል የሚል ወገን ከውርስ ተነቅያለሁ ሊል አይችልም የሚሉ ናቸዉ፡፡ እነዚህን የሰበር የሕግ ትርጉሞች በዝርዝር እንመልከታቸዉ፡፡

ሰ/መ/ቁ 57836፡- በኑዛዜ የሚከናወኑ ተግባሮች የኑዛዜ ስጦታ (legacy) ወይም የክፍያ ደንብ (rule of partiton) ሊሆኑ ይችላሉ። በመርህ ደረጃ አንድ ሰው ከውርስ ሀብቱ መካከል አንድን ንብረት ለወራሾቹ መስጠቱ የኑዛዜ ስጦታ አያሰኘውም። ይህን አይነት ስጦታ ሕጉ የሚቀበለው እንደ አንድ የክፍያ ደንብ ነው። በመሆኑም አንድ አውራሽ ለወራሹ አንድ ንብረት ቢናዘዝለት የኑዛዜው አፈጻጸም የስጦታ (legacy) አፈጻጸም በመከተል ሳይሆን የክፍያ ደንብ (partition) በመከተል የሚከናወን ነው። ሆኖም በኑዛዜው ላይ የሚሰጠውን ክፍያ መጠን በመገለጹ ብቻ ሁልጊዜ የክፍያ ደንብ ነው ሊባል የሚቻል አይሆንም። የተሰጠው የንብረት መጠን ከሟቹ የውርሰ ሀብት ግምት ጋር ታይቶ ውጤቱም በዚህ እረገድ መለየት አለበት። በሌላ አነጋገር ሟቹ በኑዛዜው ላይ የሚያሰፍረው የንብረት መጠን ከሟቹ የውርሰ ንብረት መጠን ጋር እየታየ የመነቀል ጉዳይ ነው ወይስ የክፍያ ማነስ? የሚለው ነጥብ የሚለይ ይሆናል። የባልና ሚስት የጋራ በሆነ ንብረት ላይ አንደኛው ወገን በኑዛዜው ንብረቱን በሰጠ ጊዜ በኑዛዜው ፍርስ መሆን አለመሆን ላይ ተናዛዡ በንብረቱ ላይ መብት ያለው መሆን አለመሆኑን ማወቅ ብቻ ሳይሆን ንብርቱ የጋራ መሆን አለመሆኑ ላይ የነበረው ግንዛቤ ውጤት ይኖርዋል። ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1047 (1) እና (2) መገንዘብ የሚቻለው ኑዛዜ ፍርስ ሊሆን የሚችለው ተናዛዡ ስጦታ ባደረገበት ንብረት ላይ መብት እንደሌለውና ይህንም ያውቅ እንዳልነበር ሲታወቅ ብቻ ነው። በኑዛዜ የተሰጠን ስጦታ የክፍያ ደንብን በመከተል ለመፈጸምና እና የክፍያ ማነስ ነው በማለት በክፍያ ደንብ ድንጋጌዎች ለማስተካከል በፍ/ብ/ህ/ቁ 1117 እና 1123 ጥምር ንባብ መሠረት ኑዛዜ የተደረገለት ሰው የሟቹ ተወላጅ ወይም ወደ ላይ የሚቆጠር ዘመድ መሆን አለበት። “ ልጅ ትዳር ከመሠረተች በኋላ አልተንከባከበችኝም ስታመም አልጠየቀችኝም” የሚል ምክንያት ከውርስ ለመንቀል የሚያስችል በቂና ህጋዊ ምክንያት አይደለም። ቅጽ/11

