ሕጉ ምን ይላል ?

ሕጉ ምን ይላል ? Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ሕጉ ምን ይላል ?, Lawyer & Law Firm, Bole Street, Addis Ababa.

⚖️"ሕጉ ምን ይላል"is the leading legal awareness page in providing various legal issues to communities.ABEBAW ABEBE is a Legal Advocates,Moderator,Author,founder and CEO for Maya Charitable Organization.📞+251991228122 +251942406060 www.abebawabebelawfirm.com

22/05/2026

/" ሰበር ሰሚ ችሎት " ምንድነው ?
በኢትዮጵያ ሕግ ዉስጥ " የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት " ትልቅ ተፅዕኖ ያለው ተቋም ነው ።

ምክንያቱም ፦ የሚሰጠው ዉሳኔ " አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ " /binding precedent / ስለሆነ ነው ።

ሰበር ያለዉን ሕግ መሠረት አድርጎ ይሰራል ፣ ሕጉ ምን ማለት እንደሆነ የመጨረሻ ትርጉም ይሰጣል ፣ ትርጉሙ ሌሎች ፍርድ ቤቶችን ያስገድዳል ።

⚫️ " ሰበር ሰሚ ችሎት " ምንድነው ? ✍️

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዉስጥ ያለ ልዩ ችሎት ነው ።
( Cassation Bench ) ተብሎ ይጠራል ።

_ ዋናው ተግባሩ ፦ በፍርድ ዉሳኔ ዉስጥ " መሠረታዊ የሕግ ስህተት " / Fundamental error of Law / ማረም ነው ።

_ መሠረታዊ የሕግ ስህተት /Fundamental error of Law/ ማለት ለምሳሌ ፦

_ ህጉን በተሳሳተ ሁኔታ መተርጎም
_ ስልጣን የሌለው ፍርድ ቤት ዉሳኔ መስጠት
_ የሕገ መንግስት መብት መብት / Constitutional right / መጣስ
_አስገዳጅ ስነ_ ስርዓት /mandatory procedure / አለመከተል
_ አስቀድሞ የተሰጠ የሕግ ትርጉም / precedent / መተው

⚫️ ለምን አስፈላጊ ሆነ ✍️

ምክንያቱም ዉሳኔዉ " አስገዳጅ " /binding / ነው ።
በኢትዮጵያ ሕግ ፦ የሰበር ሰሚ ችሎት ትርጓሜ ሁሉንም ፍርድ ቤቶች ያስገድዳል ።

ይህ በ federal courts proclamation No.1234/2021 ዉስጥ ተደንግጓል ። ስለዚህ ፦

_ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች /Federal Courts /
_ የክልል ፍርድ ቤቶች / Regional Courts / ሁሉም የሰበርን የህግ ትርጉም /interpretation / መከተል አለባቸው ።

⚫️ ይህ በተግባር ምን ያደርጋል ? ✍️

የህግ አሰራር አንድነትን ( uniformity ) ይፈጥራሉ ።
አንድ ሕግ በአዲስ አበባ አንድ ትርጉም ፣ በመቀሌ ሌላ ትርጉም ፣ በባህር ዳር ሌላ ትርጉም እንዳይኖረው ያደርጋል ።

⚫️ የሰበር ዉሳኔ ምን ያህል ሀይል አለው ? ✍️

በተግባር እጅግ ትልቅ ። የሰበር ሰሚ ችሎት ትርጓሜ ራሱ እንደ አዲስ ሕግ ይቆጠራል ወይም ይታያል ።
" የሰበር የህግ ትርጓሜ " በተግባር የአዲስ ሕግ ያህል ተፅዕኖ አለው ።

⚫️ አንዳንድ ጊዜ ሰበር ሕጉን ያሰፋዋል ✍️

ህግ ግልጽ ካልሆነ ፦ በሕግ ዉስጥ ክፍተት (loophole ) ወይም አሻሚነት ( ambiguity ) ሲኖር የሰበር ሰሚ ችሎት የሚሰጠው ትርጓሜ ያንን ክፍተት ይሞላል ።

