የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office

የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office, Legal, Benishangul Gumuz, Addis Ababa.

ቡልድግሉ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማራው ለሚሊሻ አባላት ለማበረታታት የገንብ ድጋፍ አደረገ።፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦።(ቡልድግሉ፣ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም) ቡልድግሉ ወረዳ  በኩርሙክ ወረዳ በግ...
23/08/2026

ቡልድግሉ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማራው ለሚሊሻ አባላት ለማበረታታት የገንብ ድጋፍ አደረገ።
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦።
(ቡልድግሉ፣ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም) ቡልድግሉ ወረዳ በኩርሙክ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማሩ ሚሊሻያ አባላት 150,000 ብር ጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገላቸው ።

የቡልድግሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በክሪ አብዱላሂ ሚሊሻ አባላቱ ከመንግስት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት በመወጣት እና የክልሉን ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን እያበረከቱት ላለውን አስተዋፆኦ ምስጋና አቅርበዋል።

በዚህም አጠቃላይ ለክልሉ ህዝብ እና መንግስት ኩራት መሆናቸውንም ተናግረው ለወደፊቱም ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።

የተደረገላቸውን ድጋፉ የቡልድግሉ ወረዳ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጠይብ ሰቢት በቦታው ተገኝተው ለሚሊሻ አባላቱ አስረክበዋል ሲል የቡልድግሉ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በፌስቡክ ገፁ አስፍሯል ።

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል በመንጌ ወረዳ ፀለንገር ቀበሌ ግዳጅ ላሉ  የሚኒሺያ አባል የቀበሌው ወጣቶች የሰብሎች አረም ቁጥጥር ስራን ሰርተዋል  ።መረጃው የመንጌ ወረዳ ግብርና ...
19/08/2026

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል በመንጌ ወረዳ ፀለንገር ቀበሌ ግዳጅ ላሉ የሚኒሺያ አባል የቀበሌው ወጣቶች የሰብሎች አረም ቁጥጥር ስራን ሰርተዋል ።

መረጃው የመንጌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ነው

በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ ውይይት ተካሄደ(ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም.) የክልሉ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ በሚስተዋሉ ችግሮችና በመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ...
17/08/2026

በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ ውይይት ተካሄደ

(ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም.) የክልሉ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ በሚስተዋሉ ችግሮችና በመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ ዘርፉ በስግብግብነትና በብልሹ አሠራር እየተፈተነ መሆኑ ተጠቁሟል። በተጨማሪም የሌሊት ነዳጅ መቅዳት፣ የስርጭት አሻጥር፣ ለግለሰቦች በርካታ ሊትር ነዳጅ እንዲቀዱ ደብዳቤ መጻፍ፣ ሕገወጥነትን መደበቅና መጠባበቂያ አለማስቀመጥ ጨምሮ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች ተነስተዋል።

በውይይቱም በነዳጅ ስርጭት ሂደትም ለሕዝብ ትራንስፖርት፣ ለፀጥታ ተቋማት፣ ለኮሪደር ሥራዎችና ለሌሎች ወሳኝ አገልግሎቶች ቅድሚያ እንዲሰጥ ተጠቁሟል።

የቢሮው የፀጥታ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢሳም ዩሱፍ፣ የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ የፀጥታ ኃይሉ ግንባር ቀደም በመሆኑ ለፀጥታ ተቋማት በተገቢው ሁኔታ የነዳጅ አቅርቦት ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸው በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በመተባበር፣ ተጠያቂነትን ተፈጻሚ በማድረግና ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምሳሉ ኢረና በበኩላቸው፣ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚስተዋለው ሕገወጥነት በእንጭጩ ካልተፈታ በቀጣይ ከፍተኛና አሳሳቢ የፀጥታ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል በአፅንኦት ተናግረዋል።

የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች መኖራቸውን በማመን፣ በቀጣይ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት ሕጋዊና ፍትሐዊ አሠራርን ለማረጋገጥ ቃል ገብተዋል።


#ነዳጅ #አቅርቦትናስርጭት #ተጠያቂነት

የኦቤ ኡቤ ኢሸ ፍቤጉ ቀበሌ በግዳጅ ላይ ለሚገኘው የሚሊሻ ሀይል የእርድ ፍየል ድጋፍ አደረጉ።(ሸርቆሌ ነሐሴ 09/2018 ዓ ም ድጋፉንም የሸርቆሌ ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ መቶ አለቃ አብራ...
15/08/2026

የኦቤ ኡቤ ኢሸ ፍቤጉ ቀበሌ በግዳጅ ላይ ለሚገኘው የሚሊሻ ሀይል የእርድ ፍየል ድጋፍ አደረጉ።

(ሸርቆሌ ነሐሴ 09/2018 ዓ ም ድጋፉንም የሸርቆሌ ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ መቶ አለቃ አብራሴን አሚሊ ተቀብለዋል።