ሰ/መ/ቁ.235837፡- አንድ ኑዛዜ ወደታች የሚቆጠር ተወላጅን ከውርስ የነቀለ ነው ሊባል የሚችለው በዝምታ ወይም በሕግ ተቀባይነት የሌለውን ምክንያት በመጥቀስ ምንም ድርሻ ሳይሰጥ ወይም በውጤት ምንም ድርሻ እንዳልተሰጠ የሚያስቆጥር የድርሻ መጠን በኑዛዜው ሲጠቀስ መሆኑን ከፍ/ሕ/ቁጥር 938 ድንጋጌ ይዘት መገንዘብ ይቻላል። እንደዚሁም አባት ወይም እናት ወይም ሌሎች ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ለልጆቻቸው ወይም ወደታች ለሚቆጠሩ ተወላጆች ሀብታቸውን ለመስጠት ወይም ለማከፋፈል እንደሚችሉ እና በስጦታው አከፋፈል ውስጥ ተቃራኒ ቃል ከሌለ በስተቀር ወደታች ከሚወለዱ ወራሾች አንዱ ሊደርሰው ከሚገባው ድርሻ ከ1/4ኛ በላይ ጉዳት ደርሶበት ከሆነ የስጦታ አከፋፈሉ እንዲቀር መጠየቅ እንደሚችል በፍ/ሕ/ቁጥር 1117 እና 1123/1 ተመልክቷል። ኑዛዜው ተወላጅን ያለምክንያት ከውርስ ሐብት የነቀለ ነው ወይም ከ1/4ኛ በላይ ጉዳት ያደረሰ ነው የሚባል ከሆነ ውጤቱ የኑዛዜ ክፍፍሉ ቀሪ ሆኖ ኑዛዜ ሳይኖር ሊያገኝ የሚችለውን ድርሻ እንዲያገኝ ማድረግ መሆኑንም ከእነዚሁ ከተጠቀሱት ድንጋጌዎች ይዘት መረዳት ይቻላል። በኑዛዜ ከውርስ ሐብት መነቀል ወይም ከ1/4ኛ በላይ ጉዳት መድረሱ ሊታወቅ የሚችለው በኑዛዜው የድርሻ መጠን ተጠቅሶ ውጤቱ ግን መንቀል መሆኑን ወይም ከ1/4ኛ በላይ ጉዳት መድረሱ ሊረጋገጥ የሚችለው ኑዛዜውን በማየት ብቻ ሳይሆን የውርስ ሐብቱ ተጣርቶ ሲቀርብ ከአጠቃላይ የውርስ ሐብቱ አንጻር ተነቅያለው ወይም ጉዳት ደርሶብኛል ለሚለው ተወላጅ በኑዛዜ የተሰጠውን የድርሻ መጠን በማገናዘብ ነው።የውርስ ሐብቱ ተጣርቶ ተጎዳሁ ወይም ተነቀልሁ ለሚለው የደረሰው ለሌሎች ከተሰጠው ጋር ተነጻጽሮ ሳይታይ በኑዛዜው ላይ ሟች ድርሻ መስጠታቸውን ብቻ በመመልከት ከኑዛዜ አልተነቀሉም ወይም በኑዛዜው ከ1/4ኛ በላይ ጉዳት አልደረሰባቸውም ሊባል አይችልም። ግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ/ም

ሰ/መ/ቁ 55648፡- ሟች በኑዛዜው ተወላጁን ስለአረዳኝ እና ስላልጠየቀኝ በሚል ምክንያት ከውርስ ሀብቱ ሊደርሰው ከሚችለው 1/4ኛ ድርሻ በላይ ሊያሳጡት አይገባም። የፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 (1) እና 938(2)”ን በጣምራ በመተርጎም መረዳት የሚቻለው ሟች የተወሰኑት ተወላጆቻቸውን ስላረዷቸውና ስላልጠየቋቸው በውርስ ከሚደርሳቸው ድርሻ ሩብ በላይ እንዲያጡ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ምክንያት አይደለም። በመሆኑም ተናዛዡ በቂ ባልሆነ ምክንያት ተወላጁን ሊደርሰው ከሚገባው ከ1/4ኛ በላይ የውርስ ድርሻ የከለከለው ከሆነ እና ለሌላኛው ተወላጅ ከሩብ በላይ የሆነውን ንብረቱን እንዲተላለፍለት ኑዛዜ አድርጎ ከተገኘ ኑዛዜው ተጎዳሁ የሚለውን ተወላጅ እስከ 1/4ኛ ድረስ ብቻ የውርስ ንብረት የሚያሳጣቸው በመሆኑ በዚሁ መንገድ ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ተደርጎ ሊተገበር ይገባዋል። ቅጽ/11