⚫️ ጠበቆች ለምን Cassation ይወዳሉ 😀

ምክንያቱም " strong authority " ነው ።
ጠበቃ ፍርድ ቤት ዉስጥ " የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ ......... ብሎ ሲናገር ክርክሩ ክብደት ያገኛል ።

በአጭሩ፦

⚫️ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ፦ ✍️

_ የመጨረሻ የሕግ ትርጉም ይሰጣል ።
_ የሕግ ትርጉሙ ሌሎች ፍርድ ቤቶችን ያስገድዳል ።
_ መሠረታዊ የሕግ ስህትን /Fundamental error of Law/ ያርማል ።
_ የቀደመዉ ዉሳኔዉ አስገዳጅ መመሪያ ስለሚያደርገዉ የ " precedent " ሀይል አለው
_ ሁሉም ፍርድ ቤቶች ተፈፃሚነት ስላለዉ " የሕግ አንድነትን " ይፈጥራል ።

,,,,,,,,✍️✍️✍️

20/05/2026

ግምት ሲባል የቤቱን የግንባታ ዋጋ እንጂ የገበያ ዋጋን ማለት አይደለም
*****
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1179 መሠረት ባለይዞታው ሳይቃወም በይዞታው ላይ ቤት የሠራ ሰው የሕንፃው ባለቤት ቢሆንም፣ ይህ መብት የመሬቱን ባለይዞታነት ስለማያካትት የመሬቱ ባለይዞታ ለቤቱ ተገቢውን ግምት በመክፈል ቤቱን አስለቅቆ የመረከብ መብት አለው። ግምት ሲባል የቤቱን የግንባታ ዋጋ እንጂ የገበያ ዋጋን ማለት አይደለም።​ የገበያ ዋጋ ማለት ቤቱ ለሽያጭ ቢቀርብ ሊያወጣ የሚችለው ዋጋ ሲሆን፤ ​የግንባታ ዋጋ ግን ቤቱን ለመገንባት የወጣውን ወጪ የሚመለከት ነው።
ሰ/መ/ቁ.249171 (ጥቅምት 05 ቀን 2017 ዓ.ም)

    /የፍርድ አፈጻጸም ስርአት /የውሳኔ መተግበር ሂደት/ፍ/ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር ወይም ውጤት የሚለውጥበት ስርአትየፍርድ አፈጻጸም ስርአት ህጉን መሰረት በማድ...
20/05/2026

