ለሚ ኩራ ፍትህ ጽ/ቤት-Lemi Kura Justice Office

ለሚ ኩራ ፍትህ ጽ/ቤት-Lemi Kura Justice Office Providing legal information and guidance, Protecting public and governmental interests through litigation

11/02/2026

የፕላስቲክ ከረጢቶች /ፌስታል ምርቶችን/ መጠቀም የሚያስከትለው ተጠያቂነት

መግቢያ
በኢትዮጵያ የሕዝብ ቁጥርና የከተሞች እድገትን ተከትሎ ባልተገባ መልኩ የሚጣሉ ደረቅ ቆሻሻዎች ማለትም እንደ ፕላስቲክ/ፌስታል/ ያሉት የአካባቢን ስነ ምህዳር በመበከል፣ የውሃ መስመሮችን በመዝጋት፣ ለረጅም ጊዜ ሳይበሰብሱ በመከማቸት ለተላላፊ በሽታዎች መስፋፋት መንስኤ ሲሆኑ ይታያሉ። በተለይ የፕላስቲክ ምርቶች ሳይበሰብሱ ለብዙ ዓመታት በመቆየት የስነ ምህዳር ጠንቅ እንደሆኑ ሳይንሳዊ ምርምሮች ያወሳሉ። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከሕገ መንግስቱ ጀምሮ የአካባቢ እንክብካቤን የተመለከቱ ሕጎች ያሏት ሲሆን የሁሉም ሕግ የበላይ ከሆነው ሕገ መንግስታችን ብንነሳ በአንቀጽ 44/1/ ስር ሁሉም ሰዎች ንጹህና ጤናማ በሆነ አካባቢ የመኖር መብት እንዳላቸው ይደነግጋል። በዚሁ ሕገ መንግስት አንቀጽ 92 ስር መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ንጹህና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲኖረው ጥረት የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት ተደንግጓል። በዚህ መነሻነት የወንጀል ሕጉ እና ሌሎች አዋጆች ለምሳሌ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ አዋጅ ቁጥር 513/1999 ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ሲሆን ከጉዳቱ መጠን እና በኢትዮጵያ ካለው የስርጭት አድማስ አንጻር በተለይ የፕላስቲክ ምርትን አስመልክቶ የሕግ ማእቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኗል። ስለሆነም የፕላስቲክ ምርቶችን መጠቀም የሚከለክል አለፍ ሲልም የወንጀል ቅጣትን የሚደነግግ አዋጅ ቁጥር 1386/2017 ወጥቶ በስራ ላይ ውሏል። በዚህ አጭር ጽሁፍም እነዚህን ክልከላዎች እና የሚያስከትሉትን ተጠያቂነት እንዳስሳለን።

የፕላስቲክ ምርት/ፌስታል/ ምንነት
በአዋጅ ቁጥር 1383/2017 አንቀጽ 2/9/ ስር እንደተደነገገው ፕላስቲክ ማለት በዋናነት ከፔትሮኬሚካል የተሰራ፣ ለስላሳና የማይበሰብስ የፖሊመር ይዘት ያለው ምርት እንደሆነ ትርጉም ተሰጥቶታል። ይህም በተለምዶ ፌስታል ተብሎ የሚጠራውን ምርት የሚያመለክት ነው። በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 2/10/ ስር እንደሰፈረው የፕላስቲክ ከረጢት ማለት አነስተኛ ጥግግት ያለው፣ በቀላሉ በስብሶ ከአፈር ጋር የማይዋሃድ እና ሌሎች ምርቶችን ለመያዝ የሚያገለግል ፕላስቲክ እንደሆነ ተመላክቷል። ይኸውም የፌስታል ከረጢትን የሚያመለክት ነው።

ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ፌስታል ጉዳይ ሲሆን በአዋጁ አንቀጽ 2/11/ ስር አንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ይኸውም መልሶ ጥቅም ላይ የማይውል ወይም መልሶ ኡደት የማይደረግ እና አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ ውሎ ቀጥታ የሚወገድ የፕላስቲክ ምርት እንደሆነ በዚሁ ድንጋጌ ተገልጿል።