ሰ/መ/ቁ 58338፡- አንድ አውራሽ ለወራሹ አንድን ንብረት ቢናዘዝለት የኑዛዜው አፈፃጸም የስጦታ አፈፃጸምን በመከተል ሳይሆን የክፍያ ደንብ በመከተል የሚከናውን ይሆናል። ነገር ግን በኑዛዜው ላይ የሚሰጠው የክፍያ መጠን በመገለጹ ብቻ ሁል ጊዜ የክፍያ ደንብ ነው ሊባል የሚቻል አይደለም። በኑዛዜ የተሰጠው የንብረት መጠን ከሟቹ የውርስ ንብረት ጋር መታየት ያለበት ነው። በሌላ አገላለጽ ሟች በኑዛዜው ላይ የሚያሰፍረው የንብረት መጠን ከሟቹ የውርስ ንብረት መጠን ጋር እየታየ የመነቀል ጉዳይ ነው ወይስ የክፍያ ማነስ የሚለው ነጥብ የሚለይ ይሆናል። ጠቅላላ ንብረቱ ስድሰት መቶ ሺህ ብር የሚቆጠር ሟች ሁለት ልጆቸ በህይወቴ ከፍተኛ ችግር ስለፈጠረብኝ እያንዳንዳቸው አምስት ብር እንዲወስዱ የወንድሜ ልጅ ቀሪውን ንብረቴን በሙሉ እንዲወስድ በሚል ቢናዘዝ ጉዳዩ የክፍያ ማነስ ሳይሆን የመነቀል ውጤት ያለው ነው። ለወንድሙ ልጅ ያደረገለት ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ በመሆኑ እንዲሁም ዝርዝሩን ሳይገልፅ በህይወቴ ከፍተኛ ችግሮች ስለፈጠሩብኝ የሚለው የተለያየ ደረጃ እና እርከን ያለው በመሆኑ ለመንቀል በቂና ህጋዊ ምክንያት ስላልሆነ በፍ/ብ/ህ/ቁ/ 938 እና 915 መሠረት ሁሉም ልጅና የወንድም ልጅ የውርሱን ንብረት እኩል ሊካፈሉ ይገባል እንጂ ውጤቱ የክፍያ ማነስ ስለሆነ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1123 መሠረት በክፍያ ደንብ የሚታይ ነው ሊባል አይገባም። ቅጽ/11

ሰ/መ/ቁ 47622፡- የፍ/ብ/ህ/ቁ 913 በኑዛዜ ስጦታ (legacy) እንዲሁም የክፍያ ደንብ (rule of partition) ማድረግ እንደሚቻል የሚናገር ነው። በመርህ ደረጃ አንድ ሰው ከውርስ ሃብቱ መካከል አንድን ንብረት ከወራሾቹ መካከል ለአንዱ በኑዛዜ መስጠት የክፍያ ደንብ እንጂ የኑዛዜ ስጦታ አያስብልም። በመሆኑም አንድ አውራሽ ለወራሹ አንድን ሃብት ሲናዘዝ የኑዛዜው አፈጻጸም የስጦታ (legacy) አፈጻጸምን በመከተል ሳይሆን የክፍያ ደንብን (rule of partition) በመከተል የሚከናወን ነው። አንድ አውራሽ በኑዛዜ ወራሽ ለሆነው ልጅ አምስት ሺ ብር ተናዘዘለት እና ለሌሎች ወራሾች ደግሞ ሌላ ንብረት ከተናዘዘላቸው የክፍያ ደንብ እንጂ የኑዛዜ ስጦታ ባለመሆኑ በክፍያው አንድ ተወላጅ ከሚደርሰው ከሩብ የበለጠ ጉዳት ከደረሰበት የኑዛዜ ክፍፍሉ እንዲቀር ጥያቄ ማቅረብ ይችላል። የጉዳቱን መጠን ለማወቅ ውርሱ መጣራት አለበት። እንዲሁም ከውርስ መነቀል ማለት ከውርስ ሃብት ምንም አይነት ድርሻ አለማግኘት እንጂ አነስተኛ ድርሻ ማግኘት ስላልሆነ ከሌሎች ወራሾች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ድርሻ ተሰጥቶኛል የሚል ወገን ከውርስ ተነቅያለሁ ሊል አይችልም። ቅጽ/10
የሰ/መ/ቁ.189118፡-------- ሌሎች ወራሾች ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ያልደረሳቸው ሳይሆን የደረሳቸው ድርሻ ግን አነስተኛ ከሆነ እነዚህ የሟች ወራሾች ከሚደርሳቸው የውርስ ሀብት ድርሻ አነስተኛ ደርሶአቸዋል ከሚበል በስተቀር ከሟች የውርስ ሀብት ምንም ድርሻ እንዳላገኙ ተነቅሏል የሚያስብል አይደለም፡፡ የካቲት 24 ቀን 2013 ዓ.ም

ሰ/መ/ቁ.135686፡- ኑዛዜው የሕጉን ፎርማሊቲ ያሟላ ነው ከተባለና በኑዛዜው አንድ ወራሽ አለአግባብ ተነቀለ የሚባል ቢሆን በውርሱ አከፋፈል ላይ የሚታይ እንጂ በአግባቡ የተሰጠን ኑዛዜ ፈራሽነት የሚያስከትል የሕግ ምክንያት አይኖርም። ከፍትሃብሔር ሕጉ አንቀጽ 913 ድንጋጌ የኑዛዜው ቃል የተናዛዥን ተቃራኒ ሐሣብ የሚገልጽ ካልሆነ በቀር ከውርስ ሃብት አንድ ድርሻን ወይም አንድ ንብረትን ሟቹ ለወራሾች መስጠቱ ተራ የሆነ የክፍያ ደንብ እንጂ እንደ ኑዛዜ ስጦታ ነው ተብሎ አይቆጠርም በማለት ያስቀምጣል።

ከዚህ ድንጋጌ ለመገንዘብ የሚቻለው በኑዛዜው የሚከናወኑ ተግባሮች የኑዛዜ ስጦታ (legacy) ወይም የክፍያ ደንብ (Rule of Partition) ሊሆኑ እንደሚችሉ ነው። በመርህ ደረጃ አንድ ሰው ከውርስ ሀብቱ መካከል አንድን ንብረት ለወራሾቹ መስጠቱ የኑዛዜ ስጦታ አያሰኘውም። ይልቁንም ይህ አይነት ኑዛዜ ሕጉ የሚቀበለው እንደ አንድ የክፍያ ደንብ ነው። በመሆኑም አንድ አውራሽ ለወራሹ አንድን ንብረት ቢናዘዝለት የኑዛዜው አፈፃፀም የስጦታ (legacy) አፈፃፀምን በመከተል ሳይሆን የክፍያ ደንብ (Partition) በመከተል የሚከናወን ይሆናል።

ኑዛዜው ስጦታን (legacy) የሚመለከት ከሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 942 ጀምሮ ባሉ አንቀፆች መሠረት በማጣራት (liquidation) ሥርዓት የሚከናወን ሲሆን ክፍያ ግን ክፍፍልን (partition) በሚመለከቱና ከአንቀጽ 1060 ጀምሮ ባሉ ድንጋጌዎች መሠረት የሚስተናገድ ነው። የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1123 ደግሞ በዚሁ የሕጉ ክፍል ማለትም የውርስ ክፍፍልን በሚመለከተው ስር ያለ ነው። በመሆኑም የቁም ስጦታ የሚለውን ቃል ብቻ በመያዝ የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1123 ድንጋጌ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም ሊባል አይገባም። ኑዛዜው የስጦታ ነው የሚባል ቢሆን ኖሮ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥሮች 1037-1051 መሠረት እንዲሁም 1047/3/ መሠረት የተጠቀሰው ንብረት ወይም ግምቱ ለስጦታ ተጠቃሚው በቅድሚያ ይሰጣል።

የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1123/1/ ድንጋጌ በስጦታ አከፋፈል ውስጥ ተቃራኒ ቃል ከሌለ በቀር ወደታች ከሚቆጠሩ ተወላጆች አንዱ ከሚደርሰው ከሩብ የበለጠ ጉዳት ደርሶበት እንደሆነ የስጦታ አከፋፈሉ እንዲቀር ለመጠየቅ ይችላል በማለት በግልፅ ያስቀምጣል። የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1123 በስጦታ አከፋፈሉ ተቃራኒ ቃል ከሌለ በቀር የሚለው ይዘት ሟች ተወላጆቹን ከሩብ የበለጠ ጉዳት እንዲደርስባቸው ለማድረግ የሚችለው ሕጋዊና በቂ ምክንያት ሲኖረው ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 938 ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ ጋር በማገናዘብ ተረድተናል። በመሆ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share