/የፍርድ አፈጻጸም ስርአት /የውሳኔ መተግበር ሂደት/

ፍ/ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር ወይም ውጤት የሚለውጥበት ስርአት
የፍርድ አፈጻጸም ስርአት ህጉን መሰረት በማድረግ የፍትሐ ብሔር ስነ-ስርዓት ህጉን መሰረታዊ ዓላማ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በአነስተኛ ወጪ፣ ጊዜና ጉልበት በተፋጠነና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲፈፀም በሚያስችል አግባብ ተግባዊ መደረግ ይኖርበታል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 91622 ቅጽ 16፣ ፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 378፣ 392፣ ፍ/ብ/ህ/ቁ. 998፣ 1195 እና 1196፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 40/1/ እና /2/
በሕግ አግባብ ታይቶ የተሰጠ ፍርድ እንደ ፍርዱ መፈፀም ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁጥር 378 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ያሣያሉ፡፡ በእነዚህ ድንጋጌዎች በተዘረጋው ስርዓት አግባብ በመመራት ካልሆነ በስተቀር በፍርድ ቤት የተሰጠ ውሣኔ በሌላ አካል ዋጋ የሚያጣበት አግባብ አይኖርም፡፡ በሕግ አግባብ የተሰጠ ፍርድ ዋጋ እንዳይኖው የሚደረገው የዳግም ዳኝነት ወይም የፍርድ መቃወሚያ ጥያቄ በሕጉ በተዘረጋው ስርዓት ቀርቦ ከታየና ተቀባይነት ካገኘ ብቻ ስለመሆኑ ከፍ/ብሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 6 እና 358 ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ አንድ የአስተዳደር አካል በፍርድ ቤት ክርክር መረታቱን ከተረዳ በኋላ በሕጉ የተሰጠውን ስልጣን መነሻ በማድረግ ለፍርዱ መሰጠት መሠረት የሆነውን ማስረጃ ዋጋ በማሣጣቱ ምክንያት የፍርድ አፈፃፀም ዋጋ እንዲያጣ የማድረግ ውጤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 78/1/ እና 79/1/ እና /4/ ስር የተረጋገጠውንና የተከበረውን የነፃ ፍርድ ቤት መኖርንና የዳኝነት ስልጣን ትርጉም አልባ የሚያደርገው ነው፡፡
ይህ ብቻ ሣይሆን በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 37 ሥር የተረጋገጠው የዜጎች ፍትህ የማግኘት መብትም ውጤት ባለው መልኩ ተግባራዊ የሚሆንበት መንገድ ጠባብ እንዲሆን የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ክርክሮች መቋጫ እንዳይኖራቸው የሚጋብዝ የፍርድ ቤትን ጊዜ ጉልበትና በጀት ለብክነት የሚዳርግ እንዲሁም ሕዝቡ በፍርድ ቤት አመኔታ እንዳይኖረው የሚያደርግ ነው፡፡ የነፃ ፍርድ ቤት መገለጫው ደግሞ የሕግ የበላይነት መኖሩና መረጋገጥ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ውጤታማ የሚሆነው አንዱ የመንግሥት አካል ሌላኛውን ሲቆጣጠረው ከመሆኑ በተጨማሪ ፍርድ ቤት የራሱን ውሣኔ ዋጋ የማያሣጣና የሕግ መሠረት የሌለውን የአስተዳደር አካል እርምጃ ውድቅ ሲያደርገው መሆኑ የሚታመን ነው፡፡ ፍርድ ቤት በሕገ መንግስቱ አንዱ የመንግስት አካል እንደመሆኑ መጠን የመንግስት የስልጣን አጠቃቀም የተወሰነና የተገደበ መሆኑ ሊያረጋግጥ እንደሚገባ ይህ ሊከናወን ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ ደግሞ በፍርድ ቤት የተሰጠ ውሣኔ ትርጉም እንዲኖረው በማድረግ ስለመሆኑ በሕገ መንግስቱ ስለፍርድ ቤቶች ስልጣን ከተመለከቱት ድንጋጌዎች እና በአገሪቱ የሕግ አካል ከሆኑ አለም አቀፍ ስምምነቶች ውስጥ ከሰፈሩት መርሆዎች ይዘትና መንፈስ የምንረዳው ጉዳይ ነው፡፡
በኢ.ፌ.ዲ. ሪ ህገ መንግስት ከላይ እንደተጠቀሰው ሕገ መንግስቱ ከተመሠረተባቸው መርሆች አንዱ የሕግ የበላይነት ስለመሆኑ በሕገ መንግስቱ መግቢያው ላይ የሰፈረ ጉዳይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ለሁሉም ወገኖች እኩል ተፈፃሚነት ባለው ሕግ መመራት ያለበት ስለመሆኑም የሕገ መንግስቱን አንቀጽ 25 እና 13/1/ ድንጋጌን ይዘትና መንፈስ በማየት መረዳት የምንችለው ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም በሕግ አግባብ የተቋቋመ ፍርድ ቤት አከራክሮ መወሰን ብቻ ሣይሆን የወሰነው ውሣኔ ውጤት ባለው መልኩ ወደ ተግባር መለወጡን ጭምር ማረጋገጥ አብይ ሀላፊነትና ተግባር በመሆኑ ይህንኑ በሕግ የተሰጠውን ስልጣን አንድ የመንግስት አካል የሚዘረጋው አሠራር ወይም የሚወስደው እርምጃ በፍርድ ቤቶች የፍርድ ስርዓት ላይ /በዳኝነት አካሉ ላይ/ የሚያመጣው ውጤት በሕግ የተመሠረተና የሚገዛ ስለመሆኑ ማየት የግድ ይላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42501 ቅጽ 15 🙏🙏🙏