በፕላስቲክ ምርት/ፌስታል/ ላይ የተደረገው ክልከላ
ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ
• መጠቀም ወይም ለመጠቀም ይዞ መገኘት፣
• ማምረት፣ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት፣ ለገበያ ማቅረብ፣ መሸጥ፣ ለንግድ ዓላማ ማከማቸት ወይም ይዞ መገኘት ክልክል መሆኑን እና አስተዳደራዊ ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል በአዋጁ አንቀጽ 24/9/ ስር ተደንግጓል። ሆኖም ግን የፌዴራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ፕላስቲኮች እንዲመረቱ ወይም ጥቅም ላይ እንዲውሉ በልዩ ሁኔታ በመመሪያ ሊፈቅድ እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 14 ስር ተደንግጓል።

የወንጀል ተጠያቂነት
በአዋጁ አንቀጽ 25 ስር ክልከላዎችን መተላለፍ የወንጀል ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል ተደንግጓል። ይኸውም፡-
• ማንኛውም ሰው የፕላስቲክ ከረጢት/የፌስታል ከረጢት/ ከተጠቀመ ወይም ለመጠቀም ይዞ ከተገኘ ከ2,000/ሁለት ሺህ ብር/ በማያንስና ከ5,000/አምስት ሺህ ብር/ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።
• ማንኛውም ሰው የፕላስቲክ ከረጢት/የፌስታል ከረጢት/ ካመረተ ወይም ወደ አገር ውስጥ ካስገባ፣ ለገበያ ካቀረበ ወይም ከሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ካከማቸ ወይም ይዞ ከተገኘ ከ50,000/ሀምሳ ሺህ ብር/ በማያንስና ከ200,000/ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከ5/አምስት አመት/ በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል፡፡ ይኸውም የፕላስቲክ ከረጢት/ፌስታል/ ከግለሰባዊ አገልግሎት ውጪ ለንግድ ዓላማ ጥቅም ላይ ሲውል ከገንዘብ ቅጣት በተደራቢነት በእስራት እንደሚያስቀጣ መረዳት ይቻላል።
• ከላይ የተመለከቱትን የወንጀል ድርጊቶች የፈጸመው ሕጋዊ ሰውነት ያለው ድርጅት ከሆነ የገንዘብ ቅጣቱ ከላይ የተገለጸውን 3/ሶስት እጥፍ/ ይሆናል።

ማጠቃለያ
የፕላስቲክ ምርቶች/ፌስታሎች/ የአካባቢ ስነ ምህዳር ብሎም የሰዎች እና የእንስሳት ጤና ጠንቅ ናቸው። ይህንን ጉልህ የሆነ የጤና ጠንቅ ለመከላከል በምርቶቹ ላይ ክልከላ እና ተጠያቂነትን የሚደነግግ ሕግ ማውጣት አንዱ ዘዴ ነው። ኢትዮጵያም ፌስታል መጠቀምን የሚከለከል ህግ አውጥታ ተግባራዊ አድርጋለች። ስለሆነም ህብረተሰቡ እነዚህን ለጤና ጠንቅ የሆኑ ምርቶችን ባለመጠቀም አጠቃላይ የስነ ምህዳር ጤንነትን በማስጠበቅ ሂደት የበኩሉን ሊወጣ ይገባል።

በንቃተ ሕግ፣ ትምህርትና ስልጠና የተዘጋጀ

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን ይቀላቀሉ
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_external

11/02/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በተዋረድ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት ሥልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016
መሰረት ከተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት መካከል፡--
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር የመንግስት መሥሪያ ቤቶች የሚያደርጉት አስተዳደራዊ ውል እንደ አስፈላጊነቱ በመመርመር ሕጋዊነታቸውን ማረጋገጥ፤ አፈፃፀማቸውን በመከታተል፤ ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወሰድ ማድረግ ወይም መውሰድ፤የክ/ከተማ አስተዳደሩ አስፈፃሚ አካላት የሚወስኗቸው ውሳኔዎች ከህግ ጋር የተጣጣመ መሆኑን በማረጋጥ፤ የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ ወይም እንዲወስዱ ማድረግ፤
የራሳቸውን የሕግ አገልግሎት እንዲኖራቸው የተፈቀደላቸው አስፈፃሚ አካላት የህግ አገልግሎቶች ዕቅድ እና ወቅታዊ ሪፖርት እንዲቀርብለት በማድረግ ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ፤ የማስተካከያ እርምጃ የመውሰድ፤ እና የከተማው አስተዳደር ያወጣቸው ሕጎች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋላቸውን መከታል፤ መቆጣጠር የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
04/062018ዓ.ም