የሸርቆሌ ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ መቶ አለቃ አብራሴን አሚሊ ድጋፉን ሲቀበሉ እንደገለጹት ድጋፉ በግዳጅ ላይ የሚገኙ የሚሊሻ አባላት ግዳጃቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲወጡ የሚያነሳሳ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም መሰል ድጋፎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

መረጃው የሸርቆሌ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።

ቡልድግሉ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማራው ለሚሊሻ አባላት ሁለት የእርድ በግና 15,000ብር ድጋፍ አደረገ።፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦።(ቡልድግሉ፣ነሀሴ 8/2018 ዓ.ም) ቡልድግሉ ወረዳ  በኩርሙ...
14/08/2026

ቡልድግሉ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማራው ለሚሊሻ አባላት ሁለት የእርድ በግና 15,000ብር ድጋፍ አደረገ።
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦።
(ቡልድግሉ፣ነሀሴ 8/2018 ዓ.ም) ቡልድግሉ ወረዳ በኩርሙክ ወረዳ በግዳጅ ላይ ለተሰማሩ ለሚሊሻያ አባላት ሁለት በግና 15,000 ብር ድጋፍ አደረገላቸው ።

የቡልድግሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በክሪ አብዱላሂ ሚሊሻ አባላቱ ከመንግስት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት በመወጣት እና የክልሉን ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን እያበረከቱት ላለውን አስተዋፆኦ ምስጋና አቅርበዋል።

በዚህም አጠቃላይ ለክልሉ ህዝብ እና መንግስት ኩራት መሆናቸውንም ተናግረዋል።

የተደረገላቸውን ድጋፉ የቡልድግሉ ወረዳ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልቃሲም ዑሱማንና የወረዳው ሚሊሺያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጠይብ ሰቢት በቦታው ተገኝተው ለሚሊሻ አባላቱ አስረክበዋል።

መረጃው የቡልድግሉ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ2019ዓ.ም በጀት ዓመት የበጀት ዕቅድ ድልድልን አፀደቀ።ነሀሴ 7/2018ዓ.ም የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ለ2019ዓ.ም የተመደበውን በጀት ከጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አባላት ...
13/08/2026

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ2019ዓ.ም በጀት ዓመት የበጀት ዕቅድ ድልድልን አፀደቀ።

ነሀሴ 7/2018ዓ.ም የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ለ2019ዓ.ም የተመደበውን በጀት ከጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አባላት ጋር የበጀት ዕቅድ ድልድሉን በመስራት በዛሬው ዕለት አፅድቀዋል ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አብዱሠላም ኢብራሂም እንደገለፁት በተደረገው የበጀት ድልድል መሠረት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት አምባ አስራ ሁለት ቀበሌ የሚሊሻ አባላትና የቀበሌው አመራሮች ባደረጉት የጸጥታ ኦፕሬሽን የበግ ስርቆት የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አዋሉ።በቀ...
12/08/2026

በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት አምባ አስራ ሁለት ቀበሌ የሚሊሻ አባላትና የቀበሌው አመራሮች ባደረጉት የጸጥታ ኦፕሬሽን የበግ ስርቆት የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አዋሉ።

በቀን 06/12/2018 ዓ.ም. ከጧቱ 12፡00 ሰዓት ገደማ በተካሄደው የጸጥታ ኦፕሬሽን፣ ግለሰቦቹ የአካባቢው ነዋሪ እንዳልሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በወንዝ ዳርቻ አካባቢ አራት በጎችን ከሰረቁ እና ካረዱ በኋላ ቆዳቸውን እየገፈፉ ባሉበት ሁኔታ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

የቀበሌው ሚሊሻ አባላትና አመራሮች በጊዜ የደረሱበት የጸጥታ እርምጃ የነዋሪዎችን ንብረት ከስርቆት ለመጠበቅና የአካባቢውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ የሚደረገውን ጥረት እጅግ የሚደነቅ ነዉ ።

በመሆኑም ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን በአፋጣኝ ማሳወቅ እና የንብረት ስርቆትን በጋራ መከላከል ይገባል።

ተጠርጣሪዎቹም በሕግ አግባብ ተጣርተው ተገቢው የሕግ ሂደት እንዲከተል ይጠበቃል።

ክብርና ምስጋና ለሚሊሻ አባላቶቻችንና ለቀበሌው አመራሮች!!