17/05/2026
17/05/2026

/ይህ መመሪያ ቁጥር 1134/2018 (በፈረንጅ አቆጣጠር 2026) የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎችን ዝግጅት እና ስርጭት ለመቆጣጠር ያወጣው መመሪያ የህግ ማጠቃለያ ነው (p. 1)።ዋና ዓላማ እና ተፈጻሚነትህጋዊ መሰረት፦ በጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/2016 አንቀፅ 58(2) መሰረት የወጣ ነው (p. 1)።ዓላማ፦ የስነ-ምግባር ጉድለት ያለባቸውን ማስታወቂያዎች በማስቀረት የማህበረሰቡን ባህል፣ እሴትና ጤና መጠበቅ (p. 1)።ወሰን፦ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ የጤና ማስታወቂያ አዘጋጆች፣ አስነጋሪዎች እና አሰራጮች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል (pp. 2-3)።ዋና ዋና ህጋዊ ግዴታዎችየቋንቋ አጠቃቀም፦ ማስታወቂያው ተደራሽነቱ በህዝብ በሚነገር ቋንቋ፣ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ በሆነ መንገድ እና ከልክ ያለፈ የሙያ ቃላት (jargons) የሌለበት መሆን አለበት (p. 3)።የተከለከሉ ቃላት፦ «ቀዳሚ ምርጫ»፣ «የሁሉም ምርጫ» እና መሰል አጋናኝ ቃላትን መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ ነው (p. 3)።ማካተት ያለባቸው መረጃዎች፦ የጤና ተቋሙ ስም፣ ደረጃ፣ በደረጃው መሰረት የሚሰጠው አገልግሎት እና የተቋሙ አድራሻ በግልፅ መቀመጥ አለበት (p. 3)።የስነ-ምግባር ክልከላዎች፦ ሌሎች ተቋማትን ማጥላላት፣ የላቀ የሙያ ክህሎት እንዳለ አድርጎ ማሳየት፣ ልዩ ንጥረ ነገር ወይም «የፈውስ ቦታ» እንደሆነ መግለፅ፣ እና «ካለመጡ ጤናዎ ይጎዳል» በማለት ማስፈራራት ክልክል ነው (p. 4)።የምስክርነት (Testimonial) ህግ፦ ምስክርነት በህክምና ህክምናው (clinical treatment) ላይ መሆን የለበትም፤ የምስክሩ የፅሁፍ ፈቃድና አገልግሎቱን በትክክል ማግኘቱ መረጋገጥ አለበት (p. 4)። ህጻናት ወይም የአእምሮ ህመምተኞች ከሆኑ የወላጅ/አስገዳጅ የፅሁፍ ፈቃድ ያስፈልጋል (p. 4)።የአሰራጮች ኃላፊነት እና ቅጣትየአሰራጭ ግዴታ፦ ማንኛውም ሚዲያ ወይም አሰራጭ ማስታወቂያው መመሪያውን ማሟላቱን እና ተቋሙ ህጋዊ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያለው መሆኑን ማረጋገጥ አለበት (pp. 4, 6)።የገንዘብ ቅጣት፦ መመሪያውን መጣስ ከ10,000 እስከ 100,000 ብር የሚደርስ አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ያስከትላል (pp. 5-6)።የሙያ ፈቃድ መታገድ፦ የተጣለውን ቅጣት በ3 ወር ውስጥ ያልከፈለ የጤና ተቋም የብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱ ቅጣቱን እስኪከፍል ድረስ ይታገዳል (p. 6)።አቤቱታ ማቅረብ፦ በቅሬታ ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎች በፌዴራል የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 መሰረት ይስተናገዳሉ (p. 6)።የተሻረ ህግ፦ የቀድሞው የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ መመሪያ ቁጥር 387/2005 በዚህ መመሪያ ተሽሯል::

15/05/2026

/ የአላባ (Usufruct) መብት በኢትዮጵያ ሕግ

አላባ ማለት የአንድ ንብረት ባለቤት የሆኑት መብቶች ተከፋፍለው፣ ባለቤቱ "እንደፈለጉ የማድረግ" (Abusus) መብቱን ለራሱ አስቀርቶ፣ ለሌላ ሰው በንብረቱ የመገልገል (Usus) እና ፍሬውን የመሰብሰብ (Fructus) መብት የሚሰጥበት የሕግ አግባብ ነው።

