የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office

የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office, Legal, Benishangul Gumuz, Addis Ababa.

በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን ክቡር አቶ ብጅጋ ፃፊዮ ገለፁ። በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ በዞኑ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን የካማሺ ዞን ዋና አ...
25/06/2026

በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን ክቡር አቶ ብጅጋ ፃፊዮ ገለፁ።

በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ በዞኑ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ብጅጋ ፃፊዮ ገልፀዋል።

የካማሺ ዞን ሰላም ግንባታና ፀጥታ መምሪያ ፣ሚሊሺያ ጽ/ቤትና ፖሊስ መምሪያ በ2018 ዓ.ም በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ የተሰሩ የስራ አፈፃፀም ሪፖርርቶችን የዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ፃፊዮ በተገኙበት ተገምግሟል።

የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ፃፊዮ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች የተረጋጋ ሰላምን በመፍጠር የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲከናወኑ የፀጥታ ዘርፉ የማይተካ ሚና ማበርከት በቻሉን ገልፀዋል።

በዞኑ የተረጋጋ ፖለቲካን በመፍጠርና አስተማማኝ ሰላምን በመገንባት፣ የህዝቡን ደህንነት በማስጠበቅ ፣የህግ የበላይነት በማስከበር ረገድ በፀጥታ አባላቱ፣በመንግስ መዋቅሮችና በህዝቡ የተቀናጀ ጥረት አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉ አቶ ብጅጋ ተናግረዋል።

7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተዓማኒ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ በዞኑ አስተማማኝ ሰላም መኖሩን አንዱ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ብጅጋ የተገኘውን ሰላም መጠበቅና መንከባከብ ባህል ማድረግ አለብን ብለዋል።

በፀጥታ ዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ህዝቡ የሰላም ባለበት በማድረግና ማህበረሰቡን ያሳተፈ የፀጥታ ስርዓትን መገንባት ይገባል ብለዋል።

በዞኑ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ወንጀሎችን ቀድሞ በመከላከል የመረጃ አሰባሰብና ትንተናን አቅምን ማሳደግ ይጠበቃልም ብለዋል ።

የተቋማትንና የወጣቶችን ቅንጅታዊ አሰራር በጥብቅ ዲሲፕሊን በመምራት ለአንድ ዓላማና ውጤት እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በፀጥታ ዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠልና ክፍተቶችን ደግሞ በአንድነት፣ በቁርጠኝነት እና በከፍተኛ የሀላፊነት ስሜት በማረም ዞኑን ለልማት እና ለኢንቨስትመንት ምቹ በማድረግ የብልጽግ ጉዟችንን እውን ማድረግ አለብን በማለት ዋና አስተዳዳሪው የሥራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የካማሺ ዞን ሰላም ግንባታና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ ቤከማ ጉዲና በበኩላቸው በዞኑ የውስጥ ሰላምን ከማፅናት ባለፈ ከአጎራባች የክልል ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጋር በርካታ የሰላም ጥምር ኮሚቴ ስራዎች በመስራት የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነቶችን ማጠናከር ተችሏል ብለዋል።

ህዝቡ በዞኑ የተገኘውን አስተማማኝ ሰላም በመጠቀም ያለምንም የፀጥታ ስጋት የልማት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት አቶ ቤከማ የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃልም ብለዋል።

አቶ ቤከማ አክለውም በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ የታዮ ስኬቶችን አጠናክሮ ከማስቀጠል ባለፈ የነበሩ ክፍተቶችን በማረም በ2019 በጀት ዓመት ውስጥ በማካተት በትኩረት እንደሚሰሩ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም በ7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በሪፖርት ግምገማ መድረኩ ላይ የዞንና የካማሺ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የካማሺ ማረሚያ ቤቶች፣የዳቡስ ሻለቃ አድማ ብተና የፀጥታ አመራሮችና አባላት ፣የሁሉም ወረዳ አስተባባሪ አመራሮች፣የሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማጎሌዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን የካማሺ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ነው፦ አቶ አሻድሊ ሀሰን‎************‎‎(አሶሳ፣ ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) የክረ...
24/06/2026

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ነው፦ አቶ አሻድሊ ሀሰን
‎************

‎(አሶሳ፣ ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ክልላዊ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ዛሬ በአሶሳ ከተማ በይፋ አስጀምረዋል።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን የዘንድሮውን ክልላዊ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በአሶሳ ከተማ ወረዳ ሁለት ተገኝተው በአቅመ ደካማ ዜጎች የቤት ግንባታ እና በችግኝ ተከላ አስጀምረዋል።