ህብረተሰብን እና ንብረትን መጠበቅ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው።

የአካባቢን ሠላም በመጠበቅ ላይ ለሚገኘው የወረዳው የሚሊሽያ አባላት ድጋፍ ተደረገ ******************************(አቡራሞ:- ነሐሴ 5/12/2018ዓ.ም)የአካባቢን ሠላም በመ...
12/08/2026

የአካባቢን ሠላም በመጠበቅ ላይ ለሚገኘው የወረዳው የሚሊሽያ አባላት ድጋፍ ተደረገ

******************************
(አቡራሞ:- ነሐሴ 5/12/2018ዓ.ም)የአካባቢን ሠላም በመጠበቅ ላይ ለሚገኘው የወረዳው የሚሊሽያ አባላት ድጋፍ ተደርጓል

ሠላምን ለመጠበቅ በግዳጅ ላይ ለሚገኙ የወረዳው የሚሊሽያ አባላት የእርድ ፍየሎችና ትጥቅ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል

በድጋፉ አሰጣጥ ወቅት የአቡራሞ ወረዳ ሠላም ግንባታና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሳ ኢብራሂም እና የአቡራሞ ወረዳ ሚሊሽያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያሲር ማህሙድ ተገኝተዋል።

መረጃው የአቡራሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።

የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ሁኔታዎች ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ አሰቀመጠ ።የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በስፋት በመወያየት ቀጣይ...
11/08/2026

የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ሁኔታዎች ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ አሰቀመጠ ።

የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ በስፋት በመወያየት ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

በውይይቱ ወቅት የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ እና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ይበልጥ በማጠናከር ህብረተሰቡ የክረምት ግብርና ሥራውን በሙሉ ትኩረት እና ጥረት እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ጌታሁን አብዲሳ አክለውም፤ የባዕዳን ተልዕኮ በመቀበል በሕዝቡ ላይ ጥቃት ለማድረስ የሚንቀሳቀሱ ጥቂት የጽንፈኝነት አስተሳሰብ የተጠናወታቸው ኃይሎች በሕዝቡ እና በጸጥታ አካላት የተቀናጀ ትብብር አይቀጡ ቅጣት እየተቀጡ ይገኛሉ ብለዋል።

አንጻራዊ ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ እና የልማት እንቅስቃሴዎችን ለማስቀጠል ህብረተሰቡ ከጸጥታ ኃይሎች ጎን በመቆም የሚያደርገውን የተለመደ ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪያቸውን ደግመው አስተላልፈዋል።

በጎነት በተግባር፦ የባምበሲ ወረዳ የበጎ ሥራ በ44 ቀበሌ ተጀመረነሐሴ 05/2018 ዓ.ምበባምበሲ ወረዳ 44 ቀበሌ በበጎ አድራጎት ወጣቶች ተነሳሽነት ለአንዲት እናት የመኖሪያ ቤት ግንባታ ተ...
11/08/2026

በጎነት በተግባር፦ የባምበሲ ወረዳ የበጎ ሥራ በ44 ቀበሌ ተጀመረ

ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም

በባምበሲ ወረዳ 44 ቀበሌ በበጎ አድራጎት ወጣቶች ተነሳሽነት ለአንዲት እናት የመኖሪያ ቤት ግንባታ ተጀመረ።

የቤቱ ግንባታ የሚከናወነው በወጣቶች በጎ ፈቃድና ተነሳሽነት ሲሆን፣ የግንባታውን የሚያስፈልጉ ሙሉ የቤት ሥራ ማቴሪያሎችም በማቅረብ ሥራው በይፋ ተጀምሯል።

የጅማሬው መርሃ ግብር በባምበሲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ፣ በአቶ አብዱልዋሂድ አዙቤር በተገኙበት አሰጀምሯዋል፣ በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም በሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ አመራሮች በተገኙበት ተከናውኗል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ በመርሃ ግብሩ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ በለውጡ ሂደት የተጀመሩ ማህበራዊ ተሳትፎና የመረዳዳት ሥራዎች ለማህበረሰቡ ሰላም፣ ልማትና መረጋጋት የሚያበረክቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በጎነት፣ እርስ በርስ መረዳዳትና መተባበር በማህበረሰቡ ውስጥ በማጠናከር መቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።

በጎነት ከቃል ወደ ተግባር

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በበጎነት ሥራዎች ማህበረሰቡ ከተረጂነት ወደ ራስን መቻል እንዲሸጋገር የሚያግዙ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጿል።

ይህ የቤት ግንባታ ተግባርም በጎነት በተግባር ሲገለጽ ምን ያህል ለዜጎች ተስፋና የኑሮ መሻሻል ሊያመጣ እንደሚችል ያሳያል።

በጎ ሥራ ለዚህች ምድር ብቻ የሚገደብ አይደለም፤ በትውልድ የሚተላለፍ የሰብዓዊነት ትሩፋት ነው። ስለሆነም ወጣቶች በበጎ ሥራዎች በትኩረት በመሳተፍ፣ የመረዳዳትና የመተባበር ባህልን ማጠናከር ይገባቸዋል።

በጎነት ተስፋን ይፈጥራል፤ መተባበር ለውጥን ያፋጥናል።
እጅ ለእጅ በመያዝ የተሻለች ማህበረሰብ እንገንባ!

መረጃው የባምባሲ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ነው

Address

Benishangul Gumuz
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category