🔹 በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(1) እና በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1309-1358 እውቅና የተሰጠው መብት ነው።

➤የመብቱ ምንጭ ከውል፣ ከኑዛዜ ወይም በቀጥታ ከሕግ (ለምሳሌ በባልና ሚስት መካከል) ሊመነጭ ይችላል (ቁ. 1184-1185)።

➤ የአላባ መብት ለተጠቃሚው በሕይወት እያለ የሚሰጥ እንጂ በውርስ ወደ ወራሾች የማይተላለፍ የግል መብት ነው (ቁ. 1322)።

🔹 የተጠቃሚው መብቶችና ግዴታዎች
✅ መብቶች፦

ንብረቱን በይዞታው ስር የማድረግ እና የመገልገል መብት (ቁ. 1311)።

የተፈጥሮ እና የሲቪል ፍሬዎችን (ኪራይ፣ ወለድ) የመሰብሰብ መብት (ቁ. 1328-1331)።

ንብረቱ የፍጆታ ዕቃ (እንደ ጥሬ ገንዘብ) ከሆነ የመጠቀም/የማዘዝ መብት (ቁ. 1327)።

ንብረቱን ለሌላ ሰው በኪራይ የመስጠት መብት (ቁ. 1331)።

⚠️ ግዴታዎች፦

ንብረቱን በቅን ልቦና የመያዝ እና መሠረታዊ ለውጥ ያለማድረግ ግዴታ (ቁ. 1312)።

መደበኛ ጥገናዎችን የማከናወን እና ግብር የመክፈል ግዴታ (ቁ. 1313-1314)።

መብቱ ሲያልቅ ንብረቱን በዓይነት የመመለስ ግዴታ (ቁ. 1321)።

🔹 መብቱ ቀሪ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች
የአላባ ተጠቃሚው ሲሞት (ቁ. 1322 የቀዳሚው ድንጋጌ)።

የተቀመጠው የውል ጊዜ ሲያልቅ።

ተጠቃሚው መብቱን በፈቃዱ ሲተው (ቁ. 1323)።

ንብረቱ ሙሉ በሙሉ ሲወድም ወይም ሲጠፋ (ቁ. 1319)።

15/05/2026

/የወንጀል እስራት ቅጣት ማገድ ወይም መገደብ
የኢፊድሪ ወንጀል ህግ ማእቀፍ እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የህግ ትርጉም 🙏