‎አቶ አሻድሊ ሀሰን በዚሁ ወቅት፣ የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በለውጡ መንግስት የተለያዩ ኢኒሼቲቮች እየተተገበሩ ነው ብለዋል።

‎የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ አሻድሊ ተናግረዋል።

‎ባለፉት ዓመታት በክልሉ ከ2 ሺህ 300 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ እና እድሳት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።

‎በተያዘው ክረምት ከ100 በላይ የአቅመ ደከማ ቤቶች ግንባታ እና ዕድሳት ሥራ ይከናወናል ያሉት አቶ አሻድሊ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ የማዕድ ማጋራትን ጨምሮ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።

‎ባለድርሻ አካላት በመርሃ-ግብሩ ላይ በንቃት እንዲሳተፉም አቶ አሻድሊ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በኩላቸው፣ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መረዳዳት እና መተሳሰብን የሚያጠናክሩ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፣ ይህንን በተባበረ ክንድ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

‎በመርሃ-ግብሩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

‎በኩርሙክ ወረዳ ከ19ኙ ቀበሌ ከተወጣጡ የሚሊሺያ አካላት ጋር በወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።‎‎(ኩርሙክ:-ሰኔ 15/2018 ዓ ም) በኩርሙክ ወረዳ ከ19ኙ ቀበሌ ከተወጣጡ...
22/06/2026

‎በኩርሙክ ወረዳ ከ19ኙ ቀበሌ ከተወጣጡ የሚሊሺያ አካላት ጋር በወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

‎(ኩርሙክ:-ሰኔ 15/2018 ዓ ም) በኩርሙክ ወረዳ ከ19ኙ ቀበሌ ከተወጣጡ የሚሊሺያ አካላት ጋር በወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

‎የኩርሙክ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ እማም አብዱራህማን የሚሊሺያ አባላት የወረዳውን ሰላም ለማሰጠበቅ እያከናወኑ ያለው ስራ አበረታች መሆኑን ጠቁመዋል።

‎እንዲሁም ወረዳው ጠረፋማና ድንበር አከባቢ ከመሆኑ አንጻር የሚሊሺያ አካላት ከፀጥታ ሀይል ጋር በመቀናጀት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

‎የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኘነት እና የፖሎቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አነስ መሀመድ በበኩላቸው የወረዳውን ዘላቂ ሰላም ለማስቀጠል የሚሊሺያ አባላት ክትትልና ቁጥጥር ወሳኝ ነው ብለዋል።

‎አቶ አነስ የሚሊሺያ አባላት በወርቅ አከባቢ የሚፈጠሩ አንድ አንድ የእርስ በርስ ግጭቶችን መቆጣጠር እና ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህግ የማቅረብ ስራ መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

መረጃው የኩርሙክ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።


የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኃይል ከዘራፊዎች ያስመለሳቸውን 33 እንስሳት ለባለቤቶቻቸው አስረከበ​(ግልገል በለስ፤ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም) የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር...
22/06/2026

የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኃይል ከዘራፊዎች ያስመለሳቸውን 33 እንስሳት ለባለቤቶቻቸው አስረከበ

​(ግልገል በለስ፤ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም) የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስና የሚሊሻ አባላት፣ በትናንትናው ዕለት ዘራፊዎች ከግልገል በለስ 102 ቀበሌ የዘረፏቸውን 33 እንስሳት እግር በእግር በመከታተልና በቁጥጥር ሥር በማዋል ለባለቤቶቻቸው ማስረከባቸው ተገለጸ።

​ዘራፊዎቹ እንስሳቱን ወደ ማንድራ ወረዳ ውዲት ቀበሌ በመውሰድ ላይ እያሉ፣ የጸጥታ ኃይሉ ባደረገው ተከታታይ ክትትል "ዷዝ ባጉና" ቀበሌ ኦፖ ጎጥ ላይ ከፍተኛ ውጊያ በማድረግ እንስሳቱን ማስመለስ መቻሉ ታውቋል።

​የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ሰላም ግንባታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደሰ ታደለ በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ፤ የከተማ አስተዳደሩ የጸጥታ አካላት ማኅበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና የአካባቢው ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲጠበቅ ሁልጊዜም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዚህም ማረጋገጫው አመራሮቹን ጨምሮ የፖሊስና የሚሊሻ አባላት በውጊያው በቀጥታ በመሳተፍ ያስመዘገቡት ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፣ ለጸጥታ ኃይሉ አባላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

​በግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል የሥራ ሂደት አስተባባሪ ኢንስፔክተር በካማ አየለ በበኩላቸው፤ ማኅበረሰቡ የክረምት የልማትና የእርሻ ሥራዎችን በሰላም ከማከናወን ጎን ለጎን፣ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመቀናጀት የአካባቢውን ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

​በተመሳሳይ፣ በከተማው ሰላም ግንባታ ጽሕፈት ቤት የሚሊሻ አስተባባሪ አቶ ጌትነት አምሳያ፤ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ አደሮችና አርሶ አደሮች እንስሶቻቸውን በዘመናዊ መንገድ በማርባትና በመጠበቅ፣ ሀብትና ንብረታቸውን ከዘራፊዎች ሊከላከሉ እንደሚገባ ገልጸዋል።

​በዚህ የጸጥታ ዘመቻ ከዘራፊዎች እጅ የተመለሱት 31 ከብቶች እና 2 አህዮች በአጠቃላይ 33 እንስሳት በዕለቱ ለባለቤቶቻቸው በሰላም ተረክበዋል።

መረጃው የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ነው።

በወረዳው በተከናወነው የተቀናጀ የሰላም ማሰከበር ስራ በጠላት ሀይል ላይ ከፍተኛ የሞራል እና የንብረት ኪሳራ ማሳደር ተችሏል አቶ አብዱሰላም ኢብራሂም።(ሸርቆሌ ሰኔ 09/2018 ዓ ም የክልል...
17/06/2026

በወረዳው በተከናወነው የተቀናጀ የሰላም ማሰከበር ስራ በጠላት ሀይል ላይ ከፍተኛ የሞራል እና የንብረት ኪሳራ ማሳደር ተችሏል አቶ አብዱሰላም ኢብራሂም።

(ሸርቆሌ ሰኔ 09/2018 ዓ ም የክልል እና የዞን ከፍተኛ የፀጥታ ዘርፍ አመራሮች በወረዳው እየተከናወኑ ያሉ አሁናዊ የሰላም ማሰከበር ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

የክልሉ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዱሰላም ኢብራሂም በዚህ ወቅት እንደገለጹት የወረዳው የተቀናጀ የፀጥታ ሀይል የወረዳውን ሰላም ለማሰጠበቅ እያከናወነ ባለው ስራ አበረታች ውጤት ማሰመዝገብ መቻሉን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ከጠላት ሀይል የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለማከሸፍ የወረዳው የተቀናጀ የፀጥታ ሀይል በልዩ ትኩረት መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።

የክልሉ ሰላም ግንባታ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡሳም የሱፍ በበኩላቸው የወረዳውን የተቀናጀ የፀጥታ ሀይል የጠላት ሀይል ይዞት የመጣውን ፈንጅ እና ዓላማ በማምከን ያከናወነው አኩሪ ተግባር የጠላት ሀይልን በእጅጉ ያሳፈረ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሸርቆሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰማኒ ሀሰን በበኩላቸው የወረዳው የተቀናጀ የፀጥታ ሀይል በድንበር በኩል በተቀሳቀሰው የጠላት ሀይል ላይ ከባድ ኪሳራ በማድረስ የወረዳው ሰላም ማሰጠበቅ መቻሉን ገልጸዋል።

በውይይቱም የህዝቡን ሰላም ለማሰጠበቅ እየተከናወኑ ያሉ የሰላምና ፀጥታ ስራዎች ይበልጥ መጠናከር መቻል እንዳለባቸው አመራሮቹ አቅጣጫ በማሰቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል።

መረጃው የሸርቆሌ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።

የሰላም፣ፀጥታ እና ፍትህ ህብረት  አመራሮችና የብልጽግና ፓርቲ አባላት "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል ርዕሰ ጉዳይ  በተዘጋጀው ሰነድ  ውይይት እያካሄዱ ነዉ፤****( ሰኔ ...
16/06/2026

