07/04/2026
የውጭ ሀገር ገንዘብን በአደራ ማስቀመጥና መዘዙ
ውልን የሚያደርጉ ወገኖች የመዋዋል ነጻነት (Freedom of Contract) ያላቸው ቢሆንም ይህ የመዋዋል ነጻነት ፍጹማዊ አይደለም፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ተዋዋይ ወገኖች ውጭ ሀገር ገንዘብን በአደራ ለማስቀመጥ ውል ይዋዋላሉ፡፡ ይህንንም በተመለከተ ምንም እንኳን ተዋዋዮች የመዋዋል ነጻነት ያላቸው ቢሆነም በወንጀለኛ መቅጫ ህጋችንና በብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት የውጭ ሀገር ገንዘብ ተቀመጠው ገደብ በላይ መያዝም ሆ0ነ ማስቀመጥ በህግ የተከለከለ በመሆኑ ይህንን ህግ በመተላለፍ የሚደረግ ውል ህግ ወጥ ተግባር በመሆኑ ውሉ ሊጸናም ሆነ ሊፈጸም የማይችል ከመሆነጀም በላይ ወንጀል ተጠያቂነት ያመጣል፡፡
የፍብ/ህ/ቁ 1716 (1)፣1678፣ወንጀሌ ህግ አንቀጽ 346 ፣አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀጽ 26 ፣ የብሓራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤፌ.ኤክስ.ዱ. 49/2017
ቴሌግራም:
ስልክ፡ (+251) 0911538683
https://t.me/GetishSalewLaw
facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61555121422107