መግቢያ
በኢፊድሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 192 እና 197 መሠረት አንድ በወንጀል የቅጣት እስራት የተወሰነበት ሰው ቅጣቱ ሊታገድ ወይም ሊገደብ እንደሚችል ተደንግጓል። በዚህ ጽሁፍ የአንድ ፍርደኛ ሰው ቅጣቱ እንዴት ሊገደብ እንደሚችል ለመገደብ ምን መስፈርቶች መሟላት እንዳለባቸው ግንዛቤ ለማስጨበጥ ቀርቧል።
1. የወንጀል እስራት ቅጣትን ማገድ ወይም ገደብ ምንድነው?..
በኢፊድሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 192 መሠረት የቅጣት ወንጀልን ማገድ ማለት አንድ ሰው በወንጀል ጥፋተኝነት ውሳኔ ተፈርዶበት የእስራት ቅጣት ከተወሰነበት በኋላ ይህ ቅጣት እንዳይፈጸም ፍርደኛው አመሉ ቢፈተን በተሰጠው የፈተና ጊዜ መልካም ጠባይ ያፈራል ተብሎ ፍርድ ቤቱ ሲያምን ቅጣቱ እንዳይፈጸም የሚያደርግበት በፍርድ ቤት ውሳኔ ወይም ትእዛዝ የፍርደኛው መብት የሚጠበቅበት መንገድ ነው።
2. በወንጀል የእስራት ቅጣት እንዲገደብ መሟላት ያለባቸው ነጥቦች ምንድን ናቸው?....
በኢፊድሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 192 እና 197 መሠረትአንድ ተከሳሽ በወንጀል ጥፈተኛ ተብሎ የቅጣት እስራት ከተላለፈለት በኋላ የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅበታል።
2.1 የእስራት ቅጣቱ መጠን አንቀጽ 194...
ፍርደኛው በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ ቅጣት የተላለፈበት እስራት ከአምስት አምስት አመት መብለጥ የለበትም።
2.2 የደረሰውን ጉዳት መካስ አንቀጽ 197...
የግል ተበዳይን ወይም ደረሰ የተባለውን ጉዳት በሚቻለው አቅም ወደ ነበረበት ለመመለስ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይጠበቅበታል
2.3 በመልካም ጸባይ እንዲመራ የሚሰጠውን ግዴታ መፈጸም አንቀጽ 197...
በፍርድ ቤት የመልካም ጸባይን ደንብን ለመጠበቅ በፍርድ ቤት የሚሰጠውን የግዴታ መመሪያ ወይም ትእዛዝ ማክበር ይጠበቅበታል
2.4 የፍርድ ቤት ወጪን መሸፈን አንቀጽ 197...
ፍርደኛው ቅጣቱ እንዲገደብለት በእርሱ ምክንያት በፍርድ ቤት የተፈጠሩ አስተዳደራዊ ወጪዎችን እንዲሸፍን በተሠጠው ጊዜ ውስጥ መክፈል ይጠበቅበታል።
2.5 የመልካም ጠባይ ዋስትና ማስያዝ አንቀጽ 197....
ፍርደኛው ቅጣቱ ቢታገድለት እንዲፈጽም የተሠጠውን ግዴታ ስለመፈጸሙ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በሚሰጠው ትእዛዝ መሠረት ዋስትና ለታገደለት የፈተና ጊዜ ድረስ ማስያዝ ይጠበቅበታል።
2.6 ከዚህ በፈት ፍርደኛው የተቀጣበት ቅጣት አይነት አንቀጽ 194....
ፍርደኛው ከዚህ በፊት ከሶስት አመት በላይ ቀላል እስራት ወይም በጽኑ እስራት የተቀጣ ከሆነ በአዲሱ ቅጣትም በእነዚህ ተመሳሳይ ቅጣት አይነት የማይቀጣ ከሆነ
2.7 ፍርድ ቤቱ ያመነበት እንደሆነ አንቀጽ 194..
ፍርድ ቤቱ ፍርደኛው ቅጣቱ ቢታገድለት ከማህበረሰቡ ጋር ቢቀላቀል መልካም የጸባይ ፍሬን እንደሚያፈራ የተረዳው እንደሆነ
2.8 ቅጣቱ በታገደለት ጊዜ ሌላ ወንጀል የማይሰራ ከሆነ....
በኢፊድሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 194 መሠረት ቀጣቱ የተገደበለት ሰው አንድን ወንጀል አስቦ የማይፈጽም እንደሆነ ገደቡ የሚጠበቅለት ይሆናል
3. ገደብን አስመልክቶ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ምን ይላል?
3.1 እርቅ በገደብ ለመለቀቅ መስፈርት ነው(የሰበር መዝገብ ቁጥር - 266395 ቀን - 26/06/2017 ዓ.ም)

ስለ ገደብ ጥያቄ በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 185700 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ከግል ተበዳይ ጋር ታርቆ ካሳ መክፈል በወንጀል ህጉ አንቀፅ 197 መሰረት ጥፋተኛው በተሰጠው የፈተና ጊዜ ውስጥ በመልካም ጠባይ እንዲመራ እና በፈተና ጊዜ ውስጥ ተገቢውን ፍሬ እንዲያፈራ በሚል ለመልካም ጠባይ አመራር ዋስትና የሚሰጥ ትዕዛዝ እንጂ ቅጣትን ለመገደብ ቅድመ ሁኔታዎች እንዳልሆኑ ትርጉም ሰጥቷል ፡፡

