25/06/2026
በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን ክቡር አቶ ብጅጋ ፃፊዮ ገለፁ።
በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ በዞኑ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ብጅጋ ፃፊዮ ገልፀዋል።
የካማሺ ዞን ሰላም ግንባታና ፀጥታ መምሪያ ፣ሚሊሺያ ጽ/ቤትና ፖሊስ መምሪያ በ2018 ዓ.ም በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ የተሰሩ የስራ አፈፃፀም ሪፖርርቶችን የዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ፃፊዮ በተገኙበት ተገምግሟል።
የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ፃፊዮ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች የተረጋጋ ሰላምን በመፍጠር የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲከናወኑ የፀጥታ ዘርፉ የማይተካ ሚና ማበርከት በቻሉን ገልፀዋል።
በዞኑ የተረጋጋ ፖለቲካን በመፍጠርና አስተማማኝ ሰላምን በመገንባት፣ የህዝቡን ደህንነት በማስጠበቅ ፣የህግ የበላይነት በማስከበር ረገድ በፀጥታ አባላቱ፣በመንግስ መዋቅሮችና በህዝቡ የተቀናጀ ጥረት አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉ አቶ ብጅጋ ተናግረዋል።
7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተዓማኒ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ በዞኑ አስተማማኝ ሰላም መኖሩን አንዱ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ብጅጋ የተገኘውን ሰላም መጠበቅና መንከባከብ ባህል ማድረግ አለብን ብለዋል።
በፀጥታ ዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ህዝቡ የሰላም ባለበት በማድረግና ማህበረሰቡን ያሳተፈ የፀጥታ ስርዓትን መገንባት ይገባል ብለዋል።
በዞኑ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ወንጀሎችን ቀድሞ በመከላከል የመረጃ አሰባሰብና ትንተናን አቅምን ማሳደግ ይጠበቃልም ብለዋል ።
የተቋማትንና የወጣቶችን ቅንጅታዊ አሰራር በጥብቅ ዲሲፕሊን በመምራት ለአንድ ዓላማና ውጤት እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በፀጥታ ዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠልና ክፍተቶችን ደግሞ በአንድነት፣ በቁርጠኝነት እና በከፍተኛ የሀላፊነት ስሜት በማረም ዞኑን ለልማት እና ለኢንቨስትመንት ምቹ በማድረግ የብልጽግ ጉዟችንን እውን ማድረግ አለብን በማለት ዋና አስተዳዳሪው የሥራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የካማሺ ዞን ሰላም ግንባታና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ ቤከማ ጉዲና በበኩላቸው በዞኑ የውስጥ ሰላምን ከማፅናት ባለፈ ከአጎራባች የክልል ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጋር በርካታ የሰላም ጥምር ኮሚቴ ስራዎች በመስራት የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነቶችን ማጠናከር ተችሏል ብለዋል።
ህዝቡ በዞኑ የተገኘውን አስተማማኝ ሰላም በመጠቀም ያለምንም የፀጥታ ስጋት የልማት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት አቶ ቤከማ የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃልም ብለዋል።
አቶ ቤከማ አክለውም በ2018 በጀት ዓመት በፀጥታ ዘርፉ የታዮ ስኬቶችን አጠናክሮ ከማስቀጠል ባለፈ የነበሩ ክፍተቶችን በማረም በ2019 በጀት ዓመት ውስጥ በማካተት በትኩረት እንደሚሰሩ አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም በ7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በሪፖርት ግምገማ መድረኩ ላይ የዞንና የካማሺ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የካማሺ ማረሚያ ቤቶች፣የዳቡስ ሻለቃ አድማ ብተና የፀጥታ አመራሮችና አባላት ፣የሁሉም ወረዳ አስተባባሪ አመራሮች፣የሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማጎሌዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን የካማሺ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።