የሰላም፣ፀጥታ እና ፍትህ ህብረት አመራሮችና የብልጽግና ፓርቲ አባላት "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በተዘጋጀው ሰነድ ውይይት እያካሄዱ ነዉ፤
****
( ሰኔ 9/2018 ዓ.ም፤አሶሳ) የሰላም ፣ ፀጥታና ፍትህ ህብረት አመራርና የብልጽግና ፓርቲ አባላት 7ኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም እና “ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግሥት” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት እያካሄዱ ይገኛሉ።
***
የክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የህብረቱ ሰብሳቢ ኮሚሽነር መንግስቱ ቴሶ የመወያያ ሰነዱን ባቀረበቡበት ወቅትም 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላምና በስኬት መጠናቀቁ የአመራሩ እና የአባላቱ የስራ ውጤት መሆኑን ገልፀዋል።
***
ፓርቲው በቅድመ ምርጫ፤ በምርጫ ዕለትና በድህረ ምርጫ ያስቀመጣቸውን ስትራቴጂክ ግቦች እውን ከማድረግ እንፃር የአመራሩና የአባላት የነቃ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር ገልፀዋል።
*****
ጠንካራ ፓርቲ ለመፍጠር ጠንካራ አመራርና አባላትን መፍጠር እና የተደራጀ ማድረግ እንደሚገባም ኮሚሽነር መንግስቱ ቴሶ ገልፀዋል።
***
በመድረኩም የ2018 የውስጠ ፓርቲ ሥራዎች የዕቅድ አፈጻጸም ሁኔታ ፤ ስኬቶች ፤ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች ላይ ሰፊ ዉይይት ተደርጎ የአፈጻጸም ግምገማዉን መነሻ በማድረግ የአባላት ምዘና እንደሚካሄድም ተገልጿል።

በመድረኩ ላይም የቤኒሻንጉል ክልል ሠላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ፣የክልሉ ፍትህ ቢሮ፣የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የኦሮሚያ ጋምቤላና ቤኒሻንጉል የጋራ ማስተባበሪያ አመራሮች እና የብልጽግና ፓርቲ አባላት ላይ ተገኝተዋል ።

የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ Benishangul Gumuz Prosperity Party-ብልጽግና Benishangul Gumuz MilishaBenishangul Gumuz Media

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የጸጥታና ህግ ማስከበር ግብረ ኃይል በግንቦት ወር የተከናወኑ የስራ ሪፖርት እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫን ገመገመ ፥(አሶሳ ፡ ሰኔ 3/2018 ዓ/ም)፦ የአሶሳ ከተ...
10/06/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የጸጥታና ህግ ማስከበር ግብረ ኃይል በግንቦት ወር የተከናወኑ የስራ ሪፖርት እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫን ገመገመ ፥

(አሶሳ ፡ ሰኔ 3/2018 ዓ/ም)፦ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የጸጥታና ህግ ማስከበር ግብረሃይል የተሰሩ ስራዎችን እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫን በዛሬው እለት በከንቲባ ቢሮ አመራሩ በተገኙበት ገምግሟል ።

በሪፖርት ግምገማው በአሶሳ ከተማ ድንገተኛ የአሰሳና የኦፕሬሽን ስራ ተደርጎ የተለያዩ ጸረ ሰላም ኃይልን በቁጥጥር ስር በማል በየመጡበት ክልል የመረጃ ልውውጥ በማድረግ ወንጀል ፈጽመው የመጡትን ወደ መጡበት ክልል የማስረከብ ስራዎች ተሰርቷል ። እንዲሁም ጨለማን ተገን በማድረግ የተሽከርካሪ ስርቆት በፈጸሙት ላይ ተይዘው ምርመራ እየተሰራባቸው እንደሚገኝም በሪፖርቱ ተመላክቷል ።

በግዳጅ አፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በመቋቋም ጥምር የጸጥታ ኃይሉ አኩሪ ስራዎችን መስራቱን ተገልጿል ።

7ኛው ሀገራዊ የምርጫ አስቻይ ሁኔታዎች በመፍጠር ጸጥታ ኃይሉ አመርቂ ስራዎችን አስቀድሞ በመስራቱ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅም ተደርጓል ተብሏል ።

የሪፖርት ግምገማውን የመሩት የአሶሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አብዱልከሪም አብዱረሂም እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት የጸጥታ ኃይሉ ዝግጁነት በላቀ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በቀጣይም በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ፖሊስ ከሌሎች የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀራረብ እንዲሰሩ ተናግረዋል ።

ክቡር ከንቲባ አብዱልከሪም ለዚህ ውጤታማ ስራ መገኘት የአካባቢው ማህበረሰብና የተለያዩ በጎ ፈቃደኞች ከጥምር ጸጥታ ኃይሉ ጎን መቆማቸውን ያመላክታል ብለዋል ።

በቀጣይም የተጀመረውን የልማትና ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ ኃላፊነት የከተማው ማህበረሰብና የጸጥታ ኃይሉ በላቀና በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ክቡር ከንቲባው አሳስበዋል ።

በመጨረሻም የክልሉ ፖሊስ ኮሙኒኬሽን ከፍተኛ መኮንኖች እና የከተማ አስተዳደርና የወረዳ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና አመራሮች እንዲሁም የአሶሳ ደንብ አስከባሪዎች በሪፖርት ግምገማው ተገኝተዋል ።

መረጃው የአሶሳ ከተማ አስተዳደፓሊስ መምሪያ ነው

ፅንፈኛው ዘራፊ ቡድን ህዝብን ሲዘርፍበት የነበረ ህገ-ወጥ ጦር-መሳሪያና ቦምብ በቁጥጥር ስር ዋለ።       ***************************              (ባምባሲ፦ሰኔ 0...
09/06/2026

ፅንፈኛው ዘራፊ ቡድን ህዝብን ሲዘርፍበት የነበረ ህገ-ወጥ ጦር-መሳሪያና ቦምብ በቁጥጥር ስር ዋለ።
***************************

(ባምባሲ፦ሰኔ 02/2018 ዓ/ም)

ፅንፈኛው ዘራፊ ቡድን ህዝብን ሲዘርፍበት የነበረ ህገ-ወጥ ጦር መሳሪያና ቦምብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ኮ/ር ሀሩን ሄረላ ገለፁ።

የእነ ከፍያለው ፅንፈኛው ዘራፊ ቡድን በተለያዩ ጊዜያት እና ወቅት አንበሳ ጫካ እስከ ቀሽማንዶ ቁጥር ሁለት ድረስ ቡድናቸውን ይዘው በመዘዋወር ፋኖ ብሎ ራሱን የሚጠራውን የዘራፊ ብድንን ለማጠናከር ከዚህ በፊት የህዝብ መመላለሻ ተሽከርካሪዎችን በማስቆም በሚልየን የሚቆጠሩ ገንዘቦችን በመዝረፍ ላይ ያሉ በተደረገው የኦፕረሽን ስራ ገንዘቡን ከዘራፊው ቡድን ማስቀረታችንን ኮማንደሩ አስታውሶም ፤ዛሬ በተደረገው አሰሳ እና ደፈጣ ልዩ ቦታው አባ ሞቲ ተራራ ሰላሀዲን መርቀኒ እርሻ ልማት ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ የሽብር ቡድኑ ተባባሪ ግለሰቦችንና የተለያዩ ህገ-ወጥ ጦር መሳሪያዎች የተያዙ ሲሆን አንድ ታጣፊ ክላሽ ከመሰል ተተኳሽ 30 ጥይት ጋር፣1 F-ONE ቦምብ ፣1 የጭስ ቦምብ እና 1 ኤስኬስ ክላሽ ከመሰል 10 ጥይት ጋር መያዙን አስታውቀዋል።

በተደረገውም የአሰሳና ደፈጣ ስራ ላይ የወረዳው ፖሊስ አባላት፣የከተማ አስተዳደር ፖሊስ አባላት እና የክልሉ አድማ ብተና ፖሊስ አባላት በመሰማራት የተያዙትን የዘራፊ ቡድኑን እና ከቡድኑ የተገኙትን ህገ-ወጥ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ለወረዳው ፖሊስ ገቢ ማድረጋቸውንም በመግለፅ ለጀግናው የፖሊስ አባላት ምስጋናውን አቅርበዋል።

ኮማንደሩም ከዚህ በፊትም ሠላም ፈላጊው እና ወንጀል ጠል ማህበረሰባችን በሚያደርግልን ጥቆማ እና መረጃ ትብብር የላቀ ምስጋና ያቀረቡ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ መስጠት ከማህበረሰቡ የሚጠበቅ የዘወትር ልምድ መሆን አለበት ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈው
የቀጣይ ስራችንንም ለህዝባችን የምናቀርብ ይሆናል ሲሉ አስታውቀዋል።

"በጀግንነት መጠበቅ፤በሠብዓዊነት ማገልገል"!!
(ሰኔ 02/2018 ዓ/ም፦ባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት)
ባምባሲ

Address

Benishangul Gumuz
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category