በወ/ህ አንቀፅ 192 ስር ቅጣቱን ለመገደብ ያልተቀመጡ ምክንያቶችን በመዘርዘር ከግል ተበዳይ ጋር ታርቆ ገንዘቡን አልከፈለም የሚል ምክንያት በማስቀመጥ እና ከተጠሪ በኩል ስለ እርቅ ጉዳይ ክርክር ሳይቀርብ በራሱ አነሳሽነት ያልተጠየቀ ዳኝነት በመስጠት ቅጣቱ ሊገደብ አይገባም በማለት መወሰኑ ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 185700 ላይ ከሰጠው የህግ ትርጉም ጋር የሚጣረስ ውሳኔ በመሆኑ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ አግኝተናል፡፡

3.2 ተከሳሽ ሕጻናት ልጆች ካሉት ቅጣት መገደብ ግደታ ነው፡- ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት ድንጋጌ ቅጣት እንዲገደብ በህጉ ክልከላ ካልተደረገበት በስተቀር ተከሳሽ ህጻናት ልጆች የሚያስተዳድር መሆኑን ገልጾ ባቀረበበት ፍ/ቤት በህጻናቱ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ቁሳዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት ሲባል ቅጣቱ ያለመገደብ መሠረታዊ የህግ ስህተት ነው።
ሰበር ሰሚ ችሎት = መ/ቁ 282248 /06/02/2017 ዓ/ም

4. በመጨረሻም ...
ፍርድ ቤቶች በፍርድ የሰጡትን የእስራት ቅጣች እንዳይፈጸም ለማድረግ ወይም ለማድረግ ከላይ የተቀመጡትን በኢፊድሪ ወንጀል ህግ 192፥194 እና 197 እንዲሁም ከእነዚህ ጋር አግባብነት ያለቸውን በህጉ የተቀመጡትን መሟያዋች ስለመሟላታቸው መመርመር ያለበት ሲሆን ፍርደኛውም ይህን ከመጠበቅ አንጻር ጽኑ ፍላጎትና የሚፈጽም መሆኑን ማሳየት አለበት። ይህንንም ሆነ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞች መሠረት ፍርድ ቤች ተግባራዊ ሊያደርጉ ይጠበቅባቸዋል።

በዚህ ፎቶ ምን ታዘባችሁ 🤔
11/05/2026

በዚህ ፎቶ ምን ታዘባችሁ 🤔

የዛሬ የችሎት ውሎ በዚህ መልኩ ተጠናቋል 💪    /ግንቦት 3/2018 በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እን...
11/05/2026

የዛሬ የችሎት ውሎ በዚህ መልኩ ተጠናቋል 💪
/ግንቦት 3/2018

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ።

መንሱር ጀማል የተባለው ተከሳሽ ግን አቃቢ ህግ መቃወሚያ ስላቀረበበት ዛሬ ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከድርጅቱ ጋር በተያያዘ በ1.9 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ፈቅዷል።

ባለፈው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከ5 ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጭ ባሉ ተጠርጣሪዎች ከሀገር እንዳይወጡ እና ከፍ ያለ ዋስትና አስይዘው የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ እንደማይቃወም አስረድቶ እንደነበር ይታወሳል።

ዛሬ በዋለው ዝግ ችሎት ተርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸው፣ ከእስር ተፈትተው በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

በዚህ መሠረት ከአንድ እስከ አራት ያሉ ተከሳሾች ማለትም ሰራዊት ፍቅሬ፣ ሰለሞን ቦጋለ፣ ይገረም ደጀኔና ዳንኤል ተገኝ በ500 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ሲፈቀድላቸው።

ስድስተኛና ሰባተኛ ተከሳሽ አብርሀም ግዛውና ካሊድ ናስር በ400 ሺህ ብር እንዲወጡ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ጠበቃ አበባው አበበ ነግረውናል።

አምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በተመለከተ አቃቢ ህግ ባቀረበው መቃወሚያ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ዛሬ 8 ሰዓት ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አበባው አበበ ተናግረዋል፡፡

ሁሉም ተከሳሾች ከሃገር እንዳይወጡ እገዳም ተጥሎባቸዋል ተብሏል።

ገዛ ጌታሁን

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

Address

Bole Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሕጉ ምን ይላል ? posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሕጉ ምን ይላል ?:

Share