07/02/2026
27/01/2026
16/01/2026
13/01/2026

በመዲናዋ በፍርድ ቤቶች በተደረጉ ክርክሮች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ የሕዝብና መንግሥት ጥቅም ማስከበር ተቻለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ በፍርድ ቤቶች በተደረጉ ክርክሮች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ የሕዝብና መንግሥት ጥቅም ማስከበር ቻለ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ በፍትሐብሔር ጉዳዮች ክርክር የፍርድ ቤት ውሳኔ ካገኙ 1 ሺህ 491 መዝገቦች ውስጥ 1 ሺህ 382 መዝገቦች ለአስተዳደሩ ተወስኗል።

በዚህም 3 ቢሊየን 212 ሚሊየን 856 ሺህ 60 ብር እንዲሁም 101 ቤቶች፣ 19 መስሪያ ቦታ ሼዶች እና 178 ነጥብ 62 ሄክታር መሬት የሕዝብ መብትና ጥቅም ማስከበር መቻሉን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት የፍትሐብሔር ጉዳዮችን ክርክር በፍርድ ቤቶች የመርታት አቅም ወደ 94 ነጥብ 7 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ 92 ነጥብ 7 በመቶ በማሳካት አፈፃፀሙም 98 በመቶ መድረሱን አመላክተዋል፡፡

5 ሺህ 416 የግል አቤቱታ እና 981 የደንብ መተላለፍ በጥቅል 6 ሺህ 397 የወንጀል መዛግብት በመመርመር የማጥራት ሥራ መሰራቱን ገልጸው÷ ምርመራቸው ከተጠናቀቀባቸው የግል አቤቱታ ወንጀል መዝገቦች ውስጥ 4 ሺህ 639 መዛግብት በእርቅ እልባት አግኝቷል ብለዋል።

በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ውሳኔ ካገኘባቸው 1 ሺህ 314 የወንጀል መዛግብት በ1 ሺህ 307 መዝገቦች ላይ ማስቀጣት መቻሉንና 7 መዛግብት በነፃ መዘጋታቸውን ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም 6 የነባር ሕጎች ማሻሻያ እና 30 አዳዲስ ሕጎች የማርቀቅ ተግባር ባለፉት ስድስት ወራት መከናወኑንም አቶ ተክሌ አስረድተዋል።

በአድማሱ አራጋው

👉ለፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች የፋና ዲጂታል አድራሻዎችን ከአስተያየት መስጫ ሳጥኑ ያግኙ:-

የሐዘን መግለጫ።።።።።።።።።።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ  በለሚ ኩራ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ዐቃቤ ህግ በነበሩት ዓቃቤ ሕግ እመቤት ወ/ስላሴ ሕልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘ...
30/12/2025

የሐዘን መግለጫ
።።።።።።።።።።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በለሚ ኩራ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ዐቃቤ ህግ በነበሩት ዓቃቤ ሕግ እመቤት ወ/ስላሴ ሕልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል።

ዓቃቤ ሕግ እመቤት ወ/ስላሴ ነሐሴ 5 ቀን 1971 ተወልደው በተወለዱ 47 አመታቸው ታኅሣሥ 21/2018 ዓ.ም ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት አመራር እና ሠራተኞች የአቃቤ እመቤት ወ/ስላሴ ነፍስ በአፀደ ገነት ያሳርፍልን እያልን ለቤተሰቦቿ እና ወዳጅ ዘመዶች በሙሉ መፅናቱን እንዲሰጥልን እንመኛለን።

ታኅሣሥ 21/2018 ዓ.ም

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ለሚ ኩራ ፍትህ ጽ/ቤት-Lemi Kura